TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
አሳዛኝ ዜና‼️

በአዲስ አበባ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው 31 ቁጥር ማዞሪያ አካባቢ ዛሬ ጠዋት በደረሰ የትራፊክ አደጋ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ  ስድስቱ ደግሞ  የአካል ጉዳት ደረሰባቸው።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ለኢዜአ እንደገለፀው አደጋው የደረሰው ተሳፋሪ ጭኖ ከቁስቋም ወደሽሮሜዳ ሲጓዝ የነበረ ሰሌዳ ቁጥሩ 10633 ኮድ አንድ የሆነ ሚኒባስ ታክሲ አቅጣጫውን ስቶ ከኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ምሶሶ ጋር በመጋጨቱ ነው።

በአደጋው ሁለት ተሳፋሪዎች #ሞተዋል፤ ጉዳት ከደረሰባቸው ስድስት ሰዎች መካከልም ሁለቱ በከባድ መጎዳታቸውም  ተመልክቷል። 

ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው። 

የአደጋው መንስኤ እየተጣራ እንደሆነም የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ተናግረዋል።

በአደጋው የሞቱት ሴቶች ሲሆኑ የተጎዱት ደግሞ ወንዶች መሆናቸውን ነው ኢንስፔክተር ማርቆስ የጠቀሱት። 

በአደጋው መስተዋቱን ጨምሮ #የተሽከርካሪው አካል መጎዳቱን በቦታው የተገኘው የኢዜአ ሪፖርተር ተመልክቷል።

የዓይን እማኞች እንደገለፁት አደጋው በተሽከርካሪው ፍሬን ችግር የተከሰተ ነው።

በታክሲው ተሳፍረው ሲጓዙ የነበሩት አቶ አንዷለም ለማ እንዳሉት በጠዋት ወደ ቢሮ ለመሄድ በጉዞ ላይ እያሉ አንዲት ተሳፋሪ መውረጃዋ ደርሶ “ወራጅ” ብትልም ታክሲው ሊቆም አልቻለም።

“ከዚያም ከደቂቃዎች ልዩነት በኋላ የታክሲው ረዳት ሰዎችን ከመንገዱ ዞር እንዲሉ ማስጠንቀቅ ጀመረ፤ ሹፌሩም የመኪናውን መሪ ይዞ ሲታገል ነበር “ያሉት አቶ አንዷለም ከዛ በኃላ መኪናው ተጋጭቶ ሲቆምና ከመኪናው ውጪም የተጎዳ ሰው ማየታቸውን ያስታውሳሉ።

ተሳፋሪው ከተረጋጋ በኃላ ሁለት ሰዎች መሞታቸውን እንደሰሙም አክለዋል።

አሽከርካሪዎች ሲጓዙ የቴክኒክ ፍተሻ በማድረግ ራሳቸውንና ኀብረተሰቡን ከአደጋ መጠበቅ እንዳለባቸውም አቶ አንዷለም መልዕክት አስተላልፈዋል። 

ምንጭ፦ ኢዜአ
ፎቶ፦NTU(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ይርጋለም #ሞረቾ #አገረሰላም~የፀጥታ ሁኔታ!

ትናንት ግጭት እና ተቃውሞ በታየባት ሐዋሳ ከተማ ዛሬ አንፃራዊ መረጋጋት እንደሚታይ የጀርመን ራድዮ ገለፀ። የጀርመን ራድዮ ዘጋቢ እንደገለፀዉ ከሐዋሳ ውጪ በሞሮቾ፣ ይርጋለም እና አገረሰላም በተባሉት ከተሞች #አሁንም ግጭቶች እና አለመረጋጋቶች እንዳሉ የዓይን እማኞች ሰቅሶ ዘግቧል። በሞሮቾ የሚገኝ አንድ የዓይን እማኝ እንዳለው ወጣቶች ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በነበራቸው ግጭት «የሚያውቃቸው ወጣቶች #ሞተዋል። መንገዶች በትላልቅ ድንጋዮች #ተዘግተዋል። ከሐዋሳ በዲላ በኩል ወደ ሞያሌ እና ኬንያ የሚወስደውም መንገድ ተዘግቷል።» አገረሠላም የሚገኙ የዓይን እማኞች እንደገለፁት ደግሞ «ትናንትና ሰዎች ሞተዋል። ወጣቶች ቤት #አቃጥለዋል።» በከተማዋ የመከላከያ ሰራዊት የገባ ሲሆን ዛሬ ላይ መጠነኛ መረጋጋት ይታያል። «ሆኖም ከተማዋ ውስጥ ዛሬም አልፎ አልፎ ተኩስ ይሰማል።» የሲዳማ ዞን ፖሊስ በሐዋሳ አጎራባች አካባቢዎች አሁንም አለመረጋጋት መኖሩን ለ ጀርመን ራድዮ አረጋግጧል። በሲዳማ በተለያዩ አካባቢዎች የታዩትን አለመረጋጋቶች ተከትሎ ደረሰ ስለተባለዉ ጉዳት ግን ፖሊስ መረጃ በማሰባሰብ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።

Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia