#ስልክአምባ
" 12 ሰዎች ናቸው የተገደሉት፤ .. ቤቶች ተቃጥለዋል፤ ከብቶችም እየተነዱ ተወስደዋል " - ነዋሪዎች
" 11 ሰዎች ስለመገደላቸው መረጃ ደርሶናል መረጃውን የማጣራት ስራ እየሰራን ነው " - ኢሰመኮ
️በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ ኖኖ ወረዳ ስልክ አምባ ከተማ ባለፈው ሠኞ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት 12 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ በ5 ቀበሌዎች ጥቃት መፈጸሙን ይህን ያደረጉት ደግመ የሸኔ ታጣቂዎች (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት) እንደሆኑ ገልጸዋል።
ከሟቾች አብዛኛዎቹ የአማራ ብሔር ተወላጆች መኾናቸውን ተናግረዋል።
ወደ 60 ቤት እህል ጭምር የያዘ መቃጠሉን እና በርካቶች ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሸሻቸውን ገልጸዋል። ከ100 በላይ ከብቶችም እየተነዱ ተወስደዋል።
አንድ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፥ ጥቃቱ ከተፈፀመ በኃላ ዘግይተው የደረሱት የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከታጣቂዎቹ ጋር ተኩስ ገጥመው እንደነበር አስረድተዋል።
ሌላ ነዋሪ ፤ " ኦነግ ሸኔ ነው የሚባለው ቁጥራቸው የበዛና ከባድ መሳሪያ ጭምር የታጠቁ ናቸው በተኛንበት 12 ሰዓት ላይ መጥተው ነው ጉዳት ያደረሱት " ብለዋል።
" እኛ ገበሬዎች ነን ምንም ኃይል የለን አቅም የለን በጣም ነው ጉዳት የደረሰብን " ያሉ ሲሆን ሴቶችን፣ አዛውንቶችን ከብቶችን በማሸሽ ወደጫካ ማስመለጥ እንደተቻለ አቅም የሌላቸው አዛውንቶች ግን መገደላቸውን እነሱንም ሲቀብሩ እንዳመሹ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፥ በአካባቢው በታጣቂዎች ግጭት ተነስቶ 11 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ከአካባቢው መረጃ እንደደረሰው ገልጾ መረጃውን ለማጣራት ጥረት ላይ መሆኑን አመልክቷል።
የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል በነዋሪዎች የቀረበበትን ክስ አስተባብሎ፤ " እኛ እንዲህ ዓይነት ድርጊት ውስጥ እጃችን የለበትም " ብሏል። " ጉዳዩ በገለልተኛ አካል ምርመራ ሊደረግበት ይገባል " ሲልም ገልጿል።
ክልሉ እስካሁን በይፋ የሰጠው መረጃ የለም።
@tikvahethiopia
" 12 ሰዎች ናቸው የተገደሉት፤ .. ቤቶች ተቃጥለዋል፤ ከብቶችም እየተነዱ ተወስደዋል " - ነዋሪዎች
" 11 ሰዎች ስለመገደላቸው መረጃ ደርሶናል መረጃውን የማጣራት ስራ እየሰራን ነው " - ኢሰመኮ
️በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ ኖኖ ወረዳ ስልክ አምባ ከተማ ባለፈው ሠኞ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት 12 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ በ5 ቀበሌዎች ጥቃት መፈጸሙን ይህን ያደረጉት ደግመ የሸኔ ታጣቂዎች (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት) እንደሆኑ ገልጸዋል።
ከሟቾች አብዛኛዎቹ የአማራ ብሔር ተወላጆች መኾናቸውን ተናግረዋል።
ወደ 60 ቤት እህል ጭምር የያዘ መቃጠሉን እና በርካቶች ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሸሻቸውን ገልጸዋል። ከ100 በላይ ከብቶችም እየተነዱ ተወስደዋል።
አንድ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፥ ጥቃቱ ከተፈፀመ በኃላ ዘግይተው የደረሱት የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከታጣቂዎቹ ጋር ተኩስ ገጥመው እንደነበር አስረድተዋል።
ሌላ ነዋሪ ፤ " ኦነግ ሸኔ ነው የሚባለው ቁጥራቸው የበዛና ከባድ መሳሪያ ጭምር የታጠቁ ናቸው በተኛንበት 12 ሰዓት ላይ መጥተው ነው ጉዳት ያደረሱት " ብለዋል።
" እኛ ገበሬዎች ነን ምንም ኃይል የለን አቅም የለን በጣም ነው ጉዳት የደረሰብን " ያሉ ሲሆን ሴቶችን፣ አዛውንቶችን ከብቶችን በማሸሽ ወደጫካ ማስመለጥ እንደተቻለ አቅም የሌላቸው አዛውንቶች ግን መገደላቸውን እነሱንም ሲቀብሩ እንዳመሹ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፥ በአካባቢው በታጣቂዎች ግጭት ተነስቶ 11 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ከአካባቢው መረጃ እንደደረሰው ገልጾ መረጃውን ለማጣራት ጥረት ላይ መሆኑን አመልክቷል።
የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል በነዋሪዎች የቀረበበትን ክስ አስተባብሎ፤ " እኛ እንዲህ ዓይነት ድርጊት ውስጥ እጃችን የለበትም " ብሏል። " ጉዳዩ በገለልተኛ አካል ምርመራ ሊደረግበት ይገባል " ሲልም ገልጿል።
ክልሉ እስካሁን በይፋ የሰጠው መረጃ የለም።
@tikvahethiopia