#Kenya
የጎረቤት ኬንያ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ለማውጣት ዜጎች ክፍያ እንዲፈጽሙ መንግሥት ያወጣውን መመሪያ #አገደ።
የኬንያ መንግሥት ይህን መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ ዜጎች ቅሬታቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ።
እንደ ቢቢሲ ዘገባ ማጋሬ ጊኬንይ የተባሉ ሐኪም ናቸው መንግሥት አዲሱን መመሪያ ያወጣው “ድንገተኛ እና ምክንያታዊ ባልሆነ መንገድ” ነው ሲሉ የሕዝብ ድምፅ በማሰባሰብ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት የወሰዱት።
የተሰበሰበው የሕዝብ ድምፅ እንደሚለው በአዲሱ መመሪያ መሠረት፤ በርካታ ዜጎች መታወቂያ ካርድ በቀላሉ ማግኘት አይችሉም።
ከዚህ ቀደም በነፃ ይሰጥ የነበረው ብሔራዊ መታወቂያ ካርድ አሁን 1 ሺህ ሺልንግ [370 ብር ገደማ] እንዲሆን መንግሥት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አዟል።
መታወቂያ ለማሳደስ ደግሞ ኬንያዊያን 2 ሺህ ሺልንግ እንዲከፍሉ ተጠይቀዋል።
ኬንያዊያን እያሻቀበ ባለው የኑሮ ግሽበት ምሬታቸውን እየገለጡ ባሉበት ወቅት ነው መንግሥት ገቢውን ለማሳደግ ሲል ዜጎች ከዚህ ቀደም በነፃ አሊያም በርካሽ የሚያገኟቸውን አገልግሎቶች በበለጠ ክፍያ እንዲሆን ያደረገው።
በርካታ ኬንያዊያን በሚከፍሉት ግብር አማካይነት ተግባራዊ እየሆኑ ላሉ የመንግሥት ግልጋሎቶች ተጨማሪ ክፍያ መጠየቃችን ተገቢ አይደለም እያሉ ናቸው።
አዲሱ መመሪያ መታወቂያ ካርድ ብቻ ሳይሆን ፓስፖርት፣ የጋብቻ ወረቀት፣ የሥራ እና የመኖሪያ ፈቃድ እንዲሁም የልደት እና ሞት ምስክር ወረቀት ለማውጣትም ክፍያ ይጠይቃል።
አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት አሊያም ለማሳደስ ይጠየቅ የነበረው ክፍያ 50 በመቶ ሲያድግ የልደት እና ሞት ወረቀት ለማውጣት የሚጠየቅ ክፍያ በአራት እጥፍ አድጎ 200 ሺልንግ ገብቷል።
መንግሥት በተጨማሪ ዜግነት አሊያም የመኖሪያ ፈቃድ ለማስጠት የሚጠይቀውን ክፍያ እጥፍ አድርጎታል።
ከኬንያዊያን ዜጎች በውጭ ሃገር የተወለዱ ልጆች የኬንያ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት የሚጠየቁት ክፍያ 1 ሚሊዮን ሺልንግ ሆኗል።
በደንገት የተጫኑት የክፍያ መመሪያዎች አቅም የሌላቸው ዜጎች የመንግሥትን ግልጋሎት ተጠቅመው አስፈላጊ ወረቀት ለማግኘት ሊቸገሩ ይችላሉ የሚል ስጋት ጭሯል።
ባለፈው ዓመት መስከረም ወደ ሥልጣን የመጡት የፕሬዝደንት ሩቶ መንግሥት በርካታ የግብር ዓይነቶችን ዜጎች ላይ የጣለ ሲሆን የነዳጅ ዋጋ ከፍ እንዲልም አድርጓል።
የብሔራዊ ፓርክ መግቢያ ዋጋን ጨምሮ በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶች ክፍያ ከፍ እንዲልም ሆኗል።
ባለፈው ሳምንት የገቢዎች መ/ቤት ባለሥልጣናት ወደ ኬንያ የሚመጡ ዜጎችም ሆኑ ጎብኝዎች ከ500 ዶላር በላይ ተመን ያለው ዕቃ ይዘው ከተገኙ ይቀረጣሉ ብሏል።
ፕሬዝደንት ሩቶ እስካሁን ስለ ዋጋው ጭማሪ ያሉት ነገር ባይኖርም ሐሙስ ዕለት ለሃገሪቱ ዜጎች ባስተላለፉት መልዕክት ኬንያዊያንን ከዕዳ ጫና ለማላቀቅ " ቀላል ያልሆኑ ግን አስፈላጊ " ውሳኔዎችን ለመውሰድ ተገድጃለሁ ብለዋል።
#BBC
@tikvahethiopia
የጎረቤት ኬንያ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ለማውጣት ዜጎች ክፍያ እንዲፈጽሙ መንግሥት ያወጣውን መመሪያ #አገደ።
