#ተመስገን_ደሳለኝ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ጥር 7 ቀን 2016 ዓ/ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰሚ ችሎት በቀረቡበት ወቅት፣ “ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን” ያሏቸውን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ከችሎት እንዲነሱ ጠይቀዋል።
ጋዜጠኛው ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ ቀጠሮ ተሰጥቶበት የነበረው ጉዳያቸው ከመታየቱ በፊት የሚያቀርቡት አቤቱታ እንዳላቸው ለዕለቱ ዳኞች ጥያቄ በማቅረብ ነው።
ስለሚያቀርቡት አቤቱታ ችሎቱ ለጋዜጠኛ ተመስገን አቤቱታቸውን እንዲገልጹ ከፈቀደላቸው በኋላ፣ “የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ አሕመድ መሐመድ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን በዚህ ጉዳይ ከችሎት እንዲነሱልኝ ምክንቻቶቼን አቀርባለሁ” ሲሉ ተደምጠዋል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ይህን ከገለጹ በኋላ የቀኝና የመሀል ዳኛ የለሆሳስ ንግግር አድርገው አቤቱታቸውን በፅሑፍ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ የሰጡ ሲሆን፣ ጋዜጠኛ ተመስገንም ፈቃድ ካገኙ በኋላ፣ “በእዚህ ችሎት በርካታ ጋዜጠኞች ስላሉ አቤቱታዬን በንባብ እንዳሰማ ሊፈቀድልኝ ይገባል” ብለውሸ ሲገልጹ፣ ፅሑፉን ባጭሩ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ ተሰጥተዋል።
አሳጥረው እንዲያቀርቡ ዳኞች በፈቀዱላቸው መሠረት ያነበቡት ፅሑፉ በዝርዝር ምን ይላል?
“ዐቃቤ ሕግ ጥቅምት 1/2015 ዓ.ም ባቀረበው የይግባኝ ቅሬታ 2ኛ ክስን በሚመለከት 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮች፤ እንዲሁም 3ኛ ክስን የይግባኝ ቅሬታ ያላቀረበበት መሆኑን ጠቅሶ ወደፊት፦ ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ውጤቱን ተመልክቶ የይግባኝ ቅሬታ እንደሚያቀርብበት በይግባኝ ማመልከቻው ላይ በግልጽ አመላክቶ እያለ፣
* ታህሳስ 17/2015 ዓ/ም መልስ ሰጪን ያስቀርባል በሚል ትዕዛዝ ከሰጡት ዳኞች መካከል አቶ መሐመድ አሕመድ የሚገኙበት መሆኑን አረጋግጫለሁ፡፡በችሎቱ የተሰጠው ትዕዛዝም ዐቃቤ ሕግ በ2ኛ ክስ ቅሬታ ያላቀረበባቸውን 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮችን በመጨመር፤
* እንዲሁም 3ኛ ክስን በማካተት በ1ኛ እና 2ኛ ክሶች መከላከል ሳያስፈልገው በነፃ እንዲሰናበት፣ 3ኛ ክስን በሚመለከት ክስ የቀረበበት ድንጋጌ ወደ ጥላቻ ንግግር ወይም የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከለከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 በመለወጥ እንዲከላከል በአብላጫ ድምጽ የተሰጠውን ብይን፤
*እንዲሁም የተጠቀሰውን አዋጅ ለጉዳዩ ያለውን አግባብነት መጣራት ያለበት መሆኑን ስለታመነበት መልስ ሰጪ ይቅረብ ብለናል በሚል ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡” የሚል ነው።
ጋዜጠኛ ተመስገን ያነበቡትና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ይኼው ሰነድ አክሎም፣ “ይህ ትዕዛዝ ዐቃቢ ህግ በይግባኝ አቤቱታው ከጠየቀው ዳኝነት በማለፍ የተሰጠ ትዕዛዝ መሆኑን መረዳት የሚቻል ከመሆኑም በላይ የመልስ ሰጪን መብት በብርቱ የሚጎዳ አድራጎት ነው” ይላል።
