TIKVAH-ETHIOPIA
የቴፒ ነገር... TIKVAH-ETHIOPIA ከቴፒ ከተማ ነዋሪ ቤተሰቦቹ መልዕክቶችን እያስተናገደ ነው። ከተማይቱ አይሁንም ቢሆን አስተማማኝ ደህንነት የላትም፤ መንግስት ኃይሉን አጠናክሮ ሰላምና ደህንነትን ማስጠበቅ አለበት ብለዋል። በተለይም የከተማው መግቢያና መውጫዎች ላይ ከፍተኛ ወንጀሎች እንድሚፈፁ ገልፀዋል። "ከቴፒ ነው የምጽፍላቹ! N ነኝ ቴፒ ነዋሪ ነኚ ቴፒ ላይ ከአቅም በላይ የሆነ ነገር አለ።…
#ቴፒ
"ከቴፒ የጻፍኩላቹ የናንተው ቤተሠብ ነኝ። ለ8 ቀን ተዘግቶ የነበረው የቴፓ መናህሪያ በመከላከያዎች ጥረትና አወያይነት ዛሬ ለመንገደኞች ክፍት ሁኖ እኛም መከላከያ ጫካውን አጅቦን ሸኚቶን ከቴፒ #ሚዛን ገብተናል መንገደኞችም ዛሬ ማንም ሣይዘረፍ ወደሚዛን ገብተናል! እድሜ ለፌደራልና ለመከላከያዋቹ ሁሉንም አመሥግኑልን የናንተው ቤተሠብ ከሚዛን ቴፒ!"
እኛ ደግሞ ይህን እንላለን...
የኢትዮጵያ መንግስት ለአካባቢው #ልዩ_ትኩረት ሰጥቶ ችግሮች በዘላቂነት የሚፈቱበትን መንገድ መፈለግ አለበት፤ ዜጎች በገዛ ሀገራቸው ላይ #ደህንነታቸው ተጠብቆ እንደልባቸው ወጥተው የሚገቡበትና ስራቸውን ያለእክል የሚሰሩበትን ሁኔታ መፍጠር ትልቁ የመንግስት ስራ በመሆኑ በተቻለ አቅምና ፍጥነት ይህን ማድረግ ይኖርበታል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ከቴፒ የጻፍኩላቹ የናንተው ቤተሠብ ነኝ። ለ8 ቀን ተዘግቶ የነበረው የቴፓ መናህሪያ በመከላከያዎች ጥረትና አወያይነት ዛሬ ለመንገደኞች ክፍት ሁኖ እኛም መከላከያ ጫካውን አጅቦን ሸኚቶን ከቴፒ #ሚዛን ገብተናል መንገደኞችም ዛሬ ማንም ሣይዘረፍ ወደሚዛን ገብተናል! እድሜ ለፌደራልና ለመከላከያዋቹ ሁሉንም አመሥግኑልን የናንተው ቤተሠብ ከሚዛን ቴፒ!"
እኛ ደግሞ ይህን እንላለን...
የኢትዮጵያ መንግስት ለአካባቢው #ልዩ_ትኩረት ሰጥቶ ችግሮች በዘላቂነት የሚፈቱበትን መንገድ መፈለግ አለበት፤ ዜጎች በገዛ ሀገራቸው ላይ #ደህንነታቸው ተጠብቆ እንደልባቸው ወጥተው የሚገቡበትና ስራቸውን ያለእክል የሚሰሩበትን ሁኔታ መፍጠር ትልቁ የመንግስት ስራ በመሆኑ በተቻለ አቅምና ፍጥነት ይህን ማድረግ ይኖርበታል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA
ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር መግለጫቸው ይበልጥ ትኩረቱን ያደረገው በሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በሚመለከት ነው።
በመግለጫቸው ምን አሉ ?
