TIKVAH-ETHIOPIA
#ሐጅ " በዘንድሮ አመት ሐጅ ለማድረግ ዕቅድ ያላችሁ ቀድማችሁ የጉዞ ሰነዳችሁን (ፓስፖርታችሁን) ከወዲሁ ዝግጁ አድርጉ " - የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ2015/1444 አሂ የሃጅ መስተንግዶ በተሻለ መልኩ ለመስጠት ከክልልና ከተማ አስተዳደር የመጂሊስ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት መደረጉን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አሳውቋል። የ2015/1444 የተከበሩ የአሏህ…
#Update
• የዘንድሮ የሐጅ አድራጊ ክፍያ 👉 315,000 ብር እንዲሆን ተወስኗል።
የ1444/2015 የሁጃጆች ምዝገባ በ16 የምዝገባ ጣቢያዎች እንደሚካሄድ የተገለፀ ሲሆን የአንድ ሐጅ አድራጊ ክፍያ ብር 315,000 (ሶስት መቶ አስራ አምስት ሺህ) እንደሚሆን ይፋ ተደርጓል።
ይህ የተሰማው በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ1444/2015 ዓ.ል የሐጅ ምዝገባ በተመለከተ እየሰጠ በሚገኘው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
በመግለጫው የሐጅ ተጓዥ ለምዝገባ በአካል መቅረብ ይኖርበታል የተባለ ሲሆን ማንኛዉም ተመዝጋቢ የሚከተሉትንን መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል ፦
1. የታደስ የነዋሪነት መታወቂያ/ መንጃ ፈቃድ
2. የጉዞ ሰነድ (ፖስፖርት ) የመጠቀሚያ ጊዜው ለመጠናቀቅ ከ9 ወራት በላይ የቀረው መሆን ይኖርበታል፡፡
3. አንድ ጉርድ ፍቶ ግራፍ
4. የኮቪድ ክትባት የወሠደበት ማስረጃ እንዲሁም የቢጫ ወባ ክትባት ካርድ (ቢጫ ካርድ) ማቅረብ ይጠበቅበታል።
5. እራሳቸዉን ችለው የሐጅ ስርዓቱን መፈፀም የሚችሉ ወይም አስፈላጊውን መስፈርት አሟልተዉና ክፍያ ከፍለው ሊያግዛቸው የሚችል ሰው ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
ከእስልምና መሰረቶች ውስጥ አንዱ የሆነዉና አቅሙ ለፈቀደት ሙስሊም ወንድም ሆነ ሴት በዕድሜ ዘመኑ ቢያንስ አንድ ጊዜ ሐጅ የማድረግ ግዴታ እንዳለበት መሆኑ ይታወቃል።
(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት
@tikvahethiopia
• የዘንድሮ የሐጅ አድራጊ ክፍያ 👉 315,000 ብር እንዲሆን ተወስኗል።
የ1444/2015 የሁጃጆች ምዝገባ በ16 የምዝገባ ጣቢያዎች እንደሚካሄድ የተገለፀ ሲሆን የአንድ ሐጅ አድራጊ ክፍያ ብር 315,000 (ሶስት መቶ አስራ አምስት ሺህ) እንደሚሆን ይፋ ተደርጓል።
ይህ የተሰማው በአሁን ሰዓት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የ1444/2015 ዓ.ል የሐጅ ምዝገባ በተመለከተ እየሰጠ በሚገኘው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
በመግለጫው የሐጅ ተጓዥ ለምዝገባ በአካል መቅረብ ይኖርበታል የተባለ ሲሆን ማንኛዉም ተመዝጋቢ የሚከተሉትንን መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል ፦
1. የታደስ የነዋሪነት መታወቂያ/ መንጃ ፈቃድ
2. የጉዞ ሰነድ (ፖስፖርት ) የመጠቀሚያ ጊዜው ለመጠናቀቅ ከ9 ወራት በላይ የቀረው መሆን ይኖርበታል፡፡
3. አንድ ጉርድ ፍቶ ግራፍ
4. የኮቪድ ክትባት የወሠደበት ማስረጃ እንዲሁም የቢጫ ወባ ክትባት ካርድ (ቢጫ ካርድ) ማቅረብ ይጠበቅበታል።
5. እራሳቸዉን ችለው የሐጅ ስርዓቱን መፈፀም የሚችሉ ወይም አስፈላጊውን መስፈርት አሟልተዉና ክፍያ ከፍለው ሊያግዛቸው የሚችል ሰው ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
ከእስልምና መሰረቶች ውስጥ አንዱ የሆነዉና አቅሙ ለፈቀደት ሙስሊም ወንድም ሆነ ሴት በዕድሜ ዘመኑ ቢያንስ አንድ ጊዜ ሐጅ የማድረግ ግዴታ እንዳለበት መሆኑ ይታወቃል።
(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት
@tikvahethiopia
#ኢትዮ_ቴሌኮም
ኢትዮ ቴሌኮም “የቴሌብር ሱፐርአፕ” በማለት የሰየመውን ማዘመኛ በዛሬው ዕለት አስተዋውቋል።
ኢትዮ ቴሌኮም በ " ቴሌብር " መተግበሪያው ቀደም ሲል ለደንበኞቹ ሲያቀርብ ከነበረው አገልግሎት በተጨማሪ ተጨማሪ አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችለውን “የቴሌብር ሱፐርአፕ” በማለት የሰየመውን ማዘመኛ በቴሌብር መተግበሪያው ላይ ተግባራዊ አድርጎ በዛሬው ዕለት አስተዋውቋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፋጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ እንደተናገሩት፤ ተቋሙ የተለያዩ አካላትን (የቢዝነስ ተቋማትን፣ ሶፍትዌር አበልጻጊዎችን፣ Solution partner, Content provider) በማካተት የዲጂታል ኢኮኖሚን እየገነባ ነው።
ኃላፊዋ ተቋሙ የሞባይል መተግበሪያው ከገንዘብ አገልግሎቶች በተጨማሪ የተለያዩ መተግበሪያዎችን በውስጡ በመያዝ ለተገልጋዩ እንደሚያደርስ ነው የገለፁት።
በ " ቴሌብር ሱፐርአፕ " የተጨመሩ አዳዲስ አገልግሎቶች ምን ምን ናቸው ?
