2021.04.19_MUSE_REPORT.pdf
1.3 MB
#ሪፖርት
በሩዋንዳ በ100 ቀን ውስጥ ብቻ 800 ሺህ ገደማ ቱትሲዎች በተጨፈጨፉበት የ1994ቱ የሩዋንዳ ጭፍጨፋ ፈረንሳይ የተባባሪነት ሚና እንደነበራት የሚያመለክት የምርመራ ሪፖርት ይፋ ሆነ፡፡
የምርመራ ሪፖርቱ ይፋ የሆነው በሩዋንዳ መንግስት ቀጣሪነት ምርመራውን ባካሄደው ‘ሌቪ ፋይር ስቶን ሚዩዝ’ በተባለ አሜሪካዊ የምርመራ ተቋም ነው፡፡
ተቋሙ እ.ኤ.አ ከ2017 ጀምሮ ላለፉት 5 ዓመታት ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ የመጨረሻ ውጤት ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡
ሪፖርቱ ይፋ የሆነው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ በመሩት እና ዛሬ በተካሄደ ልዩ የሃገሪቱ ካቢኔ ስብሰባ ነው፡፡
ቦቢ ሚዩዝ የተባሉት የመርማሪው ተቋም ባልደረባም ፥ “A Foreseeable Genocide: The Role of the French Government in Connection with the Genocide against the Tutsi” በሚል ርዕስ የተካሄደውን ምርመራ የመጨረሻ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡
ከ600 ገጾች በላይ ጥንቅር በሆነ ሪፖርቱ ፈረንሳይ ቱትሲዎች ሰለባ በሆኑበት ጭፍጨፋ የ ‘ተባባሪነት ሚና’ እንደነበራት አስቀምጧል፡፡
“ተገማች የነበረው ጭፍጨፋ እውን እንዲሆን ፈረንሳይ ‘የጎላ ሚና’ ነበራት ነው ሪፖርቱ ያለው፡፡ ይህን ሪፖርት ለማጠናቀር በሚሊዬን የሚቆጠሩ የሰነድ ማስረጃዎች ተመርምረዋል፡፡ የ250 ምስክሮች ቃል ተደምጧል፡፡
#Republic_of_Rwanda #AlAIN
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በሩዋንዳ በ100 ቀን ውስጥ ብቻ 800 ሺህ ገደማ ቱትሲዎች በተጨፈጨፉበት የ1994ቱ የሩዋንዳ ጭፍጨፋ ፈረንሳይ የተባባሪነት ሚና እንደነበራት የሚያመለክት የምርመራ ሪፖርት ይፋ ሆነ፡፡
የምርመራ ሪፖርቱ ይፋ የሆነው በሩዋንዳ መንግስት ቀጣሪነት ምርመራውን ባካሄደው ‘ሌቪ ፋይር ስቶን ሚዩዝ’ በተባለ አሜሪካዊ የምርመራ ተቋም ነው፡፡
ተቋሙ እ.ኤ.አ ከ2017 ጀምሮ ላለፉት 5 ዓመታት ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ የመጨረሻ ውጤት ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡
ሪፖርቱ ይፋ የሆነው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ በመሩት እና ዛሬ በተካሄደ ልዩ የሃገሪቱ ካቢኔ ስብሰባ ነው፡፡
ቦቢ ሚዩዝ የተባሉት የመርማሪው ተቋም ባልደረባም ፥ “A Foreseeable Genocide: The Role of the French Government in Connection with the Genocide against the Tutsi” በሚል ርዕስ የተካሄደውን ምርመራ የመጨረሻ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡
ከ600 ገጾች በላይ ጥንቅር በሆነ ሪፖርቱ ፈረንሳይ ቱትሲዎች ሰለባ በሆኑበት ጭፍጨፋ የ ‘ተባባሪነት ሚና’ እንደነበራት አስቀምጧል፡፡
“ተገማች የነበረው ጭፍጨፋ እውን እንዲሆን ፈረንሳይ ‘የጎላ ሚና’ ነበራት ነው ሪፖርቱ ያለው፡፡ ይህን ሪፖርት ለማጠናቀር በሚሊዬን የሚቆጠሩ የሰነድ ማስረጃዎች ተመርምረዋል፡፡ የ250 ምስክሮች ቃል ተደምጧል፡፡
#Republic_of_Rwanda #AlAIN
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#ሪፖርት
በአማራ ክልል "ሰሜን ሸዋ ዞን" በቅርቡ በተከሰተው የፀጥታ መደፍረስ አካባቢውን መልሶ ለማቋቋም በክልል ደረጃ የተዋቀረው የቴክኒክ ኮሚቴ የምልከታ ሪፖርቱን ለአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ አቅርቦ ነበር።
