TIKVAH-ETHIOPIA
በትግራይ እና አማራ አዋሳኝ ስፍራ ምን ተፈጠረ ? በትግራይ ክልል እና በአማራ ክልል የራያ ወረዳ አዋሳኝ አከባቢዎች በትጥቅ የተደገፈ ግጭት እንደነበረ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመስማት ችሏል። የካቲት 6 / 2016 ዓ.ም የተቀሰቀሰው መጠነኛ ነው የተባለው ግጭት በሀገር መከላከያ ሰራዊት ጥረት ሊቆም እንደቻለ ነው የተነገረው። ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የአላማጣ ከተማ ነዋሪ ለመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ…
" ችግሩ በሰላማዊ መንገድ የፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ እንዲፈታ ፍላጎታችን ነው " - አቶ ኃይሉ አበራ
ከሰሞኑን #በአማራ እና #በትግራይ ክልሎች መካከል ተቀሰቀሰ የተባለውን ለአጭር ጊዜ የቆየ የተኩስ ልውውጥ በተመለከተ በአማራ ክልል በኩል ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ በአሁን ሰዓት በአማራ ክልል ስር እየተዳደረ ያለው የአላማጣ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የሆኑት አቶ ኃይሉ አበራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ ኃይሉ አበራ ምን አሉ ?
- በባላ አቅጣጫ ማሮ በሚባል ቦታ ከእኛ ሚሊሻ ጋ ገጠሙ። ተመትተው ተመልሰዋል አሁን ላይ ቦታውን ለቀዋል።
- ወደ ሁለት ቀበሌዎች ወረራ ለማድርግ ሙከራ አድርገው ነበር። በመጀመሪያ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የሰላም ጥሪ ነበር እየተላለፈ የከረመው፣ አሁን ግን እሳቢያቸው የነበረው በወረራ ቦታውን ይዘው ‘እንደራደራለን’ አይነት፣ በተፈናቃይ ስም ግጭት መፍጠር ነው።
* የጉዳት መጠንን በተመለከተ ፦ " እኛ ጋር የደረሰ ጉዳት የለም። እነሱ ግን ሊያጠቃ የመጣ ምንጊዜም ተመትቶ ነው የሚሄደው። የተወሰኑት ተመተው ሂደዋል። " ብለዋል።
- አላማጣን፣ ኮረምን ለመውረር እንዲሁ በጡሩባ እና በጩኽት የሚለቅ ህዝብ መስሏቸው ነበር። ሕዝቡ ማዕበል ሆኖ ነው የወጣው ከዚህ በኋላ የሰላሙን ጥሪ የማይቀበሉት እና ሰላሙን የማይፈልጉት ከሆነ አሁን እኛ ህዝባዊ አድርገነዋል።
* የመፍትሄ ሀሳብን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳው ጥያቄ ፦ " ችግሩ በሰላማዊ መንገድ የፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ እንዲፈታ ፍላጎታችን ነው። 'አይ የለም ህዝቡ ወደ ሚፈልገው መሆን አይችልም፣ እኔ ብቻ ነኝ የምወስንልህ' የሚል እሳቤ የሚቀሳቀስ ከሆነ እሱ የሚቻል አይደለም። ፋሽኑም ግዜውም አልፎበታል። አሁን ላይ ወደ ኋላ የሚመልስ ኃይል የለም። Already ሁሉም ተደራጅቷአል። " ብለዋል።
- የትግራይ ፖለቲከኞችም ሀይ ሀይ የሚሉትን ዲያስፖራ ቆም ብለው ሊያስቡ ይገባል። ' አይ የለም የትግራይ ሉዐላዊ ግዛት ' እያሉ በወረራ የያዙትን ቦታ 'በኃይል እናስመልሳለን' የሚሉ ከሆነ ግን ከዚህ በኋላ የሚኖረው ሕዝባዊ ነው። ሕዝባዊ ከሆነ ደግሞ አደጋው የከፋ ነው የሚሆነው። በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ቀውስ ነው ሊፈጠር የሚችለው። ይህንን እንዲያስቡበት ነው የምናስገነዝበው።
- እኛ የማንንም መብት አንጋፋም የትኛውንም ሰው በማንነቱ ምክንያት የምናደርስበት ጉዳት የለም። ሊወርና ሊገድል ኃይል ከመጣ ግን ህዝብን መቆጣጠር አይቻልም። ስለዚህ ነገሮች ከቁጥጥር ውጭ ከመሆናቸው በፊት ቆም ብለው ቢያስቡ ይሻላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 9 ቀን 2016 ዓ/ም
አላማጣ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን #በአማራ እና #በትግራይ ክልሎች መካከል ተቀሰቀሰ የተባለውን ለአጭር ጊዜ የቆየ የተኩስ ልውውጥ በተመለከተ በአማራ ክልል በኩል ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ በአሁን ሰዓት በአማራ ክልል ስር እየተዳደረ ያለው የአላማጣ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ የሆኑት አቶ ኃይሉ አበራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ ኃይሉ አበራ ምን አሉ ?
