የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መግለጫ አውጥቷል።
ጉባኤው በመግለጫው " በጎንደር ከተማ በሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ ሚያዝያ 18 ቀን 2014 ዓ.ም የተፈፀመው የግድያ፤ የመስኪድ ቃጠሎ የሙስሊም ግለሰቦች ንብረት ውድመትና ዘረፋ በሃይማኖት እጅግ የከፋ ሃጢያት ሲሆን በፈጣሪም ዘንድ የሚያስጠይቅ ፀያፍ ተግባር ነው፡፡ የሃገራችን ሕዝብ ልዩነትን በማክበር በጋራ ጉዳዮች ላይ በመደጋገፍና በመተባበር ለዘመናት የኖረበትን የተከበሩ እሴቶችና ታሪኮች የሚያጎድፍ እጅግ አሳዛኝ ተግባር ነው፡፡ " ብሏል።
ጉባኤው " የሃገራችን ሕዝብ ልዩነትን በማክበር በጋራ ጉዳዮች ላይ በመደጋገፍና በመተባበር ለዘመናት የኖረበትን የተከበሩ እሴቶችና ታሪኮች የሚያጎድፍ እጅግ አሳዛኝ ተግባር ነው፡፡ " ሲልም አክሏል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፤ የደረሰውን የሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት ዜና የሰማው በታላቅ የልብ ስብራት መሆኑም ገልጾ ድርጊቱን አምርሮ እንደሚያወግዝ ገልጿል።
(ዝርዝር መገለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ጉባኤው በመግለጫው " በጎንደር ከተማ በሚገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ ሚያዝያ 18 ቀን 2014 ዓ.ም የተፈፀመው የግድያ፤ የመስኪድ ቃጠሎ የሙስሊም ግለሰቦች ንብረት ውድመትና ዘረፋ በሃይማኖት እጅግ የከፋ ሃጢያት ሲሆን በፈጣሪም ዘንድ የሚያስጠይቅ ፀያፍ ተግባር ነው፡፡ የሃገራችን ሕዝብ ልዩነትን በማክበር በጋራ ጉዳዮች ላይ በመደጋገፍና በመተባበር ለዘመናት የኖረበትን የተከበሩ እሴቶችና ታሪኮች የሚያጎድፍ እጅግ አሳዛኝ ተግባር ነው፡፡ " ብሏል።
ጉባኤው " የሃገራችን ሕዝብ ልዩነትን በማክበር በጋራ ጉዳዮች ላይ በመደጋገፍና በመተባበር ለዘመናት የኖረበትን የተከበሩ እሴቶችና ታሪኮች የሚያጎድፍ እጅግ አሳዛኝ ተግባር ነው፡፡ " ሲልም አክሏል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ፤ የደረሰውን የሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት ዜና የሰማው በታላቅ የልብ ስብራት መሆኑም ገልጾ ድርጊቱን አምርሮ እንደሚያወግዝ ገልጿል።
(ዝርዝር መገለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#Repost
ስለፊቼ ጨምባላላ ምን ያህል ያውቃሉ ?
- የሲዳማ ሕዝብ የጨረቃና ከዋክብትን አቀማመጥ በማጥናት አዲስ ዓመት ያከብራል። በዓሉም ፊቼ ጨምበላላ ይባላል።
- ፊቼ ጫምባላላ መከበር ከጀመረ ከ1800 ዓመታት በላይ ማስቆጠሩን የአገር ሽማግሌዎች ይናገራል።
- በዓሉ የሲዳማ ሕዝብ ማንነቱን ከተረዳበት ጊዜ አንስቶ ሲከበር ቆይቷል።
- ፊቼ ጨምበላላ በዓል የሚከበርበት ቋሚ ቀን የለውም። በአያንቱዎች ጥቆማ መሰረት በዓሉ የሚከበርበት ቀን ይቆረጣል።
- 'የፊቼ ጨምበላላ ዋነኛ ትርጉም ሰላም ነው'፤ አንድነትና ፍቅር የበዓሉ መለያ ነው።
- የተጣሉ ሰዎች በፊቼ ጨምበላላ በዓል ላይ ይታረቃሉ። ሃዘን ላይ የነበሩ ሰዎችም የሃዘን ልብሳቸውን ይቀይራሉ።
- ከቀዬው ርቆ የነበረ ሰው ለፊቼ ጨምበላላ ወደቀዬው ይመለሳል።
- ለዚህ በዓል ተብሎ እርድ አይፈጸምም፤ ስጋም አይበላም። ክብቶችን መምታትም ክልክል ነው። ላሞች ሳር የበዛበት መስክ ላይ ይሰማራሉ።
- በሲዳማ ሕዝብ ዘንድ በፊቼ ጨምበላላ በዓል ወቅት ማረስ ነውር ነው። ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የፊቼ ጨምበላላ በዓል የሲዳማ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮም ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው።
- ፊቼ የአዲስ ዓመት በዓል ዋዜማ ሲሆን፤ ጨምበላላ ደግሞ የአዲስ ዓመት መጀመሪያው ቀን ነው።
- ሲዳማ ከአንድ ዓመት ወደሌላው የሚሸጋገርበት ሂደት ሁሉቃ ይባላል። ሁሉቃ ማለት ከሸምበቆና ከአርጥብ ቅጠል ተሠርቶ የሚቆም ነገር ነው። ሁሉቃ በቤተሰብና በማኅበረሰብ ደረጃ የሚሠራ ሲሆን፤ አዲስ ዓመት ሲገባ ሰዎችና ከብቶች ይተላለፉበታል።
- የሲዳማ ሕዝብ አዲስ ዓመትን ሲቀበሉ፤ ዓመቱ የብልጽግና እንዲሆንላቸው 'ፊቼ ጄጂ' ይላሉ።
ይህ መረጃ የቀረበው ከ2019 የቢቢሲ ድረገፅ ላይ ከወጣው ፅሁፍ ነው።
@tikvahethiopia
ስለፊቼ ጨምባላላ ምን ያህል ያውቃሉ ?
- የሲዳማ ሕዝብ የጨረቃና ከዋክብትን አቀማመጥ በማጥናት አዲስ ዓመት ያከብራል። በዓሉም ፊቼ ጨምበላላ ይባላል።
- ፊቼ ጫምባላላ መከበር ከጀመረ ከ1800 ዓመታት በላይ ማስቆጠሩን የአገር ሽማግሌዎች ይናገራል።
- በዓሉ የሲዳማ ሕዝብ ማንነቱን ከተረዳበት ጊዜ አንስቶ ሲከበር ቆይቷል።
- ፊቼ ጨምበላላ በዓል የሚከበርበት ቋሚ ቀን የለውም። በአያንቱዎች ጥቆማ መሰረት በዓሉ የሚከበርበት ቀን ይቆረጣል።
- 'የፊቼ ጨምበላላ ዋነኛ ትርጉም ሰላም ነው'፤ አንድነትና ፍቅር የበዓሉ መለያ ነው።
- የተጣሉ ሰዎች በፊቼ ጨምበላላ በዓል ላይ ይታረቃሉ። ሃዘን ላይ የነበሩ ሰዎችም የሃዘን ልብሳቸውን ይቀይራሉ።
- ከቀዬው ርቆ የነበረ ሰው ለፊቼ ጨምበላላ ወደቀዬው ይመለሳል።
- ለዚህ በዓል ተብሎ እርድ አይፈጸምም፤ ስጋም አይበላም። ክብቶችን መምታትም ክልክል ነው። ላሞች ሳር የበዛበት መስክ ላይ ይሰማራሉ።
- በሲዳማ ሕዝብ ዘንድ በፊቼ ጨምበላላ በዓል ወቅት ማረስ ነውር ነው። ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የፊቼ ጨምበላላ በዓል የሲዳማ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮም ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው።
- ፊቼ የአዲስ ዓመት በዓል ዋዜማ ሲሆን፤ ጨምበላላ ደግሞ የአዲስ ዓመት መጀመሪያው ቀን ነው።
- ሲዳማ ከአንድ ዓመት ወደሌላው የሚሸጋገርበት ሂደት ሁሉቃ ይባላል። ሁሉቃ ማለት ከሸምበቆና ከአርጥብ ቅጠል ተሠርቶ የሚቆም ነገር ነው። ሁሉቃ በቤተሰብና በማኅበረሰብ ደረጃ የሚሠራ ሲሆን፤ አዲስ ዓመት ሲገባ ሰዎችና ከብቶች ይተላለፉበታል።
- የሲዳማ ሕዝብ አዲስ ዓመትን ሲቀበሉ፤ ዓመቱ የብልጽግና እንዲሆንላቸው 'ፊቼ ጄጂ' ይላሉ።
ይህ መረጃ የቀረበው ከ2019 የቢቢሲ ድረገፅ ላይ ከወጣው ፅሁፍ ነው።
@tikvahethiopia
" ማንም አገር አለኝ የማይለው የጦር መሣሪያ አለን፡፡…አስፈላጊ ከሆነ እንጠቀመዋለን " - ቭላድሚር ፑቲን
የሩሲያው መሪ ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ጦርነት እጁን የሚያስገባ ማንኛውም አገር ላይ መብረቃዊ ጥቃት እንደሚፈጸምበት አስጠነቀቁ፡፡
ይህን ለማድረግ ደግሞ አገራቸው ሩሲያ አቅምም ብቃትም አላት ብለዋል፡፡
‹‹ማንም አገር አለኝ የማይለው የጦር መሣሪያ አለን፡፡…አስፈላጊ ከሆነ እንጠቀመዋለን›› ሲሉ ብዙዎችን ያሳሰበ ንግግር አድርገዋል፡፡
አንዳንድ ተንታኞች ፑቲን በዚህ ንግግራቸው ለመጠቆም የሞከሩት ባለስቲክ ሚሳኤልና የኑክሊየር መሣሪያን ነው በማለት ግምት ወስደዋል፡፡
ፑቲን ከዚህ በፊት በለጦር ሹማምንቶቻቸው የኑክሊየር መሣሪያ በተጠንቀቅ እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡
የፑቲን መራር ንግግር የተሰማው ምዕራባዊያን ለዩክሬን እጅግ ውስብስብና ዘመናዊ መሣሪያዎችን በመስጠት በተጠመዱበት ወቅት ነው።
በተለይም ባለፉት ቀናት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን እና የመከላከያ ሚኒስትሩ ኦስቲን በኪየቭ ጉብኝት አድርገው ነበር።
በዚህ ጉብኝታቸው ለዩክሬን ወደ 700 ሚሊዮን ዶላር የተጠጋ እርዳታን ይፋ አድርገዋል፡፡
ከትናንት በስቲያ የምዕራብ አገራት በጀርመን ተሰብስበው ለዩክሬን የሚደረገውን የጦር መሣሪያ እርዳታ እንዴት ከዚህም በላቀ መልኩ ማሳደግ ይቻላል በሚል ተወያይተው ነበር፡፡
በጦርነት ጣልቃ ያለመግባት ጥብቅ ፖሊሲን ትከተል የነበረችው ጀርመን ሳይቀር ያልተጠበቀ የፖሊሲ ለውጥ በማድረግ ለዩክሬን 50 የአየር መቃወሚያ ታንኮችን እሰጣለሁ ብላለች፡፡
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
የሩሲያው መሪ ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ጦርነት እጁን የሚያስገባ ማንኛውም አገር ላይ መብረቃዊ ጥቃት እንደሚፈጸምበት አስጠነቀቁ፡፡
ይህን ለማድረግ ደግሞ አገራቸው ሩሲያ አቅምም ብቃትም አላት ብለዋል፡፡
‹‹ማንም አገር አለኝ የማይለው የጦር መሣሪያ አለን፡፡…አስፈላጊ ከሆነ እንጠቀመዋለን›› ሲሉ ብዙዎችን ያሳሰበ ንግግር አድርገዋል፡፡
አንዳንድ ተንታኞች ፑቲን በዚህ ንግግራቸው ለመጠቆም የሞከሩት ባለስቲክ ሚሳኤልና የኑክሊየር መሣሪያን ነው በማለት ግምት ወስደዋል፡፡
ፑቲን ከዚህ በፊት በለጦር ሹማምንቶቻቸው የኑክሊየር መሣሪያ በተጠንቀቅ እንዲዘጋጅ ትዕዛዝ መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡
የፑቲን መራር ንግግር የተሰማው ምዕራባዊያን ለዩክሬን እጅግ ውስብስብና ዘመናዊ መሣሪያዎችን በመስጠት በተጠመዱበት ወቅት ነው።
