TIKVAH-ETHIOPIA
" ተማሪዎቹ በሰላም ገብተዋል " ዛሬ " የሰሜን ሜጫ ወረዳ የመንግስት ኮሚኒኬሽን " እና " የመራዊ ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት " ትላንት በአምቦ መስክ ቀበሌ ከባህር ዳር ወደ ደብረ ማርቆስ ያደረገ ኮስተር ተሽከርካሪ እና #ከሰከላ_ወረዳ የ12ኛ ክፍል ተማሪዌችን ጭኖ ወደ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ ተጋጭተው " ከቀላል እስከ ከባድ " ጉዳት መድረሱን አሳውቀው ነበር። ከዚህ በተጨማሪ ፤…
" ተማሪዎች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው ተርፈዋል ፤ ወላጆችም ተረጋጉ " - የሲግሞ ወረዳ
ዛሬ በጅማ ዞን ፤ ከሲግሞ ወረዳ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ጭኖ ወደ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ስጓዝ የነበረ አውቶብስ ተገልብጦ የትራፊክ አደጋ ደርሶ ነበር።
ነገር ግን ተማሪዎች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው መትረፋቸውን የወረዳው አስተዳደር አሳውቋል።
የተማሪ ወላጆችም ይህንን በማወቅ እንዲረጋጉ መልዕክት ተላልፏል።
መረጃው የሲግሞ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን / ሱልጣን ኢብራሂም / ነው።
በዚህ አጋጣሚ ወቅቱ ተማሪዎችን ወደ መፈተኛ ማዕከላት ከማድረስ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በመኖሩ አስሽከርካሪዎች በጥንቃቄ እና በእርጋታ እንዲያሽከረርክሩ በድጋሜ አደራ እንላለን።
@tikvahethiopia
ዛሬ በጅማ ዞን ፤ ከሲግሞ ወረዳ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ጭኖ ወደ ጅማ ዩኒቨርሲቲ ስጓዝ የነበረ አውቶብስ ተገልብጦ የትራፊክ አደጋ ደርሶ ነበር።
ነገር ግን ተማሪዎች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው መትረፋቸውን የወረዳው አስተዳደር አሳውቋል።
የተማሪ ወላጆችም ይህንን በማወቅ እንዲረጋጉ መልዕክት ተላልፏል።
መረጃው የሲግሞ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን / ሱልጣን ኢብራሂም / ነው።
በዚህ አጋጣሚ ወቅቱ ተማሪዎችን ወደ መፈተኛ ማዕከላት ከማድረስ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በመኖሩ አስሽከርካሪዎች በጥንቃቄ እና በእርጋታ እንዲያሽከረርክሩ በድጋሜ አደራ እንላለን።
@tikvahethiopia
#Gambella
" የአካባቢው ማህበረሰብ በተቻለው አቅም እራሱን እንዲጠብቅ አደራ እንላለን " - የጋምቤላ ክልል መንግስት
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል፤ ኑዌር ዞን በከፈቱት ተኩስ 3 ሰዎችን ሲገድሉ ፤ አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ አፍነውን ወስደዋል።
የጋምቤላ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን እንዳሳወቀው በቀን 26/01/2015 ዓ/ም ከቀኑ 12 ሰዓት ገደማ ላይ በኑዌር ዞን ፤ በማኮይ ወረዳ በሎንጆክ ቀበሌ የሙርሌ ታጣቂዎች ተኩስ ከፍተው 3 ሰዎችን ሲገድሉ፤ አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ አፍነው ወስደዋል።