- በባላ አቅጣጫ ማሮ በሚባል ቦታ ከእኛ ሚሊሻ ጋ ገጠሙ። ተመትተው ተመልሰዋል አሁን ላይ ቦታውን ለቀዋል።
- ወደ ሁለት ቀበሌዎች ወረራ ለማድርግ ሙከራ አድርገው ነበር። በመጀመሪያ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የሰላም ጥሪ ነበር እየተላለፈ የከረመው፣ አሁን ግን እሳቢያቸው የነበረው በወረራ ቦታውን ይዘው ‘እንደራደራለን’ አይነት፣ በተፈናቃይ ስም ግጭት መፍጠር ነው።
* የጉዳት መጠንን በተመለከተ ፦ " እኛ ጋር የደረሰ ጉዳት የለም። እነሱ ግን ሊያጠቃ የመጣ ምንጊዜም ተመትቶ ነው የሚሄደው። የተወሰኑት ተመተው ሂደዋል። " ብለዋል።
- አላማጣን፣ ኮረምን ለመውረር እንዲሁ በጡሩባ እና በጩኽት የሚለቅ ህዝብ መስሏቸው ነበር። ሕዝቡ ማዕበል ሆኖ ነው የወጣው ከዚህ በኋላ የሰላሙን ጥሪ የማይቀበሉት እና ሰላሙን የማይፈልጉት ከሆነ አሁን እኛ ህዝባዊ አድርገነዋል።
* የመፍትሄ ሀሳብን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳው ጥያቄ ፦ " ችግሩ በሰላማዊ መንገድ የፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ እንዲፈታ ፍላጎታችን ነው። 'አይ የለም ህዝቡ ወደ ሚፈልገው መሆን አይችልም፣ እኔ ብቻ ነኝ የምወስንልህ' የሚል እሳቤ የሚቀሳቀስ ከሆነ እሱ የሚቻል አይደለም። ፋሽኑም ግዜውም አልፎበታል። አሁን ላይ ወደ ኋላ የሚመልስ ኃይል የለም። Already ሁሉም ተደራጅቷአል። " ብለዋል።
- የትግራይ ፖለቲከኞችም ሀይ ሀይ የሚሉትን ዲያስፖራ ቆም ብለው ሊያስቡ ይገባል። ' አይ የለም የትግራይ ሉዐላዊ ግዛት ' እያሉ በወረራ የያዙትን ቦታ 'በኃይል እናስመልሳለን' የሚሉ ከሆነ ግን ከዚህ በኋላ የሚኖረው ሕዝባዊ ነው። ሕዝባዊ ከሆነ ደግሞ አደጋው የከፋ ነው የሚሆነው። በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ቀውስ ነው ሊፈጠር የሚችለው። ይህንን እንዲያስቡበት ነው የምናስገነዝበው።
- እኛ የማንንም መብት አንጋፋም የትኛውንም ሰው በማንነቱ ምክንያት የምናደርስበት ጉዳት የለም። ሊወርና ሊገድል ኃይል ከመጣ ግን ህዝብን መቆጣጠር አይቻልም። ስለዚህ ነገሮች ከቁጥጥር ውጭ ከመሆናቸው በፊት ቆም ብለው ቢያስቡ ይሻላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 9 ቀን 2016 ዓ/ም
አላማጣ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ይሄ ' የአማራ አዋሳኝ ' የሚባለው ቀልድ መቆም ያለበት ነው " - አቶ ረዳዒ ኃለፎም
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳዒ ሀለፎም ሰሞኑን ስለነበረው የተኩስ ልውውጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ ረዳዒ ሀለፎም ምን አሉ ?
