TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#Update

ጠቅላይ ምክር ቤቱ #በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አስቸኳይ ጉባዔ ተቀምጧል። 

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባዔ እየተካሄደ ነው።

አስቸኳይ ጉባዔው በዑማ ሆቴል እየተካሄደ  ሲሆን መርሀ ግብሩን በቁርዓን የታላቁ አንዋር መስጂድ ኢማምና ኻጢብ በሆኑት በሼይኽ  ጧሐ ሙሀመድ ሐሩን መከፈቱ ተገልጿል።

የጠቅላላ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ይህንን ጉባዔ ስናካሂድ በሸገር ከተማ በርካታ መስጂዶች  የፈረሱበት የመስጂዶችን ፈረሳ ለመቃወም ከወጡ ሰዎች ዉስጥ መስዋት የሆነበት ጊዜ ነው ብለዋል።

" መስጂዶች የአሏህ ቤቶች ናቸው። ይህ ክስተንን ከሚመለከተው  አካል ጋር ለመመካከር የተደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል " ብለዋል።

" ሙስሊሞች  የሀገር የሰላም ዘብ ናቸው " ያሉት ፕሬዝዳንቱ " በሸገር ከተማ እየፈረሱ ያሉትን መስጂዶች ጉዳይ በሚመለከት  ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ጥያቄ መቅረቡን አስታውሰዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ ነገሮችን ወዳልተፈለገ መልኩ በሚወስዱ ማህበራዊ ድረ ገፅ ላይ የሚፅፉ  አንዳንድ  አካላትን ከተግባራቸው  እንዲቆጠቡ  አሳስበዋል።

" በመንግስት ዉስጥ ሆነዉ መንግስትና ሕዝብን የሚያጋጩ አካላት በሕገ ተጠያቂ መሆንን ይኖርባቸዋል "ም ብለዋል።

በትላንትናው  ዕለት  በሸገር ከተማ በ " ሕገ ወጥ " ስም የፈረሱ መስጂዶችን  ለመቃወም ወጥተው መስዋዕት የሆኑ  ወንድሞች አሏህ ጀነተል ፍርዶስ እንዲወፍቃቸው ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጆቻቸው መፅናናት እንዲሰጣቸው ጉዳት የደረሰባው ወገኖቻችን ከደረሰባቸው ጉዳት አፊያቸውን እንዲመልስላቸው ፕሬዜዳንቱ ምኞታቸውን ገልፀዋል።

በጉባዔው የኦሮሚያና የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤቶች ሪፖርታቸውን ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia