#AddisAbaba
" የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተን ለማደር ተቸግረናል " - ነዋሪዎች
በአዲስ አበባ ከተማ ከጤፍ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተው ለማደር መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ።
ለሪፖርተር ጋዜጣ ቃላቸውን የሰጡ የከተማው ነዋሪዎች ፤ ሰሞኑን የአንድ እንጀራ ዋጋ ቀደም ሲል ከነበረበት 17 ብር ወደ 22 እና 24 ብር ከፍ በማለቱ፣ ገዝተው ለመጠቀም ተቸግረዋል፡፡
እንጀራን ጋግረው ለመጠቀም ባለመቻላቸው ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን የተናገሩት እንዲት ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ እናት፣ የሚከፈላቸው የ3,000 ብር ደመወዝ ከወር ስለማያደርሳቸው በብድር እንደሚጠቀሙ ገልጸዋል፡፡
እንጀራን ጨምሮ ሌሎች ሸቀጦች ላይ እየታየ ያለው የዋጋ ጭማሪም እንዳማረራቸውም እኚሁ እናት አክለዋል።
በተመሳሳይ መልኩ የእንጀራ ዋጋ በአንድ ጊዜ ከአምስት እስከ ሰባት ብር መጨመሩን የተናገረው ወጣት ሻምበል ቢሆነኝ፣ ወጣቱ እንዳለው ከሆነ እንጀራን በቤት እንኳን ለማስጋገር አከራዮች " መብራት ይቆጥርብናል " በማለት ፈቃደኛ ስለማይሆኑ እየገዛ ለመብላት መገደዱን ተናግሯል፡፡
በዚህም ሰሞኑን በእንጀራ ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ከሚከፈለው የወር ደመወዝ ጋር ፈፅሞ የማይመጣጠን ነው ሲል አብራርቷል።
እንጀራ ሻጮችን ዋጋ ለምን እንደጨመሩ ሲጠይቃቸው፣ " ጤፍ ጨምሯል ስለተባልን ነው " እንደሚሉት ገልጿል።
ጋዜጣው በአንዳንድ የእንጀራ መሸጫ ሱቆች ተዘዋውሬ ተመልክቻለው ባለው የእንጀራ ዋጋ ከ14 ብር ጀምሮ 17፣ 22 እና 24 ብር እየተሸጠ ነው።
የእንጀራ መሸጫ ዋጋ በዚህን ያህል የዋጋ ልዩነት ለምን እንዳሳየ ነጋዴዎች ሲጠየቁ የእንጀራው መወፈርና መሳሳት፣ እንዲሁም በጤፉ ላይ የሚቀላቀለው እህል መብዛት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ስለዋጋው ጭማሪ ደግሞ የጤፍ ዋጋ ከመጨመሩ ጋር ተያይዞ እንደሆነም ጠቁመዋል። ተደረገ የተባለው የዋጋ ጭማሪ በመርካቶ እህል በረንዳ ባሉ መጋዘኖችም እንደታየ ተመላክቷል።
ብዙ የጤፍ አቅርቦት እንደሌለና የሚመጣው ጤፍ ደግሞ ዋጋው እየጨመረ መሆኑን አንዳንድ ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ ነጋዴዎች ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ፤ በተለይ በቢሾፍቱና በዱከም አካባቢ ወደ አዲስ አበባ የሚገባውን ጤፍ፣ በአካባቢው ያሉ ሆቴሎች አርሶ አደሮችም ሆኑ ነጋዴዎች አዲስ አበባ አምጥተው ከሚሸጡበት ዋጋ በላይ ስለሚገዟቸው በአቅርቦቱ ላይ ጫና ማሳደሩን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ ግጭት ከጎጃምና አካባቢው ወደ መዲናዋ የሚገባው ጤፍ መቅረቱ ደግሞ አሁን ለታየው የዋጋ ጭማሪ ሌላው መንስዔ መሆኑን ነጋዴዎቹ አብራርተዋል።
ሰኞ ነሐሴ 15 ቀን 2015 ዓ.ም፣ በእህል በረንዳ በነበረው ወቅታዊ ግብይት ፦
- ማኛ ነጭ ጤፍ 13,500 ብር እየተሸጠ ሲሆን፣
- ሠርገኛ ጤፍ ከ10,000 ብር እስከ 10,700 ብር፣
- ቀይ ጤፍ ከ9,500 ብር እስከ 10,000 ሺሕ ብር ሲሸጥ መቆየቱን ለመመልከት ተችሏል።
ሌሎች ነጋዴዎች እንዳሉት ከሆነ ደግሞ በጎጃም በኩል የሚገባው ጤፍ መቅረቱ የተወሰነ እጥረትን ቢያስከትልም፣ ከአርባ ምንጭና ከባሌ፣ እንዲሁም ከሌሎች አካባቢዎች የሚገባው ጤፍ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረው፣ አከፋፋዮችም የቻሉትን ያህል እየጫኑና እየወዱ ነው። በዚህም የምርት እጥረት አለ የሚባለውን እንደማያምኑበት ነው የተናገሩት።
ያንብቡ - https://telegra.ph/Reporter-08-23-3
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
" የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተን ለማደር ተቸግረናል " - ነዋሪዎች
በአዲስ አበባ ከተማ ከጤፍ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተው ለማደር መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ።
ለሪፖርተር ጋዜጣ ቃላቸውን የሰጡ የከተማው ነዋሪዎች ፤ ሰሞኑን የአንድ እንጀራ ዋጋ ቀደም ሲል ከነበረበት 17 ብር ወደ 22 እና 24 ብር ከፍ በማለቱ፣ ገዝተው ለመጠቀም ተቸግረዋል፡፡
እንጀራን ጋግረው ለመጠቀም ባለመቻላቸው ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን የተናገሩት እንዲት ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ እናት፣ የሚከፈላቸው የ3,000 ብር ደመወዝ ከወር ስለማያደርሳቸው በብድር እንደሚጠቀሙ ገልጸዋል፡፡
እንጀራን ጨምሮ ሌሎች ሸቀጦች ላይ እየታየ ያለው የዋጋ ጭማሪም እንዳማረራቸውም እኚሁ እናት አክለዋል።
በተመሳሳይ መልኩ የእንጀራ ዋጋ በአንድ ጊዜ ከአምስት እስከ ሰባት ብር መጨመሩን የተናገረው ወጣት ሻምበል ቢሆነኝ፣ ወጣቱ እንዳለው ከሆነ እንጀራን በቤት እንኳን ለማስጋገር አከራዮች " መብራት ይቆጥርብናል " በማለት ፈቃደኛ ስለማይሆኑ እየገዛ ለመብላት መገደዱን ተናግሯል፡፡
በዚህም ሰሞኑን በእንጀራ ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ከሚከፈለው የወር ደመወዝ ጋር ፈፅሞ የማይመጣጠን ነው ሲል አብራርቷል።
እንጀራ ሻጮችን ዋጋ ለምን እንደጨመሩ ሲጠይቃቸው፣ " ጤፍ ጨምሯል ስለተባልን ነው " እንደሚሉት ገልጿል።
ጋዜጣው በአንዳንድ የእንጀራ መሸጫ ሱቆች ተዘዋውሬ ተመልክቻለው ባለው የእንጀራ ዋጋ ከ14 ብር ጀምሮ 17፣ 22 እና 24 ብር እየተሸጠ ነው።
የእንጀራ መሸጫ ዋጋ በዚህን ያህል የዋጋ ልዩነት ለምን እንዳሳየ ነጋዴዎች ሲጠየቁ የእንጀራው መወፈርና መሳሳት፣ እንዲሁም በጤፉ ላይ የሚቀላቀለው እህል መብዛት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ስለዋጋው ጭማሪ ደግሞ የጤፍ ዋጋ ከመጨመሩ ጋር ተያይዞ እንደሆነም ጠቁመዋል። ተደረገ የተባለው የዋጋ ጭማሪ በመርካቶ እህል በረንዳ ባሉ መጋዘኖችም እንደታየ ተመላክቷል።
ብዙ የጤፍ አቅርቦት እንደሌለና የሚመጣው ጤፍ ደግሞ ዋጋው እየጨመረ መሆኑን አንዳንድ ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ ነጋዴዎች ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ፤ በተለይ በቢሾፍቱና በዱከም አካባቢ ወደ አዲስ አበባ የሚገባውን ጤፍ፣ በአካባቢው ያሉ ሆቴሎች አርሶ አደሮችም ሆኑ ነጋዴዎች አዲስ አበባ አምጥተው ከሚሸጡበት ዋጋ በላይ ስለሚገዟቸው በአቅርቦቱ ላይ ጫና ማሳደሩን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ ግጭት ከጎጃምና አካባቢው ወደ መዲናዋ የሚገባው ጤፍ መቅረቱ ደግሞ አሁን ለታየው የዋጋ ጭማሪ ሌላው መንስዔ መሆኑን ነጋዴዎቹ አብራርተዋል።
ሰኞ ነሐሴ 15 ቀን 2015 ዓ.ም፣ በእህል በረንዳ በነበረው ወቅታዊ ግብይት ፦
- ማኛ ነጭ ጤፍ 13,500 ብር እየተሸጠ ሲሆን፣
- ሠርገኛ ጤፍ ከ10,000 ብር እስከ 10,700 ብር፣
- ቀይ ጤፍ ከ9,500 ብር እስከ 10,000 ሺሕ ብር ሲሸጥ መቆየቱን ለመመልከት ተችሏል።
ሌሎች ነጋዴዎች እንዳሉት ከሆነ ደግሞ በጎጃም በኩል የሚገባው ጤፍ መቅረቱ የተወሰነ እጥረትን ቢያስከትልም፣ ከአርባ ምንጭና ከባሌ፣ እንዲሁም ከሌሎች አካባቢዎች የሚገባው ጤፍ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረው፣ አከፋፋዮችም የቻሉትን ያህል እየጫኑና እየወዱ ነው። በዚህም የምርት እጥረት አለ የሚባለውን እንደማያምኑበት ነው የተናገሩት።
ያንብቡ - https://telegra.ph/Reporter-08-23-3
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
#የዋጋ_ንረት📈
መስከረም 2015 መጀመርያ ላይ ከ6 ሺሕ ብር በታች ይሸጥ የነበረ አንድ ኩንታል ነጭ ጤፍ ለመጀመርያ ጊዜ ከ10 ሺሕ ብር በላይ ዋጋ ያወጣው ሊጠናቀቅ ሰዓታት በቀሩትና አሮጌ ብለን ልንሸኘው በተዘጋጀው 2015 ዓ.ም. ነው፡፡ የጤፍ ዋጋ ነሐሴ 2015 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ እስከ 15 ሺሕ ብር ሲደርስ ይኸው የዋጋ ጭማሪ 1 ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከዕጥፍ በላይ እንደደረሰ ያመለክታል።
#የስንዴ_ገበያም በተመሳሳይ ከፍተኛ የሆነ ዋጋ የተመዘገበበት ዓመት ይኼው 2015 ዓ.ም. ነው፡፡
በአጠቃላይ ከጤፍና ስንዴ በተጨማሪ በሌሊችም ምግብ ነክ እና ምግብ ነክ ባለሆኑ ሸቀጦች ላይ በዚህ ልንሸኘው ጥቂት ሰዓታት በቀረን 2015 ከፍተኛ የሆነ ዋጋ ተመዝግቧል።
የኢኮኖሚው ባለሙያ አቶ አወት ተክኤ ምን ይላሉ ?
" በሀገሪቱ ከፀጥታና አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች የዋጋ ንረትን በማባባስ ዓይነተኛ ሚና ነበራቸው። አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች እንዳይስፋፉ ጭምር አድርገዋል።
በ2015 ዓ/ም በጀት ዓመት ለዋጋ ንረቱ መባባስ በተደጋጋሚ ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ባሻገር፣ መንግሥት የወሰዳቸው የፖሊሲ ዕርምጃዎች ለዋጋ ንረቱ አስተዋጽኦ ነበራቸው።
ለአብነት የኢኮኖሚ የነዳጅ ጭማሪ እና ሌሎች የመንግሥት የፖሊሲ ውሳኔዎች ለዋጋ ንረቱ የራሳቸው አስተዋጽኦ አድርገዋል።
ይህ የዋጋ ንረት በቀጣይ ዓመትም እንዳይተላለፍ ለችግሩ መንስዔ የነበሩት፣ ለምሳሌ የፀጥታና ያለ መረጋጋቶች መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡
በቅርቡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ውሳኔዎችን በአግባቡ መተግበር ለዋጋ ንረት መርገብ መፍትሔ ሊሆኑ ይገባል፡፡ "
ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Ethiopianreporter-09-11
#ሪፖርተር_ጋዜጣ
@tikvahethiopia
መስከረም 2015 መጀመርያ ላይ ከ6 ሺሕ ብር በታች ይሸጥ የነበረ አንድ ኩንታል ነጭ ጤፍ ለመጀመርያ ጊዜ ከ10 ሺሕ ብር በላይ ዋጋ ያወጣው ሊጠናቀቅ ሰዓታት በቀሩትና አሮጌ ብለን ልንሸኘው በተዘጋጀው 2015 ዓ.ም. ነው፡፡ የጤፍ ዋጋ ነሐሴ 2015 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ እስከ 15 ሺሕ ብር ሲደርስ ይኸው የዋጋ ጭማሪ 1 ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከዕጥፍ በላይ እንደደረሰ ያመለክታል።
#የስንዴ_ገበያም በተመሳሳይ ከፍተኛ የሆነ ዋጋ የተመዘገበበት ዓመት ይኼው 2015 ዓ.ም. ነው፡፡
በአጠቃላይ ከጤፍና ስንዴ በተጨማሪ በሌሊችም ምግብ ነክ እና ምግብ ነክ ባለሆኑ ሸቀጦች ላይ በዚህ ልንሸኘው ጥቂት ሰዓታት በቀረን 2015 ከፍተኛ የሆነ ዋጋ ተመዝግቧል።
የኢኮኖሚው ባለሙያ አቶ አወት ተክኤ ምን ይላሉ ?
" በሀገሪቱ ከፀጥታና አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች የዋጋ ንረትን በማባባስ ዓይነተኛ ሚና ነበራቸው። አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች እንዳይስፋፉ ጭምር አድርገዋል።
በ2015 ዓ/ም በጀት ዓመት ለዋጋ ንረቱ መባባስ በተደጋጋሚ ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ባሻገር፣ መንግሥት የወሰዳቸው የፖሊሲ ዕርምጃዎች ለዋጋ ንረቱ አስተዋጽኦ ነበራቸው።
ለአብነት የኢኮኖሚ የነዳጅ ጭማሪ እና ሌሎች የመንግሥት የፖሊሲ ውሳኔዎች ለዋጋ ንረቱ የራሳቸው አስተዋጽኦ አድርገዋል።
ይህ የዋጋ ንረት በቀጣይ ዓመትም እንዳይተላለፍ ለችግሩ መንስዔ የነበሩት፣ ለምሳሌ የፀጥታና ያለ መረጋጋቶች መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡
በቅርቡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ውሳኔዎችን በአግባቡ መተግበር ለዋጋ ንረት መርገብ መፍትሔ ሊሆኑ ይገባል፡፡ "
ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Ethiopianreporter-09-11
#ሪፖርተር_ጋዜጣ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ለግብፅ መግለጫ ምን ምላሽ ተሰጠ ?
" ግብፆቹ ስለ4ኛው ሙሌት በደንብ ያውቃሉ ፤ ምንም የተጣሰ መርህ የለም " - ኢ/ር ጌዲዮን አስፋው
ከሰሞኑን ኢትዮጵያ 4ኛውን ዙር የአባይ ግድብ የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ ካሳወቀች በኃላ ግብፅ ሙሌቱ ህገወጥ እንደሆነና እ.ኤ.አ. በ2015 በሱዳን፣ በግብፅና በኢትዮጵያ የተፈረመውን የመርህ ስምምነት የጣሰ ነው በሚል ቁጣ አዘል መግለጫ አውጥታ ነበር።
ለዚህ ግብፅ መግለጫ ምላሽ የሰጡት የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎችና ባለስልጣናት " ምንም የተጣሰ ነገር የለም ፤ መግለጫዋ ለሀገር ውስጥ የሚዲያ ፍጆታ የሚውል ነው " ብለውታል።
የኢትዮጵያ የግድቡ ተደራዳሪ ኢንጂነር ጌዲዮን አስፋው ምን አሉ ?
" ምንም የተጣሰ ነገር የለም፡፡ ግብፆች ያወጡት ነገር ትክክል አይደለም፡፡ የመርህ ስምምነቱ አልተጣሰም፡፡
በመርህ ስምምነቱ መሠረት የወጣ የሙሌት ሠንጠረዥ አለ፣ በእሱ መሠረት ነው አሁን የሞላነው፡፡
አሁን በቅርቡ የተጀመረው ድርድር የአገሮቹ መሪዎች በሰጡት መመርያ መሠረት የተጀመረና የተካሄደ ነው።
የሦስትዮሽ ድርድር ከአንድ ዓመት በላይ ተቋርጦ የነበረው ከቆመበት መቀጠል እንጂ፣ አዲስ ድርድር አይደለም።
አራተኛው ሙሌት በቅርቡ ከተጀመረው ድርድር ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡
ግብፆቹ ስለአራተኛው ሙሌት በደንብ ያውቃሉ፡፡ በተስማማነው መሠረት ነው የተሞላው። "
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ምን አሉ ?
" ሙሌቱ በሌሎች የተፋሰሱ አገሮች ላይ ትርጉም ያለው ተፅዕኖ የለውም።
የእነሱ የሚዲያ እንካ ሰላንቲያ የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የቀጠለ ነው፡፡
አሁን ያወጡት መግለጫም የተለመደ የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ፍጆታ ነው፣ ለውስጥ ፍጆታ የሚጠቀሙበት ነው፡፡
እኛ የእነሱ የሚዲያ እንካ ሰላንቲያ ውስጥ መግባት አንፈልግም፡፡
ይኼ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያከብረው ፕሮጀክት ነው፡፡ ግድቡ የትብብር እንጂ የፉክክር ምንጭ መሆን የለበትም። "
Credit - #ሪፖርተር
@tikvahethiopia
" ግብፆቹ ስለ4ኛው ሙሌት በደንብ ያውቃሉ ፤ ምንም የተጣሰ መርህ የለም " - ኢ/ር ጌዲዮን አስፋው
ከሰሞኑን ኢትዮጵያ 4ኛውን ዙር የአባይ ግድብ የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ ካሳወቀች በኃላ ግብፅ ሙሌቱ ህገወጥ እንደሆነና እ.ኤ.አ. በ2015 በሱዳን፣ በግብፅና በኢትዮጵያ የተፈረመውን የመርህ ስምምነት የጣሰ ነው በሚል ቁጣ አዘል መግለጫ አውጥታ ነበር።
ለዚህ ግብፅ መግለጫ ምላሽ የሰጡት የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎችና ባለስልጣናት " ምንም የተጣሰ ነገር የለም ፤ መግለጫዋ ለሀገር ውስጥ የሚዲያ ፍጆታ የሚውል ነው " ብለውታል።
የኢትዮጵያ የግድቡ ተደራዳሪ ኢንጂነር ጌዲዮን አስፋው ምን አሉ ?