- ግጭቱ ራያ አላማጣ ሳይሆን ጨርጨር አካባቢ ነው። ይሄ የአማራ አዋሳኝ የሚባለው #ቀልድ ደግሞ መቆም ያለበት ነው።
- የትግራይ መሬት ነው ጨርጨር። ጨርጨር ትግራይ እንጂ አማራ ሆኖ አያውቅም። አሁንም አይደለም። እዚያው የአማራ ታጣቂዎች አሉ። እነዛ የአማራ ታጣቂዎች በእኛ ሚሊሻዎች ላይ የፈጸሙት ጥቃት ነው። የአጭር ጊዜ ተኩስ ልውውጥ ነበር ቁሟል አሁን ግጭቱ የለም።
* ጉዳዩን በተመለከተ ምን እየተሰራ እንደሆነ ለቀረበ ጥያቄ ፦ " በእኛ በኩል (በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርም) ከላይ ከሚመለከታቸው የፌደራሉ መንግሥትም የተወሰነ ንግግር እየተደረበት ነው " ብለዋል።
* የመፍትሄ ሀሳብን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳው ጥያቄ ፦
" የመጀመሪያው ነገር ሕገ መንግሥቱን ማክበር ነው። የአዋሳኝ ጉዳይ አይደለም መሀል ትግራይ ላይ ነው ችግሩ እየተፈጠረ ያለው። ወረው በኃይል ከያዙት መሬት ላይ ነው አሁን ደግሞ መልሰው ጥቃት እየፈጸሙ ያለት። ይሄ ትክክል አይደለም። ለማናችንም የሚጠቅም ነገር አይደለም።
መሆን ያለበት ጥያቄ ያለው አካልም በሕጉ መሠረት ካልሆነ በቀር የሆነ አጋጣሚ ተጠቅሞ ‘ጉልበት አለኝ፣ ይጠቅመኛል’ ብሎ ባሰበ ጊዜ የኃይል አማራጭ የሚወስድ ከሆነ፣ ቢያንስ የሕዝቦች ዘላቂ ወዳጅነትና መቀራረብ የሚያረጋግጥ አይደለም። ከዚህ መቆጠብ ነው ያለብን " ብለዋል።
- የፌደራል መንግሥት ሲቪሊያንን የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ድሮም ቢሆን በውሉም በተመሳሳይ ፤ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖም ከመከላከያ ሰራዊት ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ከትግራይ ክልል እንዲወጡ ውሉም ያስገድዳል። አለመውጣታቸውም ብቻ ሳይሆን በየትኛውም የአማራ ታጣቂዎች ባሉበት አካባቢ ሴቶች እየተደፈሩ ናቸው። ሰብዓዊ መብቶች እየተረገጡ ናቸው። ብዙ ጥፋቶች እየተፈጸሙ ናቸው። ስለዚህ ውሉን በአግባቡ ተግባሪዊ ማድረግና በቁጥጥር ሥር መስራት ከተቻለ ብቻ ነው ወደ ሰላም ማምራት የምንችለው።
- በአማራ ክልል እየተፈጸሙ ያሉት ትክክል ስላልሆኑ አደብ መያዝ ያስፈልጋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 8/2016 ዓ/ም
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳዒ ሀለፎም ሰሞኑን ስለነበረው የተኩስ ልውውጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ ረዳዒ ሀለፎም ምን አሉ ?
- ግጭቱ ራያ አላማጣ ሳይሆን ጨርጨር አካባቢ ነው። ይሄ የአማራ አዋሳኝ የሚባለው #ቀልድ ደግሞ መቆም ያለበት ነው።
- የትግራይ መሬት ነው ጨርጨር። ጨርጨር ትግራይ እንጂ አማራ ሆኖ አያውቅም። አሁንም አይደለም። እዚያው የአማራ ታጣቂዎች አሉ። እነዛ የአማራ ታጣቂዎች በእኛ ሚሊሻዎች ላይ የፈጸሙት ጥቃት ነው። የአጭር ጊዜ ተኩስ ልውውጥ ነበር ቁሟል አሁን ግጭቱ የለም።
* ጉዳዩን በተመለከተ ምን እየተሰራ እንደሆነ ለቀረበ ጥያቄ ፦ " በእኛ በኩል (በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርም) ከላይ ከሚመለከታቸው የፌደራሉ መንግሥትም የተወሰነ ንግግር እየተደረበት ነው " ብለዋል።
* የመፍትሄ ሀሳብን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳው ጥያቄ ፦
" የመጀመሪያው ነገር ሕገ መንግሥቱን ማክበር ነው። የአዋሳኝ ጉዳይ አይደለም መሀል ትግራይ ላይ ነው ችግሩ እየተፈጠረ ያለው። ወረው በኃይል ከያዙት መሬት ላይ ነው አሁን ደግሞ መልሰው ጥቃት እየፈጸሙ ያለት። ይሄ ትክክል አይደለም። ለማናችንም የሚጠቅም ነገር አይደለም።
መሆን ያለበት ጥያቄ ያለው አካልም በሕጉ መሠረት ካልሆነ በቀር የሆነ አጋጣሚ ተጠቅሞ ‘ጉልበት አለኝ፣ ይጠቅመኛል’ ብሎ ባሰበ ጊዜ የኃይል አማራጭ የሚወስድ ከሆነ፣ ቢያንስ የሕዝቦች ዘላቂ ወዳጅነትና መቀራረብ የሚያረጋግጥ አይደለም። ከዚህ መቆጠብ ነው ያለብን " ብለዋል።