ይህ ድርጊት የተፈፀመበት ቦታ " ጎርፍ ካጠቃቸው " ቦታዎች አንዱ ሲሆን ህብረተሰቡን የማረጋጋት እና ታጣቂዎች ለመያዝ እየተሰራ መሆኑን ክልሉ አሳውቋል።
የክልሉ መንግስት ፤ የአካባቢው ማህበረሰብ በተቻለው አቅም እራሱን እንዲጠብቅ አደራ ብሏል።
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጊዜ ድንበር ጥሰው እየገቡ በኑዌር ዞን እና አኝዋሃ ዞን በሰው ህይወት ላይ አደጋ ሲያደርሱ እና በርካታ ከብቶችንም ዘርፈው ሲወስዱ ቆይተዋል።
@tikvahethiopia
" የአካባቢው ማህበረሰብ በተቻለው አቅም እራሱን እንዲጠብቅ አደራ እንላለን " - የጋምቤላ ክልል መንግስት
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል፤ ኑዌር ዞን በከፈቱት ተኩስ 3 ሰዎችን ሲገድሉ ፤ አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ አፍነውን ወስደዋል።
የጋምቤላ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን እንዳሳወቀው በቀን 26/01/2015 ዓ/ም ከቀኑ 12 ሰዓት ገደማ ላይ በኑዌር ዞን ፤ በማኮይ ወረዳ በሎንጆክ ቀበሌ የሙርሌ ታጣቂዎች ተኩስ ከፍተው 3 ሰዎችን ሲገድሉ፤ አንድ የ11 ዓመት ታዳጊ አፍነው ወስደዋል።
ይህ ድርጊት የተፈፀመበት ቦታ " ጎርፍ ካጠቃቸው " ቦታዎች አንዱ ሲሆን ህብረተሰቡን የማረጋጋት እና ታጣቂዎች ለመያዝ እየተሰራ መሆኑን ክልሉ አሳውቋል።
የክልሉ መንግስት ፤ የአካባቢው ማህበረሰብ በተቻለው አቅም እራሱን እንዲጠብቅ አደራ ብሏል።
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጊዜ ድንበር ጥሰው እየገቡ በኑዌር ዞን እና አኝዋሃ ዞን በሰው ህይወት ላይ አደጋ ሲያደርሱ እና በርካታ ከብቶችንም ዘርፈው ሲወስዱ ቆይተዋል።
@tikvahethiopia
#UNHRC
የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ ኮሚሽን የሥራ ጊዜ ለአንድ ዓመት ተራዝሟል ፤ የስራ ጊዜው የተራዘመው ትላንት አጄኔቫ ውስጥ የተመድ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ም/ቤት አባላት ውሳኔውን በተመለከተ በሰጡት ድምጽ ነው።
የውሳኔ ሀሳቡ ጠባብ በሆነ የድምፅ ልዩነት ነው ተቀባይነት ያገኘው።
47 አባላት ካሉት የምክር ቤቱ አባላት መካከል የመርማሪ ቡድኑን ሥራ መቀጠል 21 ሀገራት ሲደግፉት 19ኙ ተቃውመውታል።
ከማላዊ " ድምፀ ተአቅቦ " በስተቀር የምክር ቤቱ አባል የሆኑ ሁሉም የአፍሪካ አገራት ውሳኔውን ተቃውመውታል።
የደገፉ ፦
- አርጀንቲና
- አርሜኒያ
- ብራዚል
- ቼክ ሪፐብሊክ
- ፊንላንድ
- ፈረንሳይ
- ጀርመን
- ሁንድራስ
- ጃፓን
- ሉቱንያ
- ሉክዘንበርግ
- ማርሻል አይላንድስ
- ሜክሲኮ
- ሞንቴኔግሮ
- ኔዘርላንድስ
- ፓራጓይ
- ፖላንድ
- ኮርያ ሪፐብሊክ
- ዩክሬን
- ዩናይትድ ኪንግደም
- አሜሪካ
የተቃወሙ ፦
- ቤኒን
- ቦሊቪያ
- ካሜሮን
- ቻይና
- ኮትዲቯር
- ኩባ
- ኤርትራ
- ጋቦን
- ጋምቢያ
- ህንድ
- ሊቢያ
- ሞሪታንያ
- ናሚቢያ
- ፓኪስታን
- ሴኔጋል
- ሶማሊያ
- ሱዳን
- ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ
- ቬንዙዌላ
ድምፀ ተአቅቦ ፦
- ኢንዶኔዥያ
- ካዛኪስታን
- ማላዊ
- ማሌዥያ
- ኔፓል