" ምንም የተጣሰ ነገር የለም፡፡ ግብፆች ያወጡት ነገር ትክክል አይደለም፡፡ የመርህ ስምምነቱ አልተጣሰም፡፡
በመርህ ስምምነቱ መሠረት የወጣ የሙሌት ሠንጠረዥ አለ፣ በእሱ መሠረት ነው አሁን የሞላነው፡፡
አሁን በቅርቡ የተጀመረው ድርድር የአገሮቹ መሪዎች በሰጡት መመርያ መሠረት የተጀመረና የተካሄደ ነው።
የሦስትዮሽ ድርድር ከአንድ ዓመት በላይ ተቋርጦ የነበረው ከቆመበት መቀጠል እንጂ፣ አዲስ ድርድር አይደለም።
አራተኛው ሙሌት በቅርቡ ከተጀመረው ድርድር ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡
ግብፆቹ ስለአራተኛው ሙሌት በደንብ ያውቃሉ፡፡ በተስማማነው መሠረት ነው የተሞላው። "
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ምን አሉ ?
" ሙሌቱ በሌሎች የተፋሰሱ አገሮች ላይ ትርጉም ያለው ተፅዕኖ የለውም።
የእነሱ የሚዲያ እንካ ሰላንቲያ የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የቀጠለ ነው፡፡
አሁን ያወጡት መግለጫም የተለመደ የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ፍጆታ ነው፣ ለውስጥ ፍጆታ የሚጠቀሙበት ነው፡፡
እኛ የእነሱ የሚዲያ እንካ ሰላንቲያ ውስጥ መግባት አንፈልግም፡፡
ይኼ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያከብረው ፕሮጀክት ነው፡፡ ግድቡ የትብብር እንጂ የፉክክር ምንጭ መሆን የለበትም። "
Credit - #ሪፖርተር
@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች አስጠልላቸው የሚገኙ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ስደተኞች የዕርዳታ እህል በመቋረጡ፣ ሕይወታቸው አደጋ ላይ መሆኑንና ለአገርም የደኅንነት ሥጋት መደቀኑ ተነገረ፡፡
ከጥቂት ወራት በፊት የዓለም የምግብ ፕሮግራምና የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) በኢትዮጵያ ተፈጸመ ባሉት የዕርዳታ እህል ዝርፊያ ምክንያት ለኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ዕርዳታ ማቆማቸው ይታወሳል፡፡
የምግብ አቅርቦቱ እንደገና እንዲጀመር የኢትዮጵያ መንግሥት እየተነጋገርኩበት ነው ቢልም፣ ዕርዳታው እየቀረበ ባለመሆኑ በኢትዮጵያ የተጠለሉ የውጭ አገሮች ስደተኞች በምግብ ዕጦት እየሞቱና ሕመም ላይ መውደቃቸውን፣ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ምን አለ ?
- ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ ስታስተናግድ የዓለም አቀፉን ሕግ መሠረት በማድረግ ከለላና ጥበቃ የምታደርግ ቢሆንም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለስደተኞች የሚቀርበው ዕርዳታ በመቆሙ ቀውስ ተፈጥሯል።
- በምግብ እጥረት ምክንያት የሚሞቱትና የሚታመሙት ወይም የሚቸገሩት ስደተኞች ብቻ ሳይሆኑ፣ ችግር ሲፈጠር በመሠረታዊነት የመጀመርያ ተጎጂ ሕፃናትና ሴቶች ናቸው።
- በመጠለያ ካምፕ የሚገኝን ሀብት አፈላልጎ ለመመገብ ጥረት በሚያደርግበት ወቅት፣ ስደተኞቹ ከአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር ግጭት ውስጥ ይገቡና ሰላማዊ የኑሮ ሁኔታን የሚያናጋ ነገር እየተፈጠረ ነው።
- በአሁኑ ወቅት ምግብ ነክ ድጋፎች እየቀረቡ ባለመሆናቸእ በቀጣይ አፋጣኝ ዕርምጃ ካልተወሰደ ችግሩ የከፋ ሊሆን ይቻላል። በሁሉም የአገሪቱ መጠለያ ካምፖች ችግሩ ተከቷል።
- በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞችን ለመታደግ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ንግግር እየተደረገ ነው ፤ በአጭር ጊዜ ዕርዳታው እንደገና ይጀመራል የሚል እምነት አለ።
በስደተኛ ቁጥር ፦
👉 በጋምቤላ ወደ 400,000
👉 በቦሎ መልካዲዳ በሶማሌ ክልል 200,000፣
👉 በቤኒሻንጉል አሶሳ ወደ 90,000፣
👉 በአፋር 68,000፣
👉 በሶማሌ ጅግጅጋ ወደ 50,000፣
👉 አማራ ክልል ባባት 25,000፣ መተማ ወደ 40,000፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ወደ 80,000 ስደኞች ይገኛሉ።
ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ስደተኞች መካከል ከ900,000 በላይ የሚሆኑት በመጠለያ ካምፕ ውስጥ ናቸው።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ፣ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ዕርዳታ ለተረጂዎች እየቀረበ ባለመሆኑ ወደ 400,000 የሚጠጉ በጋምቤላ ክልል ውስጥ በካምፕ የሚገኙ ስደተኞች ሕይወት አደጋ ውስጥ መውደቁን ገልጾ አፋጣኝ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡
በጋምቤላ ክልል ከግንቦት 2015 ዓ.ም. ወር ጀምሮ ዕርዳታ ያላገኙ ስደተኞች (አብዛኞቹ ከደ/ሱዳን የተሰደዱ) በምግብ እጥረት የተነሳ በሚመጣ ረሃብ ለሞትና ለከፋ ሕመም እየተጋለጡ መሆናቸውን አረጋግጧል።
ኮሚሽኑ ከስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ተቋም አገኘሁት ባለው መረጃ በምግብ እጥረት ምክንያት በጋምቤላ ብቻ 30 ሰዎች መሞታቸውን፣ 5 ዓመት ያልሞላቸው ሕፃናት ለከፋ ሕመም መጋለጣቸውን አስታውቋል፡፡
በተከሰተው የምግብ እጥረት የተነሳ ከስደተኞች መጠለያ ካምፕ ወጥተው ወደ ማኅበረሰቡ በሚገቡበት ወቅት ለሰላም ችግር መንስዔ መሆናቸው በኮሚሽኑ ሪፖርት የተገለጸ ሲሆን፣ ከመጠለያ ወጥተው በምግብ ስርቆት በመሰማራታቸውና ከቆሻሻ ላይ ምግብ ለማንሳት ሲጥሩ ሕይወታቸው ያለፉ መኖራቸውንም አስታውቋል፡፡
አሁን ላይ በርካታ ስደተኞች አደጋ ላይ በመሆናቸው የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም ሆኑ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡ ኢሰመኮ አሳስቧል።
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች አስጠልላቸው የሚገኙ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ስደተኞች የዕርዳታ እህል በመቋረጡ፣ ሕይወታቸው አደጋ ላይ መሆኑንና ለአገርም የደኅንነት ሥጋት መደቀኑ ተነገረ፡፡
ከጥቂት ወራት በፊት የዓለም የምግብ ፕሮግራምና የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) በኢትዮጵያ ተፈጸመ ባሉት የዕርዳታ እህል ዝርፊያ ምክንያት ለኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ዕርዳታ ማቆማቸው ይታወሳል፡፡
የምግብ አቅርቦቱ እንደገና እንዲጀመር የኢትዮጵያ መንግሥት እየተነጋገርኩበት ነው ቢልም፣ ዕርዳታው እየቀረበ ባለመሆኑ በኢትዮጵያ የተጠለሉ የውጭ አገሮች ስደተኞች በምግብ ዕጦት እየሞቱና ሕመም ላይ መውደቃቸውን፣ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ምን አለ ?
- ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ ስታስተናግድ የዓለም አቀፉን ሕግ መሠረት በማድረግ ከለላና ጥበቃ የምታደርግ ቢሆንም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለስደተኞች የሚቀርበው ዕርዳታ በመቆሙ ቀውስ ተፈጥሯል።
- በምግብ እጥረት ምክንያት የሚሞቱትና የሚታመሙት ወይም የሚቸገሩት ስደተኞች ብቻ ሳይሆኑ፣ ችግር ሲፈጠር በመሠረታዊነት የመጀመርያ ተጎጂ ሕፃናትና ሴቶች ናቸው።
- በመጠለያ ካምፕ የሚገኝን ሀብት አፈላልጎ ለመመገብ ጥረት በሚያደርግበት ወቅት፣ ስደተኞቹ ከአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር ግጭት ውስጥ ይገቡና ሰላማዊ የኑሮ ሁኔታን የሚያናጋ ነገር እየተፈጠረ ነው።
- በአሁኑ ወቅት ምግብ ነክ ድጋፎች እየቀረቡ ባለመሆናቸእ በቀጣይ አፋጣኝ ዕርምጃ ካልተወሰደ ችግሩ የከፋ ሊሆን ይቻላል። በሁሉም የአገሪቱ መጠለያ ካምፖች ችግሩ ተከቷል።
- በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞችን ለመታደግ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ንግግር እየተደረገ ነው ፤ በአጭር ጊዜ ዕርዳታው እንደገና ይጀመራል የሚል እምነት አለ።
በስደተኛ ቁጥር ፦
👉 በጋምቤላ ወደ 400,000
👉 በቦሎ መልካዲዳ በሶማሌ ክልል 200,000፣
👉 በቤኒሻንጉል አሶሳ ወደ 90,000፣
👉 በአፋር 68,000፣
👉 በሶማሌ ጅግጅጋ ወደ 50,000፣
👉 አማራ ክልል ባባት 25,000፣ መተማ ወደ 40,000፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ወደ 80,000 ስደኞች ይገኛሉ።
ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ስደተኞች መካከል ከ900,000 በላይ የሚሆኑት በመጠለያ ካምፕ ውስጥ ናቸው።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ፣ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ዕርዳታ ለተረጂዎች እየቀረበ ባለመሆኑ ወደ 400,000 የሚጠጉ በጋምቤላ ክልል ውስጥ በካምፕ የሚገኙ ስደተኞች ሕይወት አደጋ ውስጥ መውደቁን ገልጾ አፋጣኝ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡
በጋምቤላ ክልል ከግንቦት 2015 ዓ.ም. ወር ጀምሮ ዕርዳታ ያላገኙ ስደተኞች (አብዛኞቹ ከደ/ሱዳን የተሰደዱ) በምግብ እጥረት የተነሳ በሚመጣ ረሃብ ለሞትና ለከፋ ሕመም እየተጋለጡ መሆናቸውን አረጋግጧል።
ኮሚሽኑ ከስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ተቋም አገኘሁት ባለው መረጃ በምግብ እጥረት ምክንያት በጋምቤላ ብቻ 30 ሰዎች መሞታቸውን፣ 5 ዓመት ያልሞላቸው ሕፃናት ለከፋ ሕመም መጋለጣቸውን አስታውቋል፡፡
በተከሰተው የምግብ እጥረት የተነሳ ከስደተኞች መጠለያ ካምፕ ወጥተው ወደ ማኅበረሰቡ በሚገቡበት ወቅት ለሰላም ችግር መንስዔ መሆናቸው በኮሚሽኑ ሪፖርት የተገለጸ ሲሆን፣ ከመጠለያ ወጥተው በምግብ ስርቆት በመሰማራታቸውና ከቆሻሻ ላይ ምግብ ለማንሳት ሲጥሩ ሕይወታቸው ያለፉ መኖራቸውንም አስታውቋል፡፡
አሁን ላይ በርካታ ስደተኞች አደጋ ላይ በመሆናቸው የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም ሆኑ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡ ኢሰመኮ አሳስቧል።
#ሪፖርተር
@tikvahethiopia