በተለይም ባለፉት ቀናት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን እና የመከላከያ ሚኒስትሩ ኦስቲን በኪየቭ ጉብኝት አድርገው ነበር።
በዚህ ጉብኝታቸው ለዩክሬን ወደ 700 ሚሊዮን ዶላር የተጠጋ እርዳታን ይፋ አድርገዋል፡፡
ከትናንት በስቲያ የምዕራብ አገራት በጀርመን ተሰብስበው ለዩክሬን የሚደረገውን የጦር መሣሪያ እርዳታ እንዴት ከዚህም በላቀ መልኩ ማሳደግ ይቻላል በሚል ተወያይተው ነበር፡፡
በጦርነት ጣልቃ ያለመግባት ጥብቅ ፖሊሲን ትከተል የነበረችው ጀርመን ሳይቀር ያልተጠበቀ የፖሊሲ ለውጥ በማድረግ ለዩክሬን 50 የአየር መቃወሚያ ታንኮችን እሰጣለሁ ብላለች፡፡
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
#UNICEF #ETHIOPIA
ትላንት ፕሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የዩኒሴፍ ኤግዜኩቲቭ ዳይሬክትር የሆኑትን ካትሪን ራስል በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
የጉብኝታቸው ዋና ዓላማ በአገራችን በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ አደጋ የተጎዱ በርካታ ሕጻናትን ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ለማየትና ለመርዳት የሚያስችላቸውን የዓለም አቀፍ ከፍተኛ ድጋፍ ለማስገኘት ነው ተብሏል።
ዩኒሴፍ በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የመስክ ሥራ ልምድ ያለው ሲሆን ግንኙነቱን በማሻሻልና በመጠናከር መሠራት እንዳለበት ፕሬዚደንቷ ገልጸዋል።
ካትሪን ራስል ከሶስት ወር በፊት ነው የዩኒሴፍ ኤግዜኩቲቭ ዳይሬክትር የሆነው የተሾሙት።
ምንጭ፦ የፕሬዜዳንት ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
ትላንት ፕሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የዩኒሴፍ ኤግዜኩቲቭ ዳይሬክትር የሆኑትን ካትሪን ራስል በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
የጉብኝታቸው ዋና ዓላማ በአገራችን በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ አደጋ የተጎዱ በርካታ ሕጻናትን ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ለማየትና ለመርዳት የሚያስችላቸውን የዓለም አቀፍ ከፍተኛ ድጋፍ ለማስገኘት ነው ተብሏል።
ዩኒሴፍ በኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የመስክ ሥራ ልምድ ያለው ሲሆን ግንኙነቱን በማሻሻልና በመጠናከር መሠራት እንዳለበት ፕሬዚደንቷ ገልጸዋል።
ካትሪን ራስል ከሶስት ወር በፊት ነው የዩኒሴፍ ኤግዜኩቲቭ ዳይሬክትር የሆነው የተሾሙት።
ምንጭ፦ የፕሬዜዳንት ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
በዚህ ሩጫ በበዛበት ዘመን የተለያዩ የአገልግሎት ክፍያዎችን ካሉበት ሆነው ለመክፈል የአቢሲንያ ባንክ ሞባይል ባንኪንግ አይነተኛ አማራጭ ነው። በአቢሲንያ የሞባይል ባንኪንግ የዲኤስ ቲቪ፣ የኢትዮ ቴሌኮም፣ የዌብ ስፕሪክስ ኢንተርኔት ክፍያ፣ የትምህርት ቤት እና የተለያዩ አይነት የአገልግሎት ክፍያዎችን በቀላሉ ይክፈሉ!
የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻነል ይቀላቀሉ! https://yangx.top/BoAEth
በዚህ ሩጫ በበዛበት ዘመን የተለያዩ የአገልግሎት ክፍያዎችን ካሉበት ሆነው ለመክፈል የአቢሲንያ ባንክ ሞባይል ባንኪንግ አይነተኛ አማራጭ ነው። በአቢሲንያ የሞባይል ባንኪንግ የዲኤስ ቲቪ፣ የኢትዮ ቴሌኮም፣ የዌብ ስፕሪክስ ኢንተርኔት ክፍያ፣ የትምህርት ቤት እና የተለያዩ አይነት የአገልግሎት ክፍያዎችን በቀላሉ ይክፈሉ!
የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻነል ይቀላቀሉ! https://yangx.top/BoAEth
" ትውልዱ የፊቼ ጨምበላላን ትርጓሜና እሴቶቹን መገንዘብ ያስፈልገዋል " - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሲዳማ ዘመን መለወጫ በዓል ለሆነው ለፊቼ ጨምበላላ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
ዶ/ር ዐቢይ በሲዳምኛ ቋንቋ /Sidaamu Afoo/ ባስተላለፉት መልእክት ፤ በዚህ ዘመን ያለው ትውልድ የፊቼ ጨምበላላን ትርጓሜና እሴቶቹ ሰላም ፤ ፍቅር እና አንድነት መሆኑን ትምህርት መውሰድ ወይንም መገንዘብ እንደሚያስፈልገው አሳስበዋል።
#ኢብኮ
@tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሲዳማ ዘመን መለወጫ በዓል ለሆነው ለፊቼ ጨምበላላ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
ዶ/ር ዐቢይ በሲዳምኛ ቋንቋ /Sidaamu Afoo/ ባስተላለፉት መልእክት ፤ በዚህ ዘመን ያለው ትውልድ የፊቼ ጨምበላላን ትርጓሜና እሴቶቹ ሰላም ፤ ፍቅር እና አንድነት መሆኑን ትምህርት መውሰድ ወይንም መገንዘብ እንደሚያስፈልገው አሳስበዋል።
#ኢብኮ
@tikvahethiopia
#ፊቼ_ጨምበላላ
የሲዳማ የዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምባላላ በዓል እየተከበረ ይገኛል።
ዛሬ በዓሉ በሲምፖዚየምና ሌሎች ዝግጅቶች በሀዋሳ ተከብሯል።
በሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደው ሲምፖዚየም ላይ የፊቼ ጫምባላላ ባህላዊ እሴቶች ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርቧል።
በዛሬው የበዓሉ ዋዜማ የ ”ሻፌታ” ሥነ-ሥርዓትን ጨምሮ ሌሎችም ዝግጅቶች ነበሩ።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳና የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎና የዞን አመራሮች ተገኝተው ነበር።
በተጨማሪ የመጀመሪያው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ፣ አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤና አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ታድመው እንደነበር ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
የሲዳማ የዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምባላላ በዓል እየተከበረ ይገኛል።
ዛሬ በዓሉ በሲምፖዚየምና ሌሎች ዝግጅቶች በሀዋሳ ተከብሯል።
በሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደው ሲምፖዚየም ላይ የፊቼ ጫምባላላ ባህላዊ እሴቶች ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርቧል።
በዛሬው የበዓሉ ዋዜማ የ ”ሻፌታ” ሥነ-ሥርዓትን ጨምሮ ሌሎችም ዝግጅቶች ነበሩ።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳና የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎና የዞን አመራሮች ተገኝተው ነበር።
በተጨማሪ የመጀመሪያው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ፣ አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤና አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ታድመው እንደነበር ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethiopia
#ATTENTION📣
የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል ፤ በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ ከቀብር ስፍራ ጋር በተያያዘ በክርስትና እና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተቀሰቀሰውን ግጭት መነሻ በማድረግ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎችም በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር ጸረ-ኢትዮጵያ የሆኑ ሃይሎችን ፍላጎት ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አስታወቋል፡፡
በጎንደር በተከሰተው ግጭት የተሳተፉና ሁከቱን ለማባባስ የተንቀሳቀሱ 280 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን አመልክቷል፡፡
በጎንደር የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በሌሎች አካባቢዎች በተለያዩ እምነት ተከታዮች መካከል ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር የሚጋብዙ ቅስቀሳዎች እንዲሁም ሃሰተኛ መረጃዎች በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ ሲል ጠቁሟል።
በአንዳንድ አካባቢዎችም የእምነት ተቋማትና ግለሰቦች ላይ ጥቃት በመፈጸም ግጭቱ ሃገራዊ ቅርጽ እንዲኖረው ሙከራ እየተደረገ ነው ብሏል።
የፌደራል የደህንትና የጸጥታ መዋቅር በድርጊቱ በሚሳተፉት ላይ ብቻ ሳይሆን ከኋላ በመሆን በሚዘውሩት ላይ በቂ መረጃና ማስረጃ ያለው በመሆኑ ተከታታይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ አስታውቋል።
ችግሩ ወደ ሌሎች አካባቢዎችም እንዲስፋፋ በየትኛውም የመገናኛ ዘዴ የሚቀሰቅሱ፤ በተለይ ደግሞ የማህበራዊ ትስስር ገፆችን በመጠቀም ሃሰተኛና የጥላቻ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት በህግ የሚጠየቁበት አግባብ መኖሩን የጋራ ግብረ ኃይሉ የጠቆመ ሲሆን በዚህ ህግወጥ ድርጊት የሚሳተፉ ባስቸኳይ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ በጥብቅ አስጠንቅቋል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የፌደራል የደህንነትና የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል ፤ በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ ከቀብር ስፍራ ጋር በተያያዘ በክርስትና እና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የተቀሰቀሰውን ግጭት መነሻ በማድረግ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎችም በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር ጸረ-ኢትዮጵያ የሆኑ ሃይሎችን ፍላጎት ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አስታወቋል፡፡
በጎንደር በተከሰተው ግጭት የተሳተፉና ሁከቱን ለማባባስ የተንቀሳቀሱ 280 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን አመልክቷል፡፡
በጎንደር የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ በሌሎች አካባቢዎች በተለያዩ እምነት ተከታዮች መካከል ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር የሚጋብዙ ቅስቀሳዎች እንዲሁም ሃሰተኛ መረጃዎች በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ ሲል ጠቁሟል።
በአንዳንድ አካባቢዎችም የእምነት ተቋማትና ግለሰቦች ላይ ጥቃት በመፈጸም ግጭቱ ሃገራዊ ቅርጽ እንዲኖረው ሙከራ እየተደረገ ነው ብሏል።
የፌደራል የደህንትና የጸጥታ መዋቅር በድርጊቱ በሚሳተፉት ላይ ብቻ ሳይሆን ከኋላ በመሆን በሚዘውሩት ላይ በቂ መረጃና ማስረጃ ያለው በመሆኑ ተከታታይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ አስታውቋል።
ችግሩ ወደ ሌሎች አካባቢዎችም እንዲስፋፋ በየትኛውም የመገናኛ ዘዴ የሚቀሰቅሱ፤ በተለይ ደግሞ የማህበራዊ ትስስር ገፆችን በመጠቀም ሃሰተኛና የጥላቻ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት በህግ የሚጠየቁበት አግባብ መኖሩን የጋራ ግብረ ኃይሉ የጠቆመ ሲሆን በዚህ ህግወጥ ድርጊት የሚሳተፉ ባስቸኳይ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ በጥብቅ አስጠንቅቋል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#ትኩረት📣
" በእምነት ተቋማት ላይና በንፁሀን ላይ የሚፈጸመው ሕገ ወጥ ድርጊት በአስቸኳይ ይቆም ዘንድ ሁሉም የሚመለከተው አካል ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል " - የሐዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት
ዛሬ የወራቤ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ላይ ምዝበራና ውድመት መፈፀሙን የሐዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት አስታውቋል።
ድርጊቱ የተፈፀመው በአክራሪዎች እና ፅንፈኛ ኃይሎች ነው ብሏል።
እኚሁ ኃይሎች የደብሩን በር እንዲሁም ደግሞ መስኮት መሰባበራቸውን እና የጉልላት መንበሩን እንደገለበጡ ሀገረ ስብከቱ አሳውቋል።
የሐዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ባወቀ ለኢኦተቤ ቴቪ በሰጡት ቃል ፤ " አክራሪና ጽንፈኛ ቡድኖች የደብሩን የጀነሬተር ቤትና የጥበቃ ቤት አቃጥለዋል " ብለዋል ።
አገልጋዮች እና የጥበቃ ሰራተኞች ላይ ድብደባ የተፈፀመ ሲሆን ፤ የክርስቲያን ሆቴሎች ላይም ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በስልጤ ዞን ሳንኩራ ቅ/ ገብርኤል ቤተክርስቲያ ሙሉ በሙሉ ቃጠሎ መውደሙ ተገልጿል።
ሀገረ ስብከቱ ፤ ይህ ሁሉ ጥፋት ሲደርስ የሚያስቆም የዞን ኃይል ባለመኖሩ እጅግ እዳዘነ ገልጿል።
መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ፤ ከርዕሰ ከተማው ወራቤ ውጪ በሳንኩራ፣ ቂልጡ፣ ቅበት፣ ሌራ፣ ዳሎቻ፣ ቄራ በተባሉ አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ምእመናንንና አብያተክርስቲያናትን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
በጎንደር ከተማ ላይ የተከሰተውን ችግር ተከትሎ ችግሩን ለማስፋትና አጋጣሚውን ለሌላ ሁከት መጠቀም በእምነት ተቋማት ላይና በንፁሀን ላይ የሚፈጸመው ሕገ ወጥ ድርጊት በአስቸኳይ ይቆም ዘንድ ሁሉም የሚመለከተው አካል ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ተብሏል።
@tikvahethiopia
" በእምነት ተቋማት ላይና በንፁሀን ላይ የሚፈጸመው ሕገ ወጥ ድርጊት በአስቸኳይ ይቆም ዘንድ ሁሉም የሚመለከተው አካል ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል " - የሐዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት
ዛሬ የወራቤ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ላይ ምዝበራና ውድመት መፈፀሙን የሐዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት አስታውቋል።
ድርጊቱ የተፈፀመው በአክራሪዎች እና ፅንፈኛ ኃይሎች ነው ብሏል።
እኚሁ ኃይሎች የደብሩን በር እንዲሁም ደግሞ መስኮት መሰባበራቸውን እና የጉልላት መንበሩን እንደገለበጡ ሀገረ ስብከቱ አሳውቋል።
የሐዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ባወቀ ለኢኦተቤ ቴቪ በሰጡት ቃል ፤ " አክራሪና ጽንፈኛ ቡድኖች የደብሩን የጀነሬተር ቤትና የጥበቃ ቤት አቃጥለዋል " ብለዋል ።
አገልጋዮች እና የጥበቃ ሰራተኞች ላይ ድብደባ የተፈፀመ ሲሆን ፤ የክርስቲያን ሆቴሎች ላይም ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በስልጤ ዞን ሳንኩራ ቅ/ ገብርኤል ቤተክርስቲያ ሙሉ በሙሉ ቃጠሎ መውደሙ ተገልጿል።
ሀገረ ስብከቱ ፤ ይህ ሁሉ ጥፋት ሲደርስ የሚያስቆም የዞን ኃይል ባለመኖሩ እጅግ እዳዘነ ገልጿል።
መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ፤ ከርዕሰ ከተማው ወራቤ ውጪ በሳንኩራ፣ ቂልጡ፣ ቅበት፣ ሌራ፣ ዳሎቻ፣ ቄራ በተባሉ አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ምእመናንንና አብያተክርስቲያናትን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
በጎንደር ከተማ ላይ የተከሰተውን ችግር ተከትሎ ችግሩን ለማስፋትና አጋጣሚውን ለሌላ ሁከት መጠቀም በእምነት ተቋማት ላይና በንፁሀን ላይ የሚፈጸመው ሕገ ወጥ ድርጊት በአስቸኳይ ይቆም ዘንድ ሁሉም የሚመለከተው አካል ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ተብሏል።
@tikvahethiopia