በተጨማሪ ፣ “ከላይ ስማቸውን የጠቀስኩት ዳኛ በዚህ ጉዳይ ከችሎት ሳይነሱ ይቀጥሉ ቢባል ጉዳዩ ፓለቲካዊ ይዘት ያለው እንደመሆኑ መጠን በመዝገቡ ላይ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ የማላምንና ወደ ፊትም የሚሰጠው ፍርድ ነጻና ገለልተኛ ይሆናል ብዬ ስለማላምን በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 33/1/ሠ መሠረት የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ መሐመድ አሕመድ በዚህ ጉዳይ ከችሎቱ እንዲነሱልኝ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ” ሲል ያትታል።
በመጨረሻም፣ የጋዜጠኛውን አቤቱታ ካደመጠ በኋላ ችሎቱ፣ የዳኛውን ከችሎት መነሳትና አለመነሳት ጥያቄን በተመለከተ ለመወሰን፣ እንዲሁም ጋዜጠኛ ተመስገን በዋናው ክሳቸው ይሰጣሉ ተብሎ የሚጠበቀውን መለስ ለመቀበል ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ኢዮብ ትኩዬ ነው።
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ጥር 7 ቀን 2016 ዓ/ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰሚ ችሎት በቀረቡበት ወቅት፣ “ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን” ያሏቸውን የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ ከችሎት እንዲነሱ ጠይቀዋል።
ጋዜጠኛው ይህን ጥያቄ ያቀረቡት ዛሬ ቀጠሮ ተሰጥቶበት የነበረው ጉዳያቸው ከመታየቱ በፊት የሚያቀርቡት አቤቱታ እንዳላቸው ለዕለቱ ዳኞች ጥያቄ በማቅረብ ነው።
ስለሚያቀርቡት አቤቱታ ችሎቱ ለጋዜጠኛ ተመስገን አቤቱታቸውን እንዲገልጹ ከፈቀደላቸው በኋላ፣ “የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ አሕመድ መሐመድ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ ስለማላምን በዚህ ጉዳይ ከችሎት እንዲነሱልኝ ምክንቻቶቼን አቀርባለሁ” ሲሉ ተደምጠዋል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ይህን ከገለጹ በኋላ የቀኝና የመሀል ዳኛ የለሆሳስ ንግግር አድርገው አቤቱታቸውን በፅሑፍ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ የሰጡ ሲሆን፣ ጋዜጠኛ ተመስገንም ፈቃድ ካገኙ በኋላ፣ “በእዚህ ችሎት በርካታ ጋዜጠኞች ስላሉ አቤቱታዬን በንባብ እንዳሰማ ሊፈቀድልኝ ይገባል” ብለውሸ ሲገልጹ፣ ፅሑፉን ባጭሩ እንዲያቀርቡ ማሳሰቢያ ተሰጥተዋል።
አሳጥረው እንዲያቀርቡ ዳኞች በፈቀዱላቸው መሠረት ያነበቡት ፅሑፉ በዝርዝር ምን ይላል?
“ዐቃቤ ሕግ ጥቅምት 1/2015 ዓ.ም ባቀረበው የይግባኝ ቅሬታ 2ኛ ክስን በሚመለከት 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮች፤ እንዲሁም 3ኛ ክስን የይግባኝ ቅሬታ ያላቀረበበት መሆኑን ጠቅሶ ወደፊት፦ ፍርድ ከተሰጠ በኋላ ውጤቱን ተመልክቶ የይግባኝ ቅሬታ እንደሚያቀርብበት በይግባኝ ማመልከቻው ላይ በግልጽ አመላክቶ እያለ፣
* ታህሳስ 17/2015 ዓ/ም መልስ ሰጪን ያስቀርባል በሚል ትዕዛዝ ከሰጡት ዳኞች መካከል አቶ መሐመድ አሕመድ የሚገኙበት መሆኑን አረጋግጫለሁ፡፡በችሎቱ የተሰጠው ትዕዛዝም ዐቃቤ ሕግ በ2ኛ ክስ ቅሬታ ያላቀረበባቸውን 3ኛ እና 4ኛ ፍሬ ነገሮችን በመጨመር፤
* እንዲሁም 3ኛ ክስን በማካተት በ1ኛ እና 2ኛ ክሶች መከላከል ሳያስፈልገው በነፃ እንዲሰናበት፣ 3ኛ ክስን በሚመለከት ክስ የቀረበበት ድንጋጌ ወደ ጥላቻ ንግግር ወይም የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከለከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 በመለወጥ እንዲከላከል በአብላጫ ድምጽ የተሰጠውን ብይን፤
*እንዲሁም የተጠቀሰውን አዋጅ ለጉዳዩ ያለውን አግባብነት መጣራት ያለበት መሆኑን ስለታመነበት መልስ ሰጪ ይቅረብ ብለናል በሚል ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡” የሚል ነው።
ጋዜጠኛ ተመስገን ያነበቡትና ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ይኼው ሰነድ አክሎም፣ “ይህ ትዕዛዝ ዐቃቢ ህግ በይግባኝ አቤቱታው ከጠየቀው ዳኝነት በማለፍ የተሰጠ ትዕዛዝ መሆኑን መረዳት የሚቻል ከመሆኑም በላይ የመልስ ሰጪን መብት በብርቱ የሚጎዳ አድራጎት ነው” ይላል።
በተጨማሪ ፣ “ከላይ ስማቸውን የጠቀስኩት ዳኛ በዚህ ጉዳይ ከችሎት ሳይነሱ ይቀጥሉ ቢባል ጉዳዩ ፓለቲካዊ ይዘት ያለው እንደመሆኑ መጠን በመዝገቡ ላይ ትክክለኛ ፍትህ ይሰጣሉ ብዬ የማላምንና ወደ ፊትም የሚሰጠው ፍርድ ነጻና ገለልተኛ ይሆናል ብዬ ስለማላምን በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 33/1/ሠ መሠረት የግራ ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ መሐመድ አሕመድ በዚህ ጉዳይ ከችሎቱ እንዲነሱልኝ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ” ሲል ያትታል።
በመጨረሻም፣ የጋዜጠኛውን አቤቱታ ካደመጠ በኋላ ችሎቱ፣ የዳኛውን ከችሎት መነሳትና አለመነሳት ጥያቄን በተመለከተ ለመወሰን፣ እንዲሁም ጋዜጠኛ ተመስገን በዋናው ክሳቸው ይሰጣሉ ተብሎ የሚጠበቀውን መለስ ለመቀበል ለጥር 28 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ኢዮብ ትኩዬ ነው።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #ነዳጅ
የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ስጪ በሆኑ ተሽከርካሪዎች ላይ የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ በተደርገ ማሻሻያ ቀደም ሲል ሲሰጥ ከነበረው የድጎማ መጠን ዝቅ አንዲል መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ ማሻሻያ የተደረገው ፦
- በአገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣
- የከተማ አውቶብሶች
- ፐብሊክ ባስ
- ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
በየ6 ወሩ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች የድጎማ መጠን ማስተካከያ የሚደረግ ሲሆን ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም ለሚቀጥሉት 6 ወራት ፦
* ለቤንዚን ተጠቃሚ አገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣የከተማ አውቶብሶች እና ፐብሊክ ባስ ብር 22.36 በሊትር ሲሰጥ የነበረውን ድጎማ ወደ 19.16 በሊትር ዝቅ እንዲል፣
* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲሰጥ የነበረው ብር 23.21 በሊትር ድጎማ በሊትር 19.89 ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡
የታለመ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር የሚሰጠው ድጎማ በየሶስት ወሩ የሚከለስ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በዚህም ፦
* ከጥር 1 ቀን 2016ዓ.ም እስከ መጋቢት 30 ቀን 2016ዓ.ም ድረስ ለቤንዚን ተጠቃሚዎች ሲስጥ የነበረው ብር 12.78 በሊትር ድጎማ ወደ 6.39 በሊትር፣
* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲስጥ የበነረው የብር 13.27 ድጎማ ወደ ብር 6.63 በሊትር ተቀናሽ እንዲሆን የተወሰነ መሆኑ ተገልጿል፡፡
መረጃው የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኤፍ ቢ ሲ ነው።
@tikvahethiopia
የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ስጪ በሆኑ ተሽከርካሪዎች ላይ የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ በተደርገ ማሻሻያ ቀደም ሲል ሲሰጥ ከነበረው የድጎማ መጠን ዝቅ አንዲል መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
የነዳጅ ድጎማ መጠን ላይ ማሻሻያ የተደረገው ፦
- በአገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣
- የከተማ አውቶብሶች
- ፐብሊክ ባስ
- ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ላይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
በየ6 ወሩ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች የድጎማ መጠን ማስተካከያ የሚደረግ ሲሆን ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016ዓ.ም ለሚቀጥሉት 6 ወራት ፦
* ለቤንዚን ተጠቃሚ አገር አቋራጭ አውቶብሶች ፣የከተማ አውቶብሶች እና ፐብሊክ ባስ ብር 22.36 በሊትር ሲሰጥ የነበረውን ድጎማ ወደ 19.16 በሊትር ዝቅ እንዲል፣
* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲሰጥ የነበረው ብር 23.21 በሊትር ድጎማ በሊትር 19.89 ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡
የታለመ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ ሚዲባስ፣ ሚኒባስ፣ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር የሚሰጠው ድጎማ በየሶስት ወሩ የሚከለስ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በዚህም ፦
* ከጥር 1 ቀን 2016ዓ.ም እስከ መጋቢት 30 ቀን 2016ዓ.ም ድረስ ለቤንዚን ተጠቃሚዎች ሲስጥ የነበረው ብር 12.78 በሊትር ድጎማ ወደ 6.39 በሊትር፣
* ለነጭ ናፍጣና ለኬሮሲን ሲስጥ የበነረው የብር 13.27 ድጎማ ወደ ብር 6.63 በሊትር ተቀናሽ እንዲሆን የተወሰነ መሆኑ ተገልጿል፡፡
መረጃው የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኤፍ ቢ ሲ ነው።
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ #ኢትዮጵያ የአየር ክልሏን ከማንኛውም ጥቃት ሊከላከሉ የሚችሉ ዘመናዊ የውጊያ ትጥቆችን እየታጠቀች መሆኑና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አሳውቋል።
የኢትዮጵያ አየር ሀይል ዛሬ እጅግ ዘመናዊ የሆነውን የsu-30 ተዋጊ ጀቶችንና የስትራቴጂክ ሰው አልባ ተዋጊ አውሮፕላኖችን በመረከብ መታጠቁን ገልጿል።
ይህ የመጀመሪያ ዙር ሲሆን ሌሎች በሂደት እንደሚገቡ ተነግሯል።
ዛሬ የአየር ኃይሉ የታጠቃቸው የsu-30 እና የስትራቴጂክ ሰው አልባ አውሮፕሎች እጅግ ዘመናዊ፣ የ5ኛው ትውልድ አካል የሆኑ በሀገር ላይ ሊቃጡ የሚሞከሩ ጥቃቶችን ለማክሸፍ ወሳኝ የሆኑ ናቸው ተብሏል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር ሀይል ዛሬ እጅግ ዘመናዊ የሆነውን የsu-30 ተዋጊ ጀቶችንና የስትራቴጂክ ሰው አልባ ተዋጊ አውሮፕላኖችን በመረከብ መታጠቁን ገልጿል።
ይህ የመጀመሪያ ዙር ሲሆን ሌሎች በሂደት እንደሚገቡ ተነግሯል።
ዛሬ የአየር ኃይሉ የታጠቃቸው የsu-30 እና የስትራቴጂክ ሰው አልባ አውሮፕሎች እጅግ ዘመናዊ፣ የ5ኛው ትውልድ አካል የሆኑ በሀገር ላይ ሊቃጡ የሚሞከሩ ጥቃቶችን ለማክሸፍ ወሳኝ የሆኑ ናቸው ተብሏል።
@tikvahethiopia
ወደ ሚቀርብዎ የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ቅርንጫፎች ጎራ ብለው የቁጠባ ሒሳብ በመክፈት የአገልግሎቶቻችን ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡
በሚቀርብዎ አማራጮች ያግኙን፡ https://bit.ly/3TkrrXD
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!
#GlobalBankEthiopia #OurSharedSuccess #BankInEthiopia #Bank #GBE
በሚቀርብዎ አማራጮች ያግኙን፡ https://bit.ly/3TkrrXD
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!
#GlobalBankEthiopia #OurSharedSuccess #BankInEthiopia #Bank #GBE
#እንድታውቁት
ሱስ ምንድን ነው ?