በሪፖርቱ መሰረት ፦
- በሰሜን ሸዋ 3 ወረዳዎች ብቻ 281 ሰዎች ተገድለዋል።
- 197 ዜጎች ላይ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።
- 246 ሺህ 818 ሰዎች እርዳታ ፈላጊ ሆነዋል ፤ 9,661 ዜጎች ከመኖሪያ አካባቢያቸው ተፈናቅለዋል።
- በሸዋ ሮቢት፣ ቀወትና ኤፍራታ ግድም 4 ትምህርት ቤቶች ወድመዋል፤ 7 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ንብረታቸው ወድሟል።
- ሶስት የጤና ተቋማት ወድመዋል፤ አንድ ጤና ተቋም ተዘርፏል።
- 7 የእምነት ተቋማት ተቃጥለዋል።
- የውሃ መሰረተ ልማቶች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል።
- አስራ አንድ ሆቴሎች እና አርባ ዘጠኝ የግል መጋዘኖች ተቃጥለዋል።
- እንስሳት መዘረፋቸውና የግብርና መሰረተ ልማቶች ላይ የከፋ ጉዳት ደርሷል።
- የተጎዱ ዜጎችን ለማቋቋምና አካባቢውን መልሶ ለመገንባት ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል።
በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የደረሰውን ጉዳት የቴክኒክ ኮሚቴው እያጠናው የሚገኝ ሲሆን ባጭር ጊዜ ሪፖርቱን ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል "ሰሜን ሸዋ ዞን" በቅርቡ በተከሰተው የፀጥታ መደፍረስ አካባቢውን መልሶ ለማቋቋም በክልል ደረጃ የተዋቀረው የቴክኒክ ኮሚቴ የምልከታ ሪፖርቱን ለአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ አቅርቦ ነበር።
በሪፖርቱ መሰረት ፦
- በሰሜን ሸዋ 3 ወረዳዎች ብቻ 281 ሰዎች ተገድለዋል።
- 197 ዜጎች ላይ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።
- 246 ሺህ 818 ሰዎች እርዳታ ፈላጊ ሆነዋል ፤ 9,661 ዜጎች ከመኖሪያ አካባቢያቸው ተፈናቅለዋል።
- በሸዋ ሮቢት፣ ቀወትና ኤፍራታ ግድም 4 ትምህርት ቤቶች ወድመዋል፤ 7 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ንብረታቸው ወድሟል።
- ሶስት የጤና ተቋማት ወድመዋል፤ አንድ ጤና ተቋም ተዘርፏል።
- 7 የእምነት ተቋማት ተቃጥለዋል።
- የውሃ መሰረተ ልማቶች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል።
- አስራ አንድ ሆቴሎች እና አርባ ዘጠኝ የግል መጋዘኖች ተቃጥለዋል።
- እንስሳት መዘረፋቸውና የግብርና መሰረተ ልማቶች ላይ የከፋ ጉዳት ደርሷል።
- የተጎዱ ዜጎችን ለማቋቋምና አካባቢውን መልሶ ለመገንባት ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል።
በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የደረሰውን ጉዳት የቴክኒክ ኮሚቴው እያጠናው የሚገኝ ሲሆን ባጭር ጊዜ ሪፖርቱን ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። #ኢብኮ
@tikvahethiopia
#ሪፖርት
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን በተመለከተ ቃላቸውን ሰጥተውናል።
በአጠቅላይ ምርጫው ሰላማዊ መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ፣ የተለያየ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውድድሩን ህግ በማክበር ፍፁም ነው ባይባልም የተሻለ ውድድር ስሜት የተፈጠረበት እና የህዝብ መነሳሳት የታየበት አበረታች የሚባል ሂደት ነበር ብለዋል።
ነገር ግን ምርጫው እንከን አልባ እና ፍፁም ነበር ማለት እንዳልሆነ ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ አሳውቀውናል።