- 391 የሚደርሱ ሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች የባንክ ሂሳባቸው ተዘግቷል ፤ የግለሠቦቹን ስም ዝርዝር ለፍትሕ ሚኒስቴር በመላክ ክስ የመመስረት ሂደት ይጀመራል።
- በህገ ወጥ መልኩ #በጥቁር_ገበያ ላይ በተሠማሩ አካላት ላይ የተጠናከረ እርምጃ ይወሰዳል።
- በባንክ ቤቶች ውስጥ ያሉ የባንክ #ኃላፊዎችና #ሰራተኞችም በህገወጥ ተግባር ላይ የተሰማሩ አሉ በነዚህ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃና ሕጋዊ እርምጃ ይወሰዳል።
- ሕገወጥ ድርጊት ለሚጠቁሙ ዜጎች የወሮታ አከፋፈል ስርዓት ተዘጋጅቷል።
ይህ ማለት ፦
• ከተፈቀደው በላይ በቤት ውስጥ የብር ክምችት የሚያደርጉ፣
• የሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን የሚሠሩና የሚያሠራጩ አካላት፣
• በህገወጥ መልኩ የሐዋላ አገልግሎት የሚሠጡ ወይም በጥቁር ገበያ ላይ የተሰማሩ አካላትን ለሚጠቁሙ ዜጎች #ደህንነታቸው እና #ሚስጥራዊነታቸውን በጠበቀ መልኩ #የሚሸልምና #ወረታውን የሚከፈል ይሆናል።
- የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጣጠር የፈቀደውን የፍራኮ ቫሉታ ፍቃድ እንደ እድል በመጠቀም በህገወጥ መንገድ ዶላር በመጠቀም ሸቀጦችን የማስገባት ተግባር የተስተዋለ በመሆኑ በዚህ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች የባን ማስረጃ ለብሔራዊ ባንክ እንዲያቀርቡ ይደረጋል።
Credit : EPA
@tikvahethiopia
ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር መግለጫቸው ይበልጥ ትኩረቱን ያደረገው በሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በሚመለከት ነው።
በመግለጫቸው ምን አሉ ?
- 391 የሚደርሱ ሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች የባንክ ሂሳባቸው ተዘግቷል ፤ የግለሠቦቹን ስም ዝርዝር ለፍትሕ ሚኒስቴር በመላክ ክስ የመመስረት ሂደት ይጀመራል።
- በህገ ወጥ መልኩ #በጥቁር_ገበያ ላይ በተሠማሩ አካላት ላይ የተጠናከረ እርምጃ ይወሰዳል።
- በባንክ ቤቶች ውስጥ ያሉ የባንክ #ኃላፊዎችና #ሰራተኞችም በህገወጥ ተግባር ላይ የተሰማሩ አሉ በነዚህ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃና ሕጋዊ እርምጃ ይወሰዳል።
- ሕገወጥ ድርጊት ለሚጠቁሙ ዜጎች የወሮታ አከፋፈል ስርዓት ተዘጋጅቷል።
ይህ ማለት ፦
• ከተፈቀደው በላይ በቤት ውስጥ የብር ክምችት የሚያደርጉ፣
• የሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን የሚሠሩና የሚያሠራጩ አካላት፣
• በህገወጥ መልኩ የሐዋላ አገልግሎት የሚሠጡ ወይም በጥቁር ገበያ ላይ የተሰማሩ አካላትን ለሚጠቁሙ ዜጎች #ደህንነታቸው እና #ሚስጥራዊነታቸውን በጠበቀ መልኩ #የሚሸልምና #ወረታውን የሚከፈል ይሆናል።
- የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጣጠር የፈቀደውን የፍራኮ ቫሉታ ፍቃድ እንደ እድል በመጠቀም በህገወጥ መንገድ ዶላር በመጠቀም ሸቀጦችን የማስገባት ተግባር የተስተዋለ በመሆኑ በዚህ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች የባን ማስረጃ ለብሔራዊ ባንክ እንዲያቀርቡ ይደረጋል።
Credit : EPA
@tikvahethiopia