- የታቀደ ክፍያ፦ የገንዘብ እና የአየር ሰዓት ለመላክ እንዲሁም ወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን በቀኑ ለመክፈል ቀድሞ ማቀድ የሚያስችል አገልግሎት
- የድል ጨዋታ፦ አጠቃቀምን መሰረት ያደረ፣ የአጓጊ ሽልማቶች ባለቤት የሚኮንበት ልዩ ጨዋታ ነው
- ለቡድን ገንዘብ መላክ፦ ከአንድ በላይ ለሆኑ ተቀባዮች አስቀድመው በሚሞሉት መስፈርት መሰረት በአንዴ መላክ የሚያስችል አገልግሎት ነው።
- የተለያዩ መተግበሪያዎችን በአንድ ቦታ፦ የተለያዩ የአገልግሎት መተግበሪያዎችን መጫን ሳያስፈልግ በአንድ ቦታ ማግኘት የሚያስችል ነው። (ለምሳሌ:- የትራንስፖርት፣ እቁብ፣ ዴሊቨሪ፣ ኢ-ኮሜርስ፣ የትምህርት ወ.ዘ.ተ)
- የተለያዩ ዝግጅቶች/የበረራ ትኬቶችን መግዛት
መተግበሪያው የፋይናንስ እና መሰል አገልግሎቶችን በቀላሉ ለማግኘት፣ ለቢዝነስ ተቋማት ደግሞ ተጨማሪ የስራ እድልን ይፈጥራል፣ ተቋማት ከደንበኞቻቸው ጋር በቀላሉ እንዲገናኙ ያስችላል ተብሏል።
" ቴሌብር ሱፕርአፕ " መተግበሪያ በሁለተኛው ምዕራፍ የተለያዩ አዳዲስ አገልግሌቶችን ይዞ እንደሚመጣ ተጠቁሟል። " ቴሌብር ሱፐርአፕ "ን ከአፕ ስቶር ወይም ፕሌይስቶር በማዘመን/በማውረድ መጠቀም ይችላሉ።
ቴሌብር ሁለት አመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ 30 ሚሊዮን ደንበኞችን ማፍራቱን ገልጿል።
ባለፉት 22 ወራት ብቻ ከ101 ሺ በላይ ወኪሎች፣ ከ28 ሺህ ነጋዴዎች እንዲሁም ከ19 ባንኮች ጋር ትስስርን የፈጠረ ሲሆን ከ44 አገራት ከ1.95 ሚሊዮን ገቢ አድርጓል፡፡
በተጨማሪም በቅርቡ ባስጀመረው የዲጂታል ፋይናንስ የብድርና የቁጠባ አገልግሎቱ በቴሌብር መላ የብድር አገልግሎት ለ1.4 ሚሊዮን ተጠቃሚዎቹ 2.1 ቢሊዮን ብር ያበደረ ሲሆን 400 ሺ የቴሌብር ሳንዱቅ የቁጠባ አገልግሎት ተጠቃሚዎቹ 1.7 ቢሊዮን ብር እንዲቆጥቡ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል፡፡
@tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም “የቴሌብር ሱፐርአፕ” በማለት የሰየመውን ማዘመኛ በዛሬው ዕለት አስተዋውቋል።
ኢትዮ ቴሌኮም በ " ቴሌብር " መተግበሪያው ቀደም ሲል ለደንበኞቹ ሲያቀርብ ከነበረው አገልግሎት በተጨማሪ ተጨማሪ አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችለውን “የቴሌብር ሱፐርአፕ” በማለት የሰየመውን ማዘመኛ በቴሌብር መተግበሪያው ላይ ተግባራዊ አድርጎ በዛሬው ዕለት አስተዋውቋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፋጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ እንደተናገሩት፤ ተቋሙ የተለያዩ አካላትን (የቢዝነስ ተቋማትን፣ ሶፍትዌር አበልጻጊዎችን፣ Solution partner, Content provider) በማካተት የዲጂታል ኢኮኖሚን እየገነባ ነው።
ኃላፊዋ ተቋሙ የሞባይል መተግበሪያው ከገንዘብ አገልግሎቶች በተጨማሪ የተለያዩ መተግበሪያዎችን በውስጡ በመያዝ ለተገልጋዩ እንደሚያደርስ ነው የገለፁት።
በ " ቴሌብር ሱፐርአፕ " የተጨመሩ አዳዲስ አገልግሎቶች ምን ምን ናቸው ?
- የታቀደ ክፍያ፦ የገንዘብ እና የአየር ሰዓት ለመላክ እንዲሁም ወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን በቀኑ ለመክፈል ቀድሞ ማቀድ የሚያስችል አገልግሎት
- የድል ጨዋታ፦ አጠቃቀምን መሰረት ያደረ፣ የአጓጊ ሽልማቶች ባለቤት የሚኮንበት ልዩ ጨዋታ ነው
- ለቡድን ገንዘብ መላክ፦ ከአንድ በላይ ለሆኑ ተቀባዮች አስቀድመው በሚሞሉት መስፈርት መሰረት በአንዴ መላክ የሚያስችል አገልግሎት ነው።
- የተለያዩ መተግበሪያዎችን በአንድ ቦታ፦ የተለያዩ የአገልግሎት መተግበሪያዎችን መጫን ሳያስፈልግ በአንድ ቦታ ማግኘት የሚያስችል ነው። (ለምሳሌ:- የትራንስፖርት፣ እቁብ፣ ዴሊቨሪ፣ ኢ-ኮሜርስ፣ የትምህርት ወ.ዘ.ተ)
- የተለያዩ ዝግጅቶች/የበረራ ትኬቶችን መግዛት
መተግበሪያው የፋይናንስ እና መሰል አገልግሎቶችን በቀላሉ ለማግኘት፣ ለቢዝነስ ተቋማት ደግሞ ተጨማሪ የስራ እድልን ይፈጥራል፣ ተቋማት ከደንበኞቻቸው ጋር በቀላሉ እንዲገናኙ ያስችላል ተብሏል።
" ቴሌብር ሱፕርአፕ " መተግበሪያ በሁለተኛው ምዕራፍ የተለያዩ አዳዲስ አገልግሌቶችን ይዞ እንደሚመጣ ተጠቁሟል። " ቴሌብር ሱፐርአፕ "ን ከአፕ ስቶር ወይም ፕሌይስቶር በማዘመን/በማውረድ መጠቀም ይችላሉ።
ቴሌብር ሁለት አመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ 30 ሚሊዮን ደንበኞችን ማፍራቱን ገልጿል።
ባለፉት 22 ወራት ብቻ ከ101 ሺ በላይ ወኪሎች፣ ከ28 ሺህ ነጋዴዎች እንዲሁም ከ19 ባንኮች ጋር ትስስርን የፈጠረ ሲሆን ከ44 አገራት ከ1.95 ሚሊዮን ገቢ አድርጓል፡፡
በተጨማሪም በቅርቡ ባስጀመረው የዲጂታል ፋይናንስ የብድርና የቁጠባ አገልግሎቱ በቴሌብር መላ የብድር አገልግሎት ለ1.4 ሚሊዮን ተጠቃሚዎቹ 2.1 ቢሊዮን ብር ያበደረ ሲሆን 400 ሺ የቴሌብር ሳንዱቅ የቁጠባ አገልግሎት ተጠቃሚዎቹ 1.7 ቢሊዮን ብር እንዲቆጥቡ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል፡፡
@tikvahethiopia
#አብን #ኢዜማ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገራዊ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የመጀመሪያ ዙር ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ላይ አስታውቀዋል።
በቀጣይም #በሚያግባቡ_ሀገራዊ_ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና #የጋራ_አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ መደረሳቸውንም ገልፀዋል።
ሁለቱ ፓርቲዎች የ " ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት " ን ከሽብርተኝነት መዝገብ መሰረዝን በቅድሚያ የተቃወሙ ፓርቲዎች ናቸው።
ፓርቲዎቹ ተቃውሟቸውን በየተናጠል ባወጡት በመግለጫ አሳውቀዋል።
ይህ ከተሰማ ከሰዓታት በኃላ ነው ሁለቱ ፓርቲዎች በሚያግባቡ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና የጋራ አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ እንደደረሱ የተነገረው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገራዊ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ የመጀመሪያ ዙር ገንቢ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ላይ አስታውቀዋል።
በቀጣይም #በሚያግባቡ_ሀገራዊ_ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና #የጋራ_አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ መደረሳቸውንም ገልፀዋል።
ሁለቱ ፓርቲዎች የ " ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት " ን ከሽብርተኝነት መዝገብ መሰረዝን በቅድሚያ የተቃወሙ ፓርቲዎች ናቸው።
ፓርቲዎቹ ተቃውሟቸውን በየተናጠል ባወጡት በመግለጫ አሳውቀዋል።
ይህ ከተሰማ ከሰዓታት በኃላ ነው ሁለቱ ፓርቲዎች በሚያግባቡ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይቶችን ለማድረግና የጋራ አቋም ለመያዝ ከስምምነት ላይ እንደደረሱ የተነገረው።
@tikvahethiopia
#ዲጂታል_ዕቁብ
በሃገራችን የመጀመሪያ የሆነው ዲጂታል ዕቁብ አስተማማኝ፣ ተደራሽ፤ ሰፊ አማራጮች ያሉትን ዕቁቦች ይዘንሎት ስንመጣ በታላቅ ደስታ ነው።
እርስዎም አሁኑኑ የዲጂታል ዕቁብ መተግበሪያን ይጫኑ።
http://onelink.to/pm8mtg
ለነገ ህልምዎ ዛሬውኑ ዕቁብ በዲጂታል ይጀምሩ!!
ለተጨማሪ መረጃ 6091 ላይ ይደውሉ።
በሃገራችን የመጀመሪያ የሆነው ዲጂታል ዕቁብ አስተማማኝ፣ ተደራሽ፤ ሰፊ አማራጮች ያሉትን ዕቁቦች ይዘንሎት ስንመጣ በታላቅ ደስታ ነው።
እርስዎም አሁኑኑ የዲጂታል ዕቁብ መተግበሪያን ይጫኑ።
http://onelink.to/pm8mtg
ለነገ ህልምዎ ዛሬውኑ ዕቁብ በዲጂታል ይጀምሩ!!
ለተጨማሪ መረጃ 6091 ላይ ይደውሉ።
#ETHIOPIA
" የድርቅና ጎርፍ አደጋዎች በቀጣዮቹ ሳምንታትም #ተባብሠው ሊቀጥሉ ይችላሉ " - የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እየተከሠቱ ያሉት የድርቅና የጎርፍ አደጋዎች በቀጣዮቹ ሳምንታትም #ተባብሠው_ሊቀጥሉ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
የኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳሬክተር አቶ ክንፈ ኃ/ማሪያም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ62ኛ በኢትዮጵያ ለ42ኛ ጊዜ በሚከበረው የሚቲዎሮሎጂ ቀን ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው ይህ የተሰማው።
አቶ ክንፈ " በተቋሙ የተሠሩ ጥናቶች የሚያሳዩት #የድርቅ እና #የጎርፍ አደጋዎች በሀገሪቱ በቀጣይም በይበልጥ ተጠናክረው ይከሰታሉ " ብለዋል።
" የሚደርሰውን አደጋ ለመቋቋም የተጠናከረ የአየር ሁኔታ መከታተል ፣ መተንበይ እና ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሥርዓትን መገንባትና ማዘመንን ይገባል " ያሉት ምክትል ዳይሬክተሩ " እየተከሰተ ያለውን የአየር ንብረት መዛባት ቀድሞ ለመተንበይ የሚያስችል ብሔራዊ የአየር ጠባይ አገልግሎት ማዕቀፍ በሀገሪቱ ተዘርግቷል ፤ ይህ ተጠናክሮ ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲገባ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ያስፈልገዋል " ብለዋል።
አቶ ክንፈ ፤ በሀገሪቱ ለማኅበራዊ እና ለኢኮኖሚ መሠረት የሆኑ የግብርና፣ የውሀ፣ የኢነርጂና የአደጋ ሥጋት ቅነሳ መርሐ ግብሮች በአየር ንብረት መዛባት ተፅዕኖ ስር መሆናቸውን ገልፀው በእነሱ ላይ የሚደርሠውን የአየር ንብረት መዛባት አደጋ ለመቀነስ ተቋሙ ጥናትና ክትትል የማድረግ ሥራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
" በአየር ንብረት መዛባት የሚመጡ አደጋዎችን ማለትም ጎርፍ፣ ድርቅና የመሳሰሉትን ለመቀነስ ተቋሙ ክትትልና ጥናት በማድረግ ኅብረተሰቡን ከአደጋ ለመከላከል እየሠራ ነው " ሲሉ የገለፁት አቶ ክንፈ ፥ በአየር ንብረት መዛባት የሚደርሰውን የተለያየ አደጋ በዘላቂነት ለመቋቋም ተቋሙ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሠራ መሆኑን ባለድርሻ አካላትም በአጋርነት እየሰሩ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።
#ኢፕድ
@tikvahethiopia
" የድርቅና ጎርፍ አደጋዎች በቀጣዮቹ ሳምንታትም #ተባብሠው ሊቀጥሉ ይችላሉ " - የሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እየተከሠቱ ያሉት የድርቅና የጎርፍ አደጋዎች በቀጣዮቹ ሳምንታትም #ተባብሠው_ሊቀጥሉ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
የኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳሬክተር አቶ ክንፈ ኃ/ማሪያም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ62ኛ በኢትዮጵያ ለ42ኛ ጊዜ በሚከበረው የሚቲዎሮሎጂ ቀን ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው ይህ የተሰማው።
አቶ ክንፈ " በተቋሙ የተሠሩ ጥናቶች የሚያሳዩት #የድርቅ እና #የጎርፍ አደጋዎች በሀገሪቱ በቀጣይም በይበልጥ ተጠናክረው ይከሰታሉ " ብለዋል።
" የሚደርሰውን አደጋ ለመቋቋም የተጠናከረ የአየር ሁኔታ መከታተል ፣ መተንበይ እና ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሥርዓትን መገንባትና ማዘመንን ይገባል " ያሉት ምክትል ዳይሬክተሩ " እየተከሰተ ያለውን የአየር ንብረት መዛባት ቀድሞ ለመተንበይ የሚያስችል ብሔራዊ የአየር ጠባይ አገልግሎት ማዕቀፍ በሀገሪቱ ተዘርግቷል ፤ ይህ ተጠናክሮ ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲገባ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ያስፈልገዋል " ብለዋል።
አቶ ክንፈ ፤ በሀገሪቱ ለማኅበራዊ እና ለኢኮኖሚ መሠረት የሆኑ የግብርና፣ የውሀ፣ የኢነርጂና የአደጋ ሥጋት ቅነሳ መርሐ ግብሮች በአየር ንብረት መዛባት ተፅዕኖ ስር መሆናቸውን ገልፀው በእነሱ ላይ የሚደርሠውን የአየር ንብረት መዛባት አደጋ ለመቀነስ ተቋሙ ጥናትና ክትትል የማድረግ ሥራ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
" በአየር ንብረት መዛባት የሚመጡ አደጋዎችን ማለትም ጎርፍ፣ ድርቅና የመሳሰሉትን ለመቀነስ ተቋሙ ክትትልና ጥናት በማድረግ ኅብረተሰቡን ከአደጋ ለመከላከል እየሠራ ነው " ሲሉ የገለፁት አቶ ክንፈ ፥ በአየር ንብረት መዛባት የሚደርሰውን የተለያየ አደጋ በዘላቂነት ለመቋቋም ተቋሙ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሠራ መሆኑን ባለድርሻ አካላትም በአጋርነት እየሰሩ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።
#ኢፕድ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ኡጋንዳ
" ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ #አይፈርሙ " - ተመድ
" ህጉ ኤችአይቪ/ኤድስን በመዋጋት ረገድ የተገኘውን ውጤት ሊቀለበስ ይችላል " - አንቶኒ ብሊንከን (የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ከቀናት በፊት ከተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት / አፍቃሪዎች ጋር በተያያዘ የኡጋንዳ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ ተቃወመ።
የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ በሕግ አውጭዎች ማክሰኞ የፀደቀውን ህግ እንዳይፈርሙ በይፋ ጥያቄ አቅርበዋል።
ኮሚሽነሩ ህጉን " ጨካኝ ህግ " ሲሉ ጠርተው በአጠቃላይ በህብረተሰቡ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያሳድር እና የሀገሪቱን ህገ መንግስት እንደሚጥስ ገልጸዋል።
እኚሁ የተመድ ባለስልጣን ፤ ፓርላማው ያሳለፈው ይኸው ህግ አድሎአዊ ነው ብለው " ምናልባትም በዓለም ላይ ካሉት እጅግ በጣም አስከፊው ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ፕሬዜዳት ሙሴቬኒ በህጉ ላይ እንዳይፈርሙም ጠይቀዋል።
የኡጋንዳ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ የተለያዩ ምዕራባውያን ሀገራት እየተቃወሙ መሆናቸው ይታወቃል።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ውሳኔውን ተቃውመው ያሰራጩት መልዕክት በብዙሃን ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል።
ብሊንከን ህጉን " የኡጋንዳውያንን መሰረታዊ ሰብአዊ መብቶች የሚገታ እና ኤችአይቪ/ኤድስን በመዋጋት ረገድ የተገኘውን ውጤት ሊቀለበስ ይችላል። " ሲሉ ነው የገለፁት።
" የኡጋንዳ መንግስት የዚህን ህግ ተግባራዊነት እንደገና እንዲያጤነው #እናሳስባለን" ም ብለዋል።
የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሞሴቬኒ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ሀገሪቱ ለተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪዎች ምንም አይነት ቦታ እንደሌላት ገልፀዋል።
ከቀናት በፊትም በፓርላማ ባሰሙት ንግግር #ምዕራባውያን አገራት የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን መብቶች #በአፍሪካ አገራት ላይ በኃይል ለመጫን እየጣሩ ነው ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ " እንግዳ የሆነ ባህል / ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት እንድንፈቅድ ምዕራባዊያኑ ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ " ሲሉም ነው የገለፁት።
ፕሬዜዳንቱ ፓርላማው ባፀደቀው አዲሱ ህግ ላይ ፊርማቸውን ይኖራሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው ፤ ልክ ፊርማቸው እንዳረፈ በቅፅበት #ተግባራዊ ይሆናል።
በአዲሱ የኡጋንዳ ህግ ፦
- በኡጋንዳ ምድር ማንም ሰው የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪ ነኝ በሚል ማንነቱን ቢገልፅ ህይወቱን ሙሉ / ለበርካታ አመታ እስር ቤት ውስጥ እንዲያሳልፍ ይሆናል።
- በአንዳንድ ሁኔታዎች #ሞት ያስፈርዳል።
- የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን በጉያው ያቀፈ ፣ በቤተሰብ ደረጃ #ያስጠለለ ፣ ወዳጃቸው የሆነ ወይም አብሯቸው ያለ ሰው “እከሌ እና እከሌ” ብሎ ለሕግ አካላት ማንነታቸውን የማጋለጥ ግዴታን ይጥላል።
- ልጆችን ለዚሁ ለተመሳሳይ ጸታ ያጨ ወይም ያስተላለፈ #የእድሜ_ይፍታህ ፍርድ ይፀናበታል።
- " በተመሳሳይ ጸታ መብት " ዙርያ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ግንኙነቱን የሚያበረታታ ማንኛውንም የሕትመት ውጤት ማተም አልያም በሌሎች የመገናኛ ብዙኃን ማሠራጨት አይችሉም። ይህን ካደረጉ በሕግ ተጠያቂ ይሆናሉ።
@tikvahethiopia
" ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ #አይፈርሙ " - ተመድ
" ህጉ ኤችአይቪ/ኤድስን በመዋጋት ረገድ የተገኘውን ውጤት ሊቀለበስ ይችላል " - አንቶኒ ብሊንከን (የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር)
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ከቀናት በፊት ከተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት / አፍቃሪዎች ጋር በተያያዘ የኡጋንዳ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ ተቃወመ።
የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ በሕግ አውጭዎች ማክሰኞ የፀደቀውን ህግ እንዳይፈርሙ በይፋ ጥያቄ አቅርበዋል።
ኮሚሽነሩ ህጉን " ጨካኝ ህግ " ሲሉ ጠርተው በአጠቃላይ በህብረተሰቡ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያሳድር እና የሀገሪቱን ህገ መንግስት እንደሚጥስ ገልጸዋል።
እኚሁ የተመድ ባለስልጣን ፤ ፓርላማው ያሳለፈው ይኸው ህግ አድሎአዊ ነው ብለው " ምናልባትም በዓለም ላይ ካሉት እጅግ በጣም አስከፊው ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ፕሬዜዳት ሙሴቬኒ በህጉ ላይ እንዳይፈርሙም ጠይቀዋል።
የኡጋንዳ ፓርላማ ያሳለፈውን ውሳኔ የተለያዩ ምዕራባውያን ሀገራት እየተቃወሙ መሆናቸው ይታወቃል።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ውሳኔውን ተቃውመው ያሰራጩት መልዕክት በብዙሃን ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል።
ብሊንከን ህጉን " የኡጋንዳውያንን መሰረታዊ ሰብአዊ መብቶች የሚገታ እና ኤችአይቪ/ኤድስን በመዋጋት ረገድ የተገኘውን ውጤት ሊቀለበስ ይችላል። " ሲሉ ነው የገለፁት።
" የኡጋንዳ መንግስት የዚህን ህግ ተግባራዊነት እንደገና እንዲያጤነው #እናሳስባለን" ም ብለዋል።
የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሞሴቬኒ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ሀገሪቱ ለተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪዎች ምንም አይነት ቦታ እንደሌላት ገልፀዋል።
ከቀናት በፊትም በፓርላማ ባሰሙት ንግግር #ምዕራባውያን አገራት የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን መብቶች #በአፍሪካ አገራት ላይ በኃይል ለመጫን እየጣሩ ነው ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ " እንግዳ የሆነ ባህል / ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት እንድንፈቅድ ምዕራባዊያኑ ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ " ሲሉም ነው የገለፁት።
ፕሬዜዳንቱ ፓርላማው ባፀደቀው አዲሱ ህግ ላይ ፊርማቸውን ይኖራሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው ፤ ልክ ፊርማቸው እንዳረፈ በቅፅበት #ተግባራዊ ይሆናል።
በአዲሱ የኡጋንዳ ህግ ፦
- በኡጋንዳ ምድር ማንም ሰው የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪ ነኝ በሚል ማንነቱን ቢገልፅ ህይወቱን ሙሉ / ለበርካታ አመታ እስር ቤት ውስጥ እንዲያሳልፍ ይሆናል።
- በአንዳንድ ሁኔታዎች #ሞት ያስፈርዳል።
- የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን በጉያው ያቀፈ ፣ በቤተሰብ ደረጃ #ያስጠለለ ፣ ወዳጃቸው የሆነ ወይም አብሯቸው ያለ ሰው “እከሌ እና እከሌ” ብሎ ለሕግ አካላት ማንነታቸውን የማጋለጥ ግዴታን ይጥላል።
- ልጆችን ለዚሁ ለተመሳሳይ ጸታ ያጨ ወይም ያስተላለፈ #የእድሜ_ይፍታህ ፍርድ ይፀናበታል።
- " በተመሳሳይ ጸታ መብት " ዙርያ የሚሠሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ግንኙነቱን የሚያበረታታ ማንኛውንም የሕትመት ውጤት ማተም አልያም በሌሎች የመገናኛ ብዙኃን ማሠራጨት አይችሉም። ይህን ካደረጉ በሕግ ተጠያቂ ይሆናሉ።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳደር አድርገው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አሳውቋል። ርዕሰ መስተዳደሩ በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎችን ውክልና የሚያረጋገጥና አካታች የሆነ አስተዳደር በማዋቀር የክልሉን አስፈፃሚ አካል የመምራትና የማስተባበር ሃላፊነት ተጥሎባቸዋል ተብሏል። @tikvahethiopia
#Update
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በክልሉ ለሚገኙ መገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም መግለጫቸው ፤ " የትግራይ ህዝብ እራሱን ከጥፋትና ውድመት ለማዳን ሁሉንም አይነት መስዋዕትነት ከፍሏል። " ያሉ ሲሆን " ጊዜያዊ አስተዳደሩም የትግራይ ህዝብ የታገለለትንና መስዋእትነት የከፈለበትን ዓላማ ለማሳካት ይሰራል " ብለዋል።
አቶ ጌታቸው አስተዳደራቸው የትግራይን ግዛታዊ አንድነትን ማረጋገጥ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቄያቸው መመለስ እና የህዝቡን ሁለንተናዊ ችግሮች በፍጥነት መፍታት ዋነኛው አላማው አድርጎ እንደሚሰራ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውን ከክልሉ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን እንዲመሩ በህወሓት ማዕከላይ ኮሚቴ አብላጫ ድምፅ አግኝተው ከተመረጡ በኃላ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ክልሉን እንዲያስተዳድሩ ርዕሰ መስተዳደር አድርገው እንደሾሟቸው ትላንት የጠ/ሚ ፅ/ቤት ማሳወቁ ይታወሳል።
ተጨማሪ መረጃዎች ይኖራሉ።
@tikvahethiopia
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በክልሉ ለሚገኙ መገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህም መግለጫቸው ፤ " የትግራይ ህዝብ እራሱን ከጥፋትና ውድመት ለማዳን ሁሉንም አይነት መስዋዕትነት ከፍሏል። " ያሉ ሲሆን " ጊዜያዊ አስተዳደሩም የትግራይ ህዝብ የታገለለትንና መስዋእትነት የከፈለበትን ዓላማ ለማሳካት ይሰራል " ብለዋል።
አቶ ጌታቸው አስተዳደራቸው የትግራይን ግዛታዊ አንድነትን ማረጋገጥ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቄያቸው መመለስ እና የህዝቡን ሁለንተናዊ ችግሮች በፍጥነት መፍታት ዋነኛው አላማው አድርጎ እንደሚሰራ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውን ከክልሉ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን እንዲመሩ በህወሓት ማዕከላይ ኮሚቴ አብላጫ ድምፅ አግኝተው ከተመረጡ በኃላ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ክልሉን እንዲያስተዳድሩ ርዕሰ መስተዳደር አድርገው እንደሾሟቸው ትላንት የጠ/ሚ ፅ/ቤት ማሳወቁ ይታወሳል።
ተጨማሪ መረጃዎች ይኖራሉ።
@tikvahethiopia
“ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” - ስፔንሰር ኮክስ
የአሜሪካ ሀገር " ዩታህ ግዛት " በታዳጊዎች ፌስቡክ፣ ቲክቶክ እና ኢነስታግራምን የመሰሉ ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸው ላይ ገደብ ጣለች።
ይህ በማድረግ አሜሪካ ውስጥ የመጀመሪያዋ ግዛት ሆናለች።
ትላንት ሀሙስ በፀደቀው ደንብ መሰረት ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም፣ #ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።
የፀደቀው ደንብ ምን ይዟል ?
- የማኅበራዊ ሚዲያ አገልግሎት አቅራቢ ኩባንያዎች ለልጆች አገልግሎቱን ከማቅረባቸው በፊት #የወላጆችን ይሁንታ ማግኘት ይኖርባቸዋል።
- ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም፣ #ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።
- ኩባንያዎች መተግበሪያዎቻቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ አዳጊዎች ያለ ወላጅ ይሁንታ እንዳይከፍቱ ያደረጋሉ።
- ኩባንያዎቹ የአዳጊዎቹን የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣ ታሪክ፣ የለጠፏቸውን እና በግል #የተጻጻፏቸውን_መልዕክቶች ሁሉ ለወላጆች መስጠት ይገደዳሉ።
- የማኅበራዊ ሚዲያ አቅራቢ ኩባንያዎች የልጆቹን ፍላጎት እና ምርጫ መሠረት አድርገው #ማስታወቂያ በልጆቹ የማኅበራዊ ሚዲያ ሰሌዳቸው ላይ እንዳይለቁ ይገደዳሉ።
- ታዳጊዎች ማኅበራዊ ትስስር መድረኮችን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት እስከ ንጋት 12፡30 ድረስ መጠቀም እንዳይችሉ ይደነግጋል።
ሕጉ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ከሚቀጥለው ዓመት መጋቢት ጀምሮ ነው።
ይህን እርምጃ መውሰድ ያስፈለገው ማኅበራዊ የትስስር መድረኮች በልጆች #የአእምሮ_ጤና ላይ ከፍ ያለ መረበሽን እያደረሱ መሆኑ ከተደረሰበት በኋላ ነው ተብሏል።
የዩታህ ግዛት ገዢ ስፔንሰር ኮክስ በትዊተር ገፃቸው ላይ ፤ “ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” ሲሉ ጽፈዋል።
ከዩታህ በተጨማሪ ተመሳሳይ ሕጎች በቴክሳስ፣ በኦሃዮ፣ በአርካንሳስ፣ በኒው ጀርሲ እና በሊዊዚያና ግዛቶች እየተረቀቁ ነው መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።
Credit : #BBC
@tikvahethiopia
የአሜሪካ ሀገር " ዩታህ ግዛት " በታዳጊዎች ፌስቡክ፣ ቲክቶክ እና ኢነስታግራምን የመሰሉ ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸው ላይ ገደብ ጣለች።
ይህ በማድረግ አሜሪካ ውስጥ የመጀመሪያዋ ግዛት ሆናለች።
ትላንት ሀሙስ በፀደቀው ደንብ መሰረት ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም፣ #ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።
የፀደቀው ደንብ ምን ይዟል ?
- የማኅበራዊ ሚዲያ አገልግሎት አቅራቢ ኩባንያዎች ለልጆች አገልግሎቱን ከማቅረባቸው በፊት #የወላጆችን ይሁንታ ማግኘት ይኖርባቸዋል።
- ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም፣ #ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።
- ኩባንያዎች መተግበሪያዎቻቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ አዳጊዎች ያለ ወላጅ ይሁንታ እንዳይከፍቱ ያደረጋሉ።
- ኩባንያዎቹ የአዳጊዎቹን የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣ ታሪክ፣ የለጠፏቸውን እና በግል #የተጻጻፏቸውን_መልዕክቶች ሁሉ ለወላጆች መስጠት ይገደዳሉ።
- የማኅበራዊ ሚዲያ አቅራቢ ኩባንያዎች የልጆቹን ፍላጎት እና ምርጫ መሠረት አድርገው #ማስታወቂያ በልጆቹ የማኅበራዊ ሚዲያ ሰሌዳቸው ላይ እንዳይለቁ ይገደዳሉ።
- ታዳጊዎች ማኅበራዊ ትስስር መድረኮችን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት እስከ ንጋት 12፡30 ድረስ መጠቀም እንዳይችሉ ይደነግጋል።
ሕጉ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ከሚቀጥለው ዓመት መጋቢት ጀምሮ ነው።
ይህን እርምጃ መውሰድ ያስፈለገው ማኅበራዊ የትስስር መድረኮች በልጆች #የአእምሮ_ጤና ላይ ከፍ ያለ መረበሽን እያደረሱ መሆኑ ከተደረሰበት በኋላ ነው ተብሏል።
የዩታህ ግዛት ገዢ ስፔንሰር ኮክስ በትዊተር ገፃቸው ላይ ፤ “ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” ሲሉ ጽፈዋል።
ከዩታህ በተጨማሪ ተመሳሳይ ሕጎች በቴክሳስ፣ በኦሃዮ፣ በአርካንሳስ፣ በኒው ጀርሲ እና በሊዊዚያና ግዛቶች እየተረቀቁ ነው መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።
Credit : #BBC
@tikvahethiopia
#EthioTelecom
የምስራች !
ተወዳጁ ቴሌብር የከፍታ ጉዞውን በመቀጠል በአዲስ መተግበሪያ #ቴሌብር_ሱፐር_አፕ በርካታ መተግበሪያዎችንና አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ የሚያከናውኑበትንና የባዮሜትሪክስ የደህንነት ማረጋገጫን አካትቶ በአዲስ መልክ፤ በአዲስ ገጽታ ቀረበልዎ!
መተግበሪያውን ከ onelink.to/75zfa5 ያውርዱ፤ እልፍ ጉዳዮችዎን በአንድ ቦታ ይከውኑ!
ምን ይሄ ብቻ አዲሱን መተግበሪያ አውርደው የእድል ጨዋታ ሲጫወቱ እስከ መጋቢት 17 ድረስ 2 ላፕቶፖች፣ 3 ስማርት ስልኮች፣ 10 ስማርት ሰዓቶች እና ከ7ሺ በላይ የ100 ብር ሽልማቶች ይጠብቁዎታል።
(ኢትዮ ቴሌኮም)
የምስራች !
ተወዳጁ ቴሌብር የከፍታ ጉዞውን በመቀጠል በአዲስ መተግበሪያ #ቴሌብር_ሱፐር_አፕ በርካታ መተግበሪያዎችንና አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ የሚያከናውኑበትንና የባዮሜትሪክስ የደህንነት ማረጋገጫን አካትቶ በአዲስ መልክ፤ በአዲስ ገጽታ ቀረበልዎ!
መተግበሪያውን ከ onelink.to/75zfa5 ያውርዱ፤ እልፍ ጉዳዮችዎን በአንድ ቦታ ይከውኑ!
ምን ይሄ ብቻ አዲሱን መተግበሪያ አውርደው የእድል ጨዋታ ሲጫወቱ እስከ መጋቢት 17 ድረስ 2 ላፕቶፖች፣ 3 ስማርት ስልኮች፣ 10 ስማርት ሰዓቶች እና ከ7ሺ በላይ የ100 ብር ሽልማቶች ይጠብቁዎታል።
(ኢትዮ ቴሌኮም)
#አቢሲንያ_ባንክ
ከአጭበርባሪዎች ይጠንቀቁ፣ የይለፍ ቃል ለማንም አይስጡ !
አንዳንድ አጭበርባሪዎች በሞባይል ቴክስት የአንድ ጊዜ መጠቀሚያ የይለፍ ቃል (OTP) እንዲላክ ካረጉ በኋላ ከአቢሲንያ ባንክ የተደወለ በማስመሰል የተላከውን ቁጥር እንዲነግሯቸው እየጠየቁ ሲሆን አንዳንድ ደንበኞችም በቅንነት የሚስጥር ቁጥራቸውን አሳልፈው በመስጠት ለገንዘብ መጭበርበር እየተጋለጡ መሆኑን ደርሰንበታል፡፡
በመሆኑም በምንም መልኩ የሞባይል ባንኪንግ መጠቀሚያ የሚስጥር ቁጥራችሁን ለሶስተኛ ወገን አሳልፋችሁ እንዳትሰጡ እናሳስባለን፡፡
(አቢሲንያ ባንክ)
ከአጭበርባሪዎች ይጠንቀቁ፣ የይለፍ ቃል ለማንም አይስጡ !
አንዳንድ አጭበርባሪዎች በሞባይል ቴክስት የአንድ ጊዜ መጠቀሚያ የይለፍ ቃል (OTP) እንዲላክ ካረጉ በኋላ ከአቢሲንያ ባንክ የተደወለ በማስመሰል የተላከውን ቁጥር እንዲነግሯቸው እየጠየቁ ሲሆን አንዳንድ ደንበኞችም በቅንነት የሚስጥር ቁጥራቸውን አሳልፈው በመስጠት ለገንዘብ መጭበርበር እየተጋለጡ መሆኑን ደርሰንበታል፡፡
በመሆኑም በምንም መልኩ የሞባይል ባንኪንግ መጠቀሚያ የሚስጥር ቁጥራችሁን ለሶስተኛ ወገን አሳልፋችሁ እንዳትሰጡ እናሳስባለን፡፡
(አቢሲንያ ባንክ)