- ኳታር
- ሁዝቤክስታን
የውሳኔ ሀሳቡን መፅደቅ ተከትሎ በተ.መ.ድ. የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ፅ/ቤት (ጄኔቫ) ባወጣው መግለጫ ፤ የውሳኔ ሀሳቡን የተቃወሙ እና አጋርነትን ላሳዩ ፣ የድምፀ ተአቅቦ ላደረጉ የም/ቤት አባላት ምስጋና አቅርቦ ፤ በሰጡት ድምፅ ጣልቃ ገብነትን፣ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ማተራመስንና ማደፍረስን ነው የተቃወሙት ብሏል።
(የፅ/ቤቱ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መርማሪ ኮሚሽን የሥራ ጊዜ ለአንድ ዓመት ተራዝሟል ፤ የስራ ጊዜው የተራዘመው ትላንት አጄኔቫ ውስጥ የተመድ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ም/ቤት አባላት ውሳኔውን በተመለከተ በሰጡት ድምጽ ነው።
የውሳኔ ሀሳቡ ጠባብ በሆነ የድምፅ ልዩነት ነው ተቀባይነት ያገኘው።
47 አባላት ካሉት የምክር ቤቱ አባላት መካከል የመርማሪ ቡድኑን ሥራ መቀጠል 21 ሀገራት ሲደግፉት 19ኙ ተቃውመውታል።
ከማላዊ " ድምፀ ተአቅቦ " በስተቀር የምክር ቤቱ አባል የሆኑ ሁሉም የአፍሪካ አገራት ውሳኔውን ተቃውመውታል።
የደገፉ ፦
- አርጀንቲና
- አርሜኒያ
- ብራዚል
- ቼክ ሪፐብሊክ
- ፊንላንድ
- ፈረንሳይ
- ጀርመን
- ሁንድራስ
- ጃፓን
- ሉቱንያ
- ሉክዘንበርግ
- ማርሻል አይላንድስ
- ሜክሲኮ
- ሞንቴኔግሮ
- ኔዘርላንድስ
- ፓራጓይ
- ፖላንድ
- ኮርያ ሪፐብሊክ
- ዩክሬን
- ዩናይትድ ኪንግደም
- አሜሪካ
የተቃወሙ ፦
- ቤኒን
- ቦሊቪያ
- ካሜሮን
- ቻይና
- ኮትዲቯር
- ኩባ
- ኤርትራ
- ጋቦን
- ጋምቢያ
- ህንድ
- ሊቢያ
- ሞሪታንያ
- ናሚቢያ
- ፓኪስታን
- ሴኔጋል
- ሶማሊያ
- ሱዳን
- ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ
- ቬንዙዌላ
ድምፀ ተአቅቦ ፦
- ኢንዶኔዥያ
- ካዛኪስታን
- ማላዊ
- ማሌዥያ
- ኔፓል
- ኳታር
- ሁዝቤክስታን
የውሳኔ ሀሳቡን መፅደቅ ተከትሎ በተ.መ.ድ. የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ፅ/ቤት (ጄኔቫ) ባወጣው መግለጫ ፤ የውሳኔ ሀሳቡን የተቃወሙ እና አጋርነትን ላሳዩ ፣ የድምፀ ተአቅቦ ላደረጉ የም/ቤት አባላት ምስጋና አቅርቦ ፤ በሰጡት ድምፅ ጣልቃ ገብነትን፣ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ማተራመስንና ማደፍረስን ነው የተቃወሙት ብሏል።
(የፅ/ቤቱ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#WFP
የዓለም ምግብ ፕሮግራም ወደ ትግራይ ክልል በረራ ማድረጉን ዛሬ ገልጿል።
ይህ ጉዞ ከ6 ሳምንታት በኋላ የመጀመሪያው ነው።
ድርጅቱ 34 ሰራተኞቹን ከክልሉ ማስወጣቱን ገልጿል።
ተጨማሪ በረራዎች በመጪዎቹ ቀናት በማድረግ ሰራተኞቹን ከመቐለ ለማስወጣት ቀጠሮ መያዙንም የዓለም ምግብ ፕሮግራም አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የዓለም ምግብ ፕሮግራም ወደ ትግራይ ክልል በረራ ማድረጉን ዛሬ ገልጿል።
ይህ ጉዞ ከ6 ሳምንታት በኋላ የመጀመሪያው ነው።
ድርጅቱ 34 ሰራተኞቹን ከክልሉ ማስወጣቱን ገልጿል።
ተጨማሪ በረራዎች በመጪዎቹ ቀናት በማድረግ ሰራተኞቹን ከመቐለ ለማስወጣት ቀጠሮ መያዙንም የዓለም ምግብ ፕሮግራም አሳውቋል።
@tikvahethiopia