- ቀጣይነት ያለው፣ ሊመላለስ የሚችል፣ ተጓዳኝ ችግሮች እንዳሉት እየታወቀ እንኳን ከፍትኛ የሆነ ንጥረ-ነገር የመጠቀም ፍላጎት ነው፡፡
- እንደ የአዕምሮ እክል የሚቆጠር ሲሆን፣ አእምሮን የተለመደ ስራውን እንዳይሰራ በእጅጉ ይገድበዋል ፡፡
- መከላከል እንዲሁም መታከም የሚችል ነው፡፡
- ብዙ ጊዜ ከደካማነት የተነሳ ሰዎች
እንደሚያደርጉት እየታሰበ ቢቆይም፤ በአሁን ጊዜ በዚህ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ለመጠቀም ዋነኛ ምክንያታቸው ከአካላዊ እና ከስሜታዊ ህመሞቻቸው ለመሸሽ እንደሆነ እየታመነ ነው፡፡
- ሱስ ከንጥረ-ነገር ጋር የተያያዘ (ሲጋራ፣አልኮል) ወይም ያልተያያዘ (እንደ ቁማር) ሊሆን ይችላል፡፡
አጋላጭ ሁኔታዎች፦
* ከቤተሰብ የሱስ ችግር ከነበረ
* የአቻ ግፊት
* ስነ-ልቦናዊ ችግሮች የመሳሰሉት ናቸው።
- ሱስ እጅግ አደገኛና በአንድም በሌላ መንገድ የብዙ ሰዎችን ህይወት የሚቀጥፍ ነው፡፡
- ከሱስ መላቀቅ ይቻላል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች በራሳቸው ጊዜ ሲያቆሙ በህክምና እርዳታም መቆም ይችላል፡፡
- ይህ ችግር ተመላላሽ ስለሆነ ለማቆም ብዙ ሙከራዎች ያስፈልጉታል፡፡በተለይም የሲጋራ ሱስ ለማቆም ረጅም ጊዜ ሊወስድ ይችላል፡፡
- በአሁን ጊዜ ግን በሰለጠነው ዓለም የተለያዩ ሳይንሳዊ ግኝቶች ይህን ችግር የበለጠ ለመረዳት እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡
(ምሳ. Brain Imaging Technologies)-አዕምሮአችን ለተለያዩ ሁኔታዎች (ለንጥረ-ነገር ጋር የተያያዙ ወይም ያልተያያዙ ሱሶች) ተመሳሳይ ምላሽ እንደሚሰጥ አሳይተዋል፡፡
መፍትሄ ፦
➡ ለማቆም ተነሳሽነትን ማዳበር
➡ አካባቢያችንን፣ ውሎአችንን ማስተካከል
➡ የስነ-ልቦና ምክር
➡ በሽታ መሆኑን በመገንዘብ ወደ ህክምና አልያም ማገገሚያ ቦታዎች መሄድ ያስፈልጋል።
#HarvardHealthPublishing
@tikvahethiopia
ሱስ ምንድን ነው ?
- ቀጣይነት ያለው፣ ሊመላለስ የሚችል፣ ተጓዳኝ ችግሮች እንዳሉት እየታወቀ እንኳን ከፍትኛ የሆነ ንጥረ-ነገር የመጠቀም ፍላጎት ነው፡፡
- እንደ የአዕምሮ እክል የሚቆጠር ሲሆን፣ አእምሮን የተለመደ ስራውን እንዳይሰራ በእጅጉ ይገድበዋል ፡፡
- መከላከል እንዲሁም መታከም የሚችል ነው፡፡
- ብዙ ጊዜ ከደካማነት የተነሳ ሰዎች
እንደሚያደርጉት እየታሰበ ቢቆይም፤ በአሁን ጊዜ በዚህ በሽታ የተጠቁ ሰዎች ለመጠቀም ዋነኛ ምክንያታቸው ከአካላዊ እና ከስሜታዊ ህመሞቻቸው ለመሸሽ እንደሆነ እየታመነ ነው፡፡
- ሱስ ከንጥረ-ነገር ጋር የተያያዘ (ሲጋራ፣አልኮል) ወይም ያልተያያዘ (እንደ ቁማር) ሊሆን ይችላል፡፡
አጋላጭ ሁኔታዎች፦
* ከቤተሰብ የሱስ ችግር ከነበረ
* የአቻ ግፊት
* ስነ-ልቦናዊ ችግሮች የመሳሰሉት ናቸው።
- ሱስ እጅግ አደገኛና በአንድም በሌላ መንገድ የብዙ ሰዎችን ህይወት የሚቀጥፍ ነው፡፡
- ከሱስ መላቀቅ ይቻላል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች በራሳቸው ጊዜ ሲያቆሙ በህክምና እርዳታም መቆም ይችላል፡፡
- ይህ ችግር ተመላላሽ ስለሆነ ለማቆም ብዙ ሙከራዎች ያስፈልጉታል፡፡በተለይም የሲጋራ ሱስ ለማቆም ረጅም ጊዜ ሊወስድ ይችላል፡፡
- በአሁን ጊዜ ግን በሰለጠነው ዓለም የተለያዩ ሳይንሳዊ ግኝቶች ይህን ችግር የበለጠ ለመረዳት እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡
(ምሳ. Brain Imaging Technologies)-አዕምሮአችን ለተለያዩ ሁኔታዎች (ለንጥረ-ነገር ጋር የተያያዙ ወይም ያልተያያዙ ሱሶች) ተመሳሳይ ምላሽ እንደሚሰጥ አሳይተዋል፡፡
መፍትሄ ፦
➡ ለማቆም ተነሳሽነትን ማዳበር
➡ አካባቢያችንን፣ ውሎአችንን ማስተካከል
➡ የስነ-ልቦና ምክር
➡ በሽታ መሆኑን በመገንዘብ ወደ ህክምና አልያም ማገገሚያ ቦታዎች መሄድ ያስፈልጋል።
#HarvardHealthPublishing
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
የግብረ-ስጋ ግንኙነት እንዲፈፅሙ ጠይቋት ፈቃደኛ ባለመሆኗ ሟችን በቢላዋ ወግቶ የገደለው ተከሳሽ በ23 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።
ዳንኤል በርሄ ስዩም የተባለ ተከሳሽ ሀምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ በግምት 3፡30 ሲሆን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ሳሪስ አደይ አበባ መኪና መሻገሪያ ድልድይ አካባቢ በሚገኘው ፍሬሕይወት ህንፃ ውስጥ ሟችን የሽንት ቤት ቁልፍ ክፈችልኝ ብሏት ስትከፍትለት የግብረ-ስጋ ግንኙነት እንዲፈፅሙ ጠይቋት ፈቃደኛ ባለመሆንዋ አንገትዋን በቢላ በመውጋት ሕይወትዋ እንዲያልፍ አድርጓል፡፡
በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶ በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት በወ/ሕ/አ 539/1/ሀ መሰረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡
በክርክሩ ሂደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ተሰጥቶ ተከሳሽ የመከላከያ ምስክሮች በማስረጃነት አቅርቦ ያሰማ ቢሆንም በዐቃቤ ሕግ የቀረበበትን ክስ መከላከል ባለመቻሉ ምክንያት ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት ተከሳሽ በ23 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ወስኗል፡፡
#MinistryofJustice
@tikvahethiopia
የግብረ-ስጋ ግንኙነት እንዲፈፅሙ ጠይቋት ፈቃደኛ ባለመሆኗ ሟችን በቢላዋ ወግቶ የገደለው ተከሳሽ በ23 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።
ዳንኤል በርሄ ስዩም የተባለ ተከሳሽ ሀምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ በግምት 3፡30 ሲሆን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ሳሪስ አደይ አበባ መኪና መሻገሪያ ድልድይ አካባቢ በሚገኘው ፍሬሕይወት ህንፃ ውስጥ ሟችን የሽንት ቤት ቁልፍ ክፈችልኝ ብሏት ስትከፍትለት የግብረ-ስጋ ግንኙነት እንዲፈፅሙ ጠይቋት ፈቃደኛ ባለመሆንዋ አንገትዋን በቢላ በመውጋት ሕይወትዋ እንዲያልፍ አድርጓል፡፡
በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶ በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት በወ/ሕ/አ 539/1/ሀ መሰረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡
በክርክሩ ሂደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ተሰጥቶ ተከሳሽ የመከላከያ ምስክሮች በማስረጃነት አቅርቦ ያሰማ ቢሆንም በዐቃቤ ሕግ የቀረበበትን ክስ መከላከል ባለመቻሉ ምክንያት ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት ተከሳሽ በ23 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል ወስኗል፡፡
#MinistryofJustice
@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ
1. አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእቃ ጭነት አገልግሎት (ካርጎ) በኩል ለተለያዩ ግለሰቦች ዕቃ እንደተላከላቸው አስመስሎ በመደወል እና ሐሰተኛ የእቃ ጭነት መለያ ቁጥር Air Waybill (AWB) በመጠቀም የተላከውን ዕቃ ለመቀበል የሚከፈል በሚል ክፍያ በመጠየቅ የማጭበርበርና የማታለል ስራ እየሰሩ ስለሆነ ጥንቃቄ ይደረግ።