የኬንያ መንግሥት ይህን መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ ዜጎች ቅሬታቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ።
እንደ ቢቢሲ ዘገባ ማጋሬ ጊኬንይ የተባሉ ሐኪም ናቸው መንግሥት አዲሱን መመሪያ ያወጣው “ድንገተኛ እና ምክንያታዊ ባልሆነ መንገድ” ነው ሲሉ የሕዝብ ድምፅ በማሰባሰብ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት የወሰዱት።
የተሰበሰበው የሕዝብ ድምፅ እንደሚለው በአዲሱ መመሪያ መሠረት፤ በርካታ ዜጎች መታወቂያ ካርድ በቀላሉ ማግኘት አይችሉም።
ከዚህ ቀደም በነፃ ይሰጥ የነበረው ብሔራዊ መታወቂያ ካርድ አሁን 1 ሺህ ሺልንግ [370 ብር ገደማ] እንዲሆን መንግሥት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አዟል።
መታወቂያ ለማሳደስ ደግሞ ኬንያዊያን 2 ሺህ ሺልንግ እንዲከፍሉ ተጠይቀዋል።
ኬንያዊያን እያሻቀበ ባለው የኑሮ ግሽበት ምሬታቸውን እየገለጡ ባሉበት ወቅት ነው መንግሥት ገቢውን ለማሳደግ ሲል ዜጎች ከዚህ ቀደም በነፃ አሊያም በርካሽ የሚያገኟቸውን አገልግሎቶች በበለጠ ክፍያ እንዲሆን ያደረገው።
በርካታ ኬንያዊያን በሚከፍሉት ግብር አማካይነት ተግባራዊ እየሆኑ ላሉ የመንግሥት ግልጋሎቶች ተጨማሪ ክፍያ መጠየቃችን ተገቢ አይደለም እያሉ ናቸው።
አዲሱ መመሪያ መታወቂያ ካርድ ብቻ ሳይሆን ፓስፖርት፣ የጋብቻ ወረቀት፣ የሥራ እና የመኖሪያ ፈቃድ እንዲሁም የልደት እና ሞት ምስክር ወረቀት ለማውጣትም ክፍያ ይጠይቃል።
አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት አሊያም ለማሳደስ ይጠየቅ የነበረው ክፍያ 50 በመቶ ሲያድግ የልደት እና ሞት ወረቀት ለማውጣት የሚጠየቅ ክፍያ በአራት እጥፍ አድጎ 200 ሺልንግ ገብቷል።
መንግሥት በተጨማሪ ዜግነት አሊያም የመኖሪያ ፈቃድ ለማስጠት የሚጠይቀውን ክፍያ እጥፍ አድርጎታል።
ከኬንያዊያን ዜጎች በውጭ ሃገር የተወለዱ ልጆች የኬንያ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት የሚጠየቁት ክፍያ 1 ሚሊዮን ሺልንግ ሆኗል።
በደንገት የተጫኑት የክፍያ መመሪያዎች አቅም የሌላቸው ዜጎች የመንግሥትን ግልጋሎት ተጠቅመው አስፈላጊ ወረቀት ለማግኘት ሊቸገሩ ይችላሉ የሚል ስጋት ጭሯል።
ባለፈው ዓመት መስከረም ወደ ሥልጣን የመጡት የፕሬዝደንት ሩቶ መንግሥት በርካታ የግብር ዓይነቶችን ዜጎች ላይ የጣለ ሲሆን የነዳጅ ዋጋ ከፍ እንዲልም አድርጓል።
የብሔራዊ ፓርክ መግቢያ ዋጋን ጨምሮ በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶች ክፍያ ከፍ እንዲልም ሆኗል።
ባለፈው ሳምንት የገቢዎች መ/ቤት ባለሥልጣናት ወደ ኬንያ የሚመጡ ዜጎችም ሆኑ ጎብኝዎች ከ500 ዶላር በላይ ተመን ያለው ዕቃ ይዘው ከተገኙ ይቀረጣሉ ብሏል።
ፕሬዝደንት ሩቶ እስካሁን ስለ ዋጋው ጭማሪ ያሉት ነገር ባይኖርም ሐሙስ ዕለት ለሃገሪቱ ዜጎች ባስተላለፉት መልዕክት ኬንያዊያንን ከዕዳ ጫና ለማላቀቅ " ቀላል ያልሆኑ ግን አስፈላጊ " ውሳኔዎችን ለመውሰድ ተገድጃለሁ ብለዋል።
#BBC
@tikvahethiopia
ቪድዮ፦ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን በረራ ላይ ሳለ #መስኮቱ_መገንጠሉን ተከትሎ አንድ የአሜሪካ አየር መንገድ አውሮፕላኑን ከበረራ አግዶታል።
