#Ethiopia #UNICEF
ስለምስራቅ አፍሪካ ድርቅ እና በሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ ስላሳደረው ተፅእኖ ምን ያህል እናውቃለን ?
(የተመድ የህጻናት ተራድኦ ድርጅት - UNICEF)
➤ ኢትዮጵያን ጨምሮ ምስራቅ አፍሪቃን የመታው ድርቅ ከ10 ሚሊየን በላይ #ህጻናት ለአስከፊ የምግብ እጥረት ዳርጓል። እስካሁን በርሃም አደጋው የሞተ ሰው አላጋጠመም።
➤ በኢትዮጵያ ባጋጠመው 3 ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች የዝናብ እጥረት በዓመታት አስከፊ የድርቅ ሁኔታ እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል፤ አስከፊው ድርቅ ለበርካታ እንስሳት ሞት ፣ የውኃ ምንጮችም ተሟጠው እንዲደርቁ መንስኤ ሆኗል።
➤ በ4 ክልሎች (ሶማሊ፣ ኦሮሚያ ፣ አፋር፣ ደቡብ ) ድርቅ በሰፊው የተከሰተባት ኢትዮጵያ ከችግሩ ለመላቀቅ ቢያንስ 5 ዓመታት ያስፈልጓታል።
➤ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች (ኦሮሚያ፣ ሶማሊ፣ አፋርና ደቡብ) ድርቁ 10 ሚሊየን ህዝብ ላይ ቀጥተኛ ተፅእኖ አሳርፏል። ከዚህ ውስጥ 1.5 ያህሉ ለተመጣጠነ የምግብ እጥረት የተዳረጉ ህጻናት ናቸው፡፡
➤ በኢትዮጵያ ያለው ድርቅ 1.75 ሚሊየን ህዝብን ከመኖሪያ ቀዬው አፈናቋል።
➤ በሶማሊ ክልል ከ5 ዓመት በታች የሆኑ 220 ሺ ህጻናት ገደማ የተመጣጠነ ምግብ እጦት አለባቸው፡፡ ከ150 ሺህ በላይ አጥቢና እርጉዝ እናቶች በቂ ምግብ የማያገኙ ናቸው።
➤ ባለፈው ዓመት በችግሩ ሳቢያ ከ400 ሺ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ተቆራርጠዋል፡፡ ይህ ደግሞ ያለዕድሜ ጋብቻን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ ምስቅልቅሎችን አሳርፏል።
➤ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ሳቢያ የናረው የስንዴና ሌሎች መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ዋጋ የድርቅ ተፅእኖውን ምላሽ የመስጠት ጥረቶችን አዳጋች አድርጎታል።
#UNICEF #ዶቼቨለ
@tikvahethiopia
ስለምስራቅ አፍሪካ ድርቅ እና በሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ ስላሳደረው ተፅእኖ ምን ያህል እናውቃለን ?
(የተመድ የህጻናት ተራድኦ ድርጅት - UNICEF)
➤ ኢትዮጵያን ጨምሮ ምስራቅ አፍሪቃን የመታው ድርቅ ከ10 ሚሊየን በላይ #ህጻናት ለአስከፊ የምግብ እጥረት ዳርጓል። እስካሁን በርሃም አደጋው የሞተ ሰው አላጋጠመም።
➤ በኢትዮጵያ ባጋጠመው 3 ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች የዝናብ እጥረት በዓመታት አስከፊ የድርቅ ሁኔታ እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል፤ አስከፊው ድርቅ ለበርካታ እንስሳት ሞት ፣ የውኃ ምንጮችም ተሟጠው እንዲደርቁ መንስኤ ሆኗል።
➤ በ4 ክልሎች (ሶማሊ፣ ኦሮሚያ ፣ አፋር፣ ደቡብ ) ድርቅ በሰፊው የተከሰተባት ኢትዮጵያ ከችግሩ ለመላቀቅ ቢያንስ 5 ዓመታት ያስፈልጓታል።
➤ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች (ኦሮሚያ፣ ሶማሊ፣ አፋርና ደቡብ) ድርቁ 10 ሚሊየን ህዝብ ላይ ቀጥተኛ ተፅእኖ አሳርፏል። ከዚህ ውስጥ 1.5 ያህሉ ለተመጣጠነ የምግብ እጥረት የተዳረጉ ህጻናት ናቸው፡፡
➤ በኢትዮጵያ ያለው ድርቅ 1.75 ሚሊየን ህዝብን ከመኖሪያ ቀዬው አፈናቋል።
➤ በሶማሊ ክልል ከ5 ዓመት በታች የሆኑ 220 ሺ ህጻናት ገደማ የተመጣጠነ ምግብ እጦት አለባቸው፡፡ ከ150 ሺህ በላይ አጥቢና እርጉዝ እናቶች በቂ ምግብ የማያገኙ ናቸው።
➤ ባለፈው ዓመት በችግሩ ሳቢያ ከ400 ሺ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ተቆራርጠዋል፡፡ ይህ ደግሞ ያለዕድሜ ጋብቻን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ ምስቅልቅሎችን አሳርፏል።
➤ በሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ሳቢያ የናረው የስንዴና ሌሎች መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ዋጋ የድርቅ ተፅእኖውን ምላሽ የመስጠት ጥረቶችን አዳጋች አድርጎታል።
#UNICEF #ዶቼቨለ
@tikvahethiopia
#DireDawa
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለቀጣይ አምስት ወር በመኖሪያ ቤት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግም ሆነ ተከራዮችን ቤት ማስለቀቅ እንደማይቻል ውሳኔ አሳልፏል።
ከተማ አስተዳደሩ ፤ በመኖርያ ቤት ተከራዮች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ እና አለአግባብ ከፍተኛ ጭማሪ እየተደረገ መሆኑን በተለያየ መንገድ አረጋግጫለሁ ብሏል።
ይህን ተከትሎ ነው ለ 5 ወራት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግ ሆነ ከተከራዩት ቤት ማስወጣት እንደማይቻል ውሳኔ ያሳለፈው።
#ዶቼቨለ
@tikvahethiopia
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለቀጣይ አምስት ወር በመኖሪያ ቤት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግም ሆነ ተከራዮችን ቤት ማስለቀቅ እንደማይቻል ውሳኔ አሳልፏል።
ከተማ አስተዳደሩ ፤ በመኖርያ ቤት ተከራዮች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ እና አለአግባብ ከፍተኛ ጭማሪ እየተደረገ መሆኑን በተለያየ መንገድ አረጋግጫለሁ ብሏል።
ይህን ተከትሎ ነው ለ 5 ወራት ተከራዮች ላይ ጭማሪ ማድረግ ሆነ ከተከራዩት ቤት ማስወጣት እንደማይቻል ውሳኔ ያሳለፈው።
#ዶቼቨለ
@tikvahethiopia