2. አጭበርባሪዎች #ስራ_ፈላጊዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመቀጠር ለምዝገባ እና ለተለያዩ ወጪዎች በሚል ገንዘብ በማስከፈል የማታለል ተግባር ላይ በመሰማራታቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።
3. የካናዳ መንግስት የስራ እና የትምህርት እድል እንዳወጣ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ሰው እንደወከለ እንዲሁም መመዝገብ ለሚፈልጉም ሁሉ ክፍያ የሚፈፅሙበት የባንክ አካውንትም አንዳሳወቀ በማስመሰል ደብዳቤ በማዘጋጀት ሰዎችን የማታለል ተግባር ላይ አጭበርባሪዎች በመሰማራታቸው ተገቢው ጥንቃቄ ይደረግ።
እንድታውቁት ፦
➡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዕቃ ለተላከላቸው ደንበኞቹ ዕቃቸው መድረሱን እና ወደ ድርጅቱ በመምጣት አስፈላጊ ሂደቶችን እንዲያስጀምሩ ከማሳወቅ ውጪ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዲከፍሉ በስልክ አይጠይቅም።
➡ ለስራ ቅጥር በሚል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ አይጠይቅም ፤ ከማንኛውም አይነት ኤጀንት ጋር አብሮ አይሰራም ፤ ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ የትኛውም ሀገር ሰዎችን የመላክ ስራ ላይ አልተሰማራም።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
@tikvahethiopia
1. አጭበርባሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ የእቃ ጭነት አገልግሎት (ካርጎ) በኩል ለተለያዩ ግለሰቦች ዕቃ እንደተላከላቸው አስመስሎ በመደወል እና ሐሰተኛ የእቃ ጭነት መለያ ቁጥር Air Waybill (AWB) በመጠቀም የተላከውን ዕቃ ለመቀበል የሚከፈል በሚል ክፍያ በመጠየቅ የማጭበርበርና የማታለል ስራ እየሰሩ ስለሆነ ጥንቃቄ ይደረግ።
2. አጭበርባሪዎች #ስራ_ፈላጊዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመቀጠር ለምዝገባ እና ለተለያዩ ወጪዎች በሚል ገንዘብ በማስከፈል የማታለል ተግባር ላይ በመሰማራታቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።
3. የካናዳ መንግስት የስራ እና የትምህርት እድል እንዳወጣ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ሰው እንደወከለ እንዲሁም መመዝገብ ለሚፈልጉም ሁሉ ክፍያ የሚፈፅሙበት የባንክ አካውንትም አንዳሳወቀ በማስመሰል ደብዳቤ በማዘጋጀት ሰዎችን የማታለል ተግባር ላይ አጭበርባሪዎች በመሰማራታቸው ተገቢው ጥንቃቄ ይደረግ።
እንድታውቁት ፦
➡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዕቃ ለተላከላቸው ደንበኞቹ ዕቃቸው መድረሱን እና ወደ ድርጅቱ በመምጣት አስፈላጊ ሂደቶችን እንዲያስጀምሩ ከማሳወቅ ውጪ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዲከፍሉ በስልክ አይጠይቅም።
➡ ለስራ ቅጥር በሚል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ አይጠይቅም ፤ ከማንኛውም አይነት ኤጀንት ጋር አብሮ አይሰራም ፤ ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ የትኛውም ሀገር ሰዎችን የመላክ ስራ ላይ አልተሰማራም።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
@tikvahethiopia