የአሜሪካው አላስካ አየር መንገድ በቁጥር 65 የሆኑ 737 ማክስ 9 አውሮፕላኖቹን አግዷል።
እገዳው በበረራ ወቅት የአንደኛው አውሮፕላን መስኮት ተገንጥሎ አውሮፕላኑ በአስቸኳይ ለማረፍ ከተገደደ በኋላ ነው።
አርብ ዕለት በኦሬጎን ግዛት ከፖርትላንድ ከተማ ተነስቶ ወደ ካሊፎርኒያ ሲበር የነበረው አውሮፕላን የገጠመውን አደጋ ተከትሎ ከ35 ደቂቃዎች በረራ በኋላ በመነሻው ለማረፍ ተገዷል።
አየር መንገዱ በአውሮፕላኑ ተሳፍረው የነበሩት 177 ተሳፋሪዎች እና ሠራተኞች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው አውሮፕላኑ #በሰላም አርፏል ብሏል።
የአደጋው መንስዔ እስኪጣራ ድረስ ሁሉንም 737 ማክስ 9 አውሮፕላኖች በጊዜያዊነት ከበረራ እንዳገደ አየር መንገዱ አስታውቋል።
ይህ ቦይንግ ሰራሹ አውሮፕላን ባለፉት ዓመታት መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።
ከአምስት ዓመት በፊት #በኢትዮጵያ እና #ኢንዶኔዢያ ባጋጠመ አደጋ ምክንያት ከበረራ ታግዶ የነበረው ይህ ማክስ 737 ዝርያ መሆኑ ይታወቃል። #BBC
@tikvahethiopia
የአሜሪካው አላስካ አየር መንገድ በቁጥር 65 የሆኑ 737 ማክስ 9 አውሮፕላኖቹን አግዷል።
እገዳው በበረራ ወቅት የአንደኛው አውሮፕላን መስኮት ተገንጥሎ አውሮፕላኑ በአስቸኳይ ለማረፍ ከተገደደ በኋላ ነው።
አርብ ዕለት በኦሬጎን ግዛት ከፖርትላንድ ከተማ ተነስቶ ወደ ካሊፎርኒያ ሲበር የነበረው አውሮፕላን የገጠመውን አደጋ ተከትሎ ከ35 ደቂቃዎች በረራ በኋላ በመነሻው ለማረፍ ተገዷል።
አየር መንገዱ በአውሮፕላኑ ተሳፍረው የነበሩት 177 ተሳፋሪዎች እና ሠራተኞች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው አውሮፕላኑ #በሰላም አርፏል ብሏል።
የአደጋው መንስዔ እስኪጣራ ድረስ ሁሉንም 737 ማክስ 9 አውሮፕላኖች በጊዜያዊነት ከበረራ እንዳገደ አየር መንገዱ አስታውቋል።
ይህ ቦይንግ ሰራሹ አውሮፕላን ባለፉት ዓመታት መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።
ከአምስት ዓመት በፊት #በኢትዮጵያ እና #ኢንዶኔዢያ ባጋጠመ አደጋ ምክንያት ከበረራ ታግዶ የነበረው ይህ ማክስ 737 ዝርያ መሆኑ ይታወቃል። #BBC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EHRC የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በአማራ ከልል ምዕራብ ጎጃም ዞን መርዓዊ ከተማ በ20/05/2016 ዓ.ም በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኖች መካከል በነበረ ግጭት ከፍተኛ የሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሱት ባወጣው መግለጫ አሳውቋል። በእዚህ ግጭት ምክንያት በመርዓዊ ከተማ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ እንደነበር…
#USA #ETHIOPIA #MERAWI
በአማራ ክልል መርዓዊ ከተማ ሰላማዊ ሰዎችን ኢላማ በማድረግ ግድያ የፈጸሙ ላይ ምርመራ ተደርጎ ለፍርድ እንዲቀርቡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጠየቁ።
አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በኤምባሲው የX ገጽ ላይ ባወጡት መልዕክት በመርዓዊ ከተማ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በሚመለከት የወጡ ሪፖርቶች የአሜሪካ መንግሥትን እንደሚያሳስበው ገልጸዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ፣ የክስተቱን አሳሳቢነት ከመግለጻቸው ባሻገር " የግድያውን ፈጻሚዎች ለሕግ ለማቅረብ " ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ተቆጣጣሪዎች ምንም ገደብ ሳይደረግባቸው ወደ ሥፍራው እንዲንቀሳቀሱ እንዲፈቀድላቸው እንዲሁም በግድያው ዙሪያ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።
በአገሪቱ ባሉት የአማራ እና የኦሮሚያ ክልሎችን ጨምሮ በሌሎችም ቦታዎች ላይ " በመንግሥት እና ከመንግሥት ውጪ በሆኑ ኃይሎች በተመሳሳይ የመብት ጥሰቶች እና ጥቃቶችን መፈጸማቸውን የሚያመልክቱ በርካታ የሚረብሹ ሪፖርቶች " እየወጡ መሆናቸውንም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።
" ኃይል ሳይሆን ውይይት ብቸኛው አማራጭ ነው"ም ሲሉ አሳውቀዋል። #USEmbassy #BBC
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል መርዓዊ ከተማ ሰላማዊ ሰዎችን ኢላማ በማድረግ ግድያ የፈጸሙ ላይ ምርመራ ተደርጎ ለፍርድ እንዲቀርቡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጠየቁ።
አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በኤምባሲው የX ገጽ ላይ ባወጡት መልዕክት በመርዓዊ ከተማ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በሚመለከት የወጡ ሪፖርቶች የአሜሪካ መንግሥትን እንደሚያሳስበው ገልጸዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ፣ የክስተቱን አሳሳቢነት ከመግለጻቸው ባሻገር " የግድያውን ፈጻሚዎች ለሕግ ለማቅረብ " ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ተቆጣጣሪዎች ምንም ገደብ ሳይደረግባቸው ወደ ሥፍራው እንዲንቀሳቀሱ እንዲፈቀድላቸው እንዲሁም በግድያው ዙሪያ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።
በአገሪቱ ባሉት የአማራ እና የኦሮሚያ ክልሎችን ጨምሮ በሌሎችም ቦታዎች ላይ " በመንግሥት እና ከመንግሥት ውጪ በሆኑ ኃይሎች በተመሳሳይ የመብት ጥሰቶች እና ጥቃቶችን መፈጸማቸውን የሚያመልክቱ በርካታ የሚረብሹ ሪፖርቶች " እየወጡ መሆናቸውንም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።
" ኃይል ሳይሆን ውይይት ብቸኛው አማራጭ ነው"ም ሲሉ አሳውቀዋል። #USEmbassy #BBC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአማራ ክልል መንግሥት ምን አለ ? ዛሬ የአማራ ክልል መንግሥት ይፋዊ መግለጫ ሰጠ። የክልሉ መንግሥት ፥ " ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ከሷል። " ህወሓት የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት ማወጁና…
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከ ' ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ' ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።
በቃለምልልሱ ፥ ባለፉት ሳምንታት በአማራ እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች የነበረው ግጭት በ " የሚሊሻ አባላት " መካከል እንጂ መደበኛ ኃይሎች የተሳተፉበት አልነበረም ብለዋል።
" አማራ ክልል በኩል የነበሩ ሚሊሻዎች የተለያዩ አስጊ እንቅስቃሴያዎችን ሲያደርጉ ነበር። በእኛ በኩል ያሉ የሚሊሻ አባላት ምላሽ ሰጥተዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ያወጣውን መግለጫም " መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያላገናዘበ " ብለዋል።
የሰላም ስምምነቱ #ተፈጻሚ_እንዳይሆን እያደረገ ያለው " ሕጋዊ የልሆነ የአማራ አስተዳደር ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ጌታቸው በዚሁ ቃለ ምልልስ ፥ በሰላም ስምምነቱ መሰረት በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉትን ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ከስምምነት መደረሱን አስታውሰዋል።
" ሕጋዊ ያልሆኑ አስተዳደሮችን ለማፍረስ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር አብረን እየሠራን ነው። ከአማራ ክልል ጋርም ቢሆን በተወሰነ ደረጃ አብረን እየሠራን ነው " ብለዋል።
" የፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚሹ አካላት እንዳሉ ግን በጣም እርግጠኞች ነን " ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ጌታቸው እነዚህ አካላት እነማን እነደሆኑ በግልጽ በስም ጠርተው አልጠቀሱም።
#BBC #FocusonAfrica
@tikvahethiopia
በቃለምልልሱ ፥ ባለፉት ሳምንታት በአማራ እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች የነበረው ግጭት በ " የሚሊሻ አባላት " መካከል እንጂ መደበኛ ኃይሎች የተሳተፉበት አልነበረም ብለዋል።
" አማራ ክልል በኩል የነበሩ ሚሊሻዎች የተለያዩ አስጊ እንቅስቃሴያዎችን ሲያደርጉ ነበር። በእኛ በኩል ያሉ የሚሊሻ አባላት ምላሽ ሰጥተዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
የአማራ ክልል ያወጣውን መግለጫም " መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያላገናዘበ " ብለዋል።
የሰላም ስምምነቱ #ተፈጻሚ_እንዳይሆን እያደረገ ያለው " ሕጋዊ የልሆነ የአማራ አስተዳደር ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ጌታቸው በዚሁ ቃለ ምልልስ ፥ በሰላም ስምምነቱ መሰረት በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉትን ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ከስምምነት መደረሱን አስታውሰዋል።
" ሕጋዊ ያልሆኑ አስተዳደሮችን ለማፍረስ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር አብረን እየሠራን ነው። ከአማራ ክልል ጋርም ቢሆን በተወሰነ ደረጃ አብረን እየሠራን ነው " ብለዋል።
" የፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚሹ አካላት እንዳሉ ግን በጣም እርግጠኞች ነን " ሲሉ ተደምጠዋል።
አቶ ጌታቸው እነዚህ አካላት እነማን እነደሆኑ በግልጽ በስም ጠርተው አልጠቀሱም።
#BBC #FocusonAfrica
@tikvahethiopia