- የፌደራል መንግሥት ሲቪሊያንን የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ድሮም ቢሆን በውሉም በተመሳሳይ ፤ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖም ከመከላከያ ሰራዊት ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ከትግራይ ክልል እንዲወጡ ውሉም ያስገድዳል። አለመውጣታቸውም ብቻ ሳይሆን በየትኛውም የአማራ ታጣቂዎች ባሉበት አካባቢ ሴቶች እየተደፈሩ ናቸው። ሰብዓዊ መብቶች እየተረገጡ ናቸው። ብዙ ጥፋቶች እየተፈጸሙ ናቸው። ስለዚህ ውሉን በአግባቡ ተግባሪዊ ማድረግና በቁጥጥር ሥር መስራት ከተቻለ ብቻ ነው ወደ ሰላም ማምራት የምንችለው።
- በአማራ ክልል እየተፈጸሙ ያሉት ትክክል ስላልሆኑ አደብ መያዝ ያስፈልጋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 8/2016 ዓ/ም
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
#ሆሣዕና
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2016 ዓ/ም ሆሣዕና በዓል አስመልክተው በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተገኝተው ትምህርት፣ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል።
ቅዱስነታቸው ፤ የዛሬው የሆሣዕና በዓል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙት እና የሚከተሉት ህዝብ በተለይ አእሩግ እና ሕጻናት " ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም " በማለት ጌታችንን መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል መሆኑን አስረድተዋል።
ቅዱስ ፓትርያርኩ ሰሙነ ህማማትንም አስመልክተው ለመላው ምዕመናን አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ቅዱስነታቸው ፦
" ሰሙነ ሕማማትን እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አስጀምሮ እንዲያስፈጽመን ለብርሃነ ትንሳዔው እንዲያበቃን እግዚአብሔር አምላካችንን እንለምነዋለን።
ሰሙነ ሕማማትን ሁላችንም በየአካባቢያችን ባለው ቤተክርስቲያን ተገኝተን ሰሞነ ሕማማትን ፣ ስግደቱን ፣ ጸሎቱን፣ ልመናውን በሕብረት ወደ እግዚአብሔር አምላካችን እንጸልያለን።
በጸሎታችን ደግሞ ያለውን ችግር ሁሉ እንዲያስወግድልን ፦
- #ሰላሙን፣
- #ፍቅሩን፣
- #አንድነቱን እንዲሰጠን የሁላችንም ጸሎትና ምኞት ነውና እግዚአብሔር አምላካችን ከዚያ ያድርሰን ሰሙነ ሕማማቱን በሰላም ያስፈጽመን። "
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2016 ዓ/ም ሆሣዕና በዓል አስመልክተው በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተገኝተው ትምህርት፣ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል።
ቅዱስነታቸው ፤ የዛሬው የሆሣዕና በዓል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙት እና የሚከተሉት ህዝብ በተለይ አእሩግ እና ሕጻናት " ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ሚመጣ የተባረከ ነው ፤ ሆሣዕና በአርያም " በማለት ጌታችንን መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል መሆኑን አስረድተዋል።
ቅዱስ ፓትርያርኩ ሰሙነ ህማማትንም አስመልክተው ለመላው ምዕመናን አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ቅዱስነታቸው ፦
" ሰሙነ ሕማማትን እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አስጀምሮ እንዲያስፈጽመን ለብርሃነ ትንሳዔው እንዲያበቃን እግዚአብሔር አምላካችንን እንለምነዋለን።
ሰሙነ ሕማማትን ሁላችንም በየአካባቢያችን ባለው ቤተክርስቲያን ተገኝተን ሰሞነ ሕማማትን ፣ ስግደቱን ፣ ጸሎቱን፣ ልመናውን በሕብረት ወደ እግዚአብሔር አምላካችን እንጸልያለን።
በጸሎታችን ደግሞ ያለውን ችግር ሁሉ እንዲያስወግድልን ፦
- #ሰላሙን፣
- #ፍቅሩን፣
- #አንድነቱን እንዲሰጠን የሁላችንም ጸሎትና ምኞት ነውና እግዚአብሔር አምላካችን ከዚያ ያድርሰን ሰሙነ ሕማማቱን በሰላም ያስፈጽመን። "
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia