TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.7K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#update በእስር ላይ የሚገኙት እነ አቶ በረከት ስምዖን #ኮምፒውተር#ስልክ እና #የኢንተርኔት አገልግሎት ለማግኘት ያቀረቡትን ጥያቄ ፍርድ ቤት #ውድቅ አድርጎባቸዋል። ተጠርጣሪዎቹ አቶ በረከት ስምዖንና አቶ #ታደሰ_ካሳ ከዚህ በፊት ምስክሮችንና የሕግ ባለሞያዎችን ምክር ለማገኘት እንዲረዳቸው የኮምፒውተር፣ የኢንተርኔትና የስልክ አገልግሎቶች በባህር ዳር ማረሚያ ቤት እንዲሟላላቸው ጠይቀው ነበር፡፡ ሆኖም ለአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት ኮምፒዩተሮችና የስልክ አገልግሎት በማረሚያ ቤቱ ስለሚገኙ ተጠርጣሪዎቹም በዛው እንዲገለገሉ በማለት የባሕር ዳር እና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥያቄውን ዛሬ ወድቅ ማድረጉን የጀርመን ራድዮ ዘግቧል። ፍርድ ቤቱ ግለሰቦቹ እንደሌሎች ጠጠርጣሪዎች ማረሚያ ቤቱ የሚያቀርበውን ማንኛውንም ቁሳቁስ እንዲጠቀሙ በማለት ትዕዛዝ ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ ባለፈው አርብ እለት የአማራ ክልል የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የጠየቀውን የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ በመፍቀድ #ተጠርጣሪዎቹ ለመጋቢት 2 ቀን 2011 ዓ.ም እንዲቀርቡ አዟል።

Via የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሀዋሳ #የኢንተርኔት_አገልግሎት_መስራት_ጀምሯል

ከሳምንት በላይ ለሚሆን ጊዜ በሀዋሳ ከተማና ዙሪያዋ ተቋርጦ የነበረው የኢንተርኔት አገልግሎት ዛሬ መስራት ጀምሯል።
#ሀዋሳ #የኢንተርኔት_አገልግሎት_መስራት_ጀምሯል

ከሳምንት በላይ ለሚሆን ጊዜ በሀዋሳ ከተማና ዙሪያዋ ተቋርጦ የነበረው የኢንተርኔት አገልግሎት ዛሬ መስራት ጀምሯል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሟቾች ቁጥር 100 ደርሷል፤ ኢንተርኔት በበርካታ የሀገሪቱ ከተሞችም ተዘግቷል!

በኢራቅ ዋና ከተማ ባግዳድና አከባቢዋ 6 ቀናትን ባስቆጠረው ታቀውሞ የሞቱት ሰዎች 100 ደርሰዋል። በኢራቅ የተለያዩ ክፍሎች የሀገሪቱን መንግስት በመቃውም ተቃውሞ ከተቀሳቀሰ ስድስት ቀናትን አስቆጥሯል። በዚህ ታቃውሞ በርከት ብለው በመሳተፍ ላይ የሚገኙት ወጣቶች ሲሆኑ  ሙስናን ፣ ስራ አጥነትን እና ዝቅተኛ መንግስት አገልግሎትን በመቃወም ነው ተቃውሟቸውን እያሰሙ የሚገኙት፡፡

#የኢንተርኔት_አገልግሎት በበርካታ የሀገሪቱ ከተሞች ተቋርጧል። ዛሬ ጥዋት ለጥቂት ሰዓት ተከፍቶ የነበረ ቢሆንም የኢራቅ መንግስት ዳግም እንዲዘጋ አድርጎታል። ኢንተርኔት በተከፈተበት ወቅት የኢራቅ ዜጎች #VPN በመጠቀም በርካታ አሳዛኝና ለማየት የሚከብዱ ቪድዮዎችን ሲያጋሩ ነበር።

#IRAQ

•100 ሰዎች ሞተዋል
•4000 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል
•በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረዋል
•ሙሉ በሙሉ በሚል ደረጃ ኢንተርኔት ተዘግቷል

@tsegabwolde @tikvahethiopia