ምርጫው ላይ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ እንደሆነም አንስተዋል።
ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ ፥ "የትኛውም ምርጫ ፍፁም ሆኖም አያውቅም፣ ሊሆንም አይችልም፤ ምርጫ ሂደት ነው የምንማርበት ነው ከዚህ ምርጫ የተሻለ አፈፃፀም ደግሞ በሚቀጥለው ይታያል ብዬ አስባለሁ" ብለዋል።
* የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን በተመለከተ ቃላቸውን ሰጥተውናል።
በአጠቅላይ ምርጫው ሰላማዊ መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ፣ የተለያየ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውድድሩን ህግ በማክበር ፍፁም ነው ባይባልም የተሻለ ውድድር ስሜት የተፈጠረበት እና የህዝብ መነሳሳት የታየበት አበረታች የሚባል ሂደት ነበር ብለዋል።
ነገር ግን ምርጫው እንከን አልባ እና ፍፁም ነበር ማለት እንዳልሆነ ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ አሳውቀውናል።
ምርጫው ላይ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ እንደሆነም አንስተዋል።
ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ ፥ "የትኛውም ምርጫ ፍፁም ሆኖም አያውቅም፣ ሊሆንም አይችልም፤ ምርጫ ሂደት ነው የምንማርበት ነው ከዚህ ምርጫ የተሻለ አፈፃፀም ደግሞ በሚቀጥለው ይታያል ብዬ አስባለሁ" ብለዋል።
* የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Joint_Report_of_the_EHRC_OHCHR_Joint_Investigations_on_Human_Rights.pdf
#ሪፖርት
በትግራይ ግጭት ሁሉም አካላት ሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ፈፅመው መገኘታቸውን የጋራ ሪፖርቱ አመላክቷል።
ተፈፅመዋል የተባሉ ጥሰቶች ፦
• ከሕግ ውጪ ግድያና ርሸና፣
• ማሰቃየት፣
• ወሲባዊና ጾታዊ ጥቃቶች፣
• በስደተኞች ላይ የተፈጸሙ ግፎች እንዲሁም ሰላማዊ ሰዎችን በኃይል ማፈናቀል ይገኙበታል።
በጋራ የምርመራ ሪፖርቱ ከቀረቡት ክስተቶች መካካል በጥቂቱ ፦
በማይካድራ "ሳምረ" በተባለ ቡድን የተፈጸመ ጥቃት ይገኝበታል ፤ ምንም እንኳን ቁጥሩን እርግጠኛ ለመሆን ባይቻልም ከ200 በላይ ሰዎች በዚህ ጥቃት ተገድለው በጅምላ መቃብሮች መቀበራቸውን ተመላክቷል።
የመከላከያ ሠራዊት እና የአማራ ልዩ ኃይል ከተማውን በተቆጣጠሩባቸው ቀጣይ ቀናት የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የማይካድራ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የበቀል ግድያዎች መፈጸማቸውን እና የፋኖ ሚሊሺያዎችም በግድያው መሳተፋቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል።
በአክሱም ከተማ የኤርትራ ሠራዊት አባላት ከ100 በላይ ሲቪሎችን መግደላቸውን፤ በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ግድያዎቹ ሲፈጸሙ ጣልቃ ሳይገቡ መቅረታቸውን ሪፖርቱ ገልጿል።
በቦራ አምደውሃ ፣ በቦራ ጫማላ እና ማኢ ሊሃም ከተሞች ከ70 በላይ ሲቪሎች በመከላከያ ሠራዊት መገደላቸውን የጋራ ሪፖርቱ ገልጿል።
እነዚህን እና ሌሎች የግድያ ማስረጃዎችን በመያዝ የሕግ ትንታኔ የሰጠው የምርመራ ቡድኑ በዚህ ጦርነት ውስጥ "የጦር ወንጀሎች" ተፈጽመው ሊሆን እንደሚችል ጠቁሟል።
#EHRC #OHCHR
@tikvahethiopia
በትግራይ ግጭት ሁሉም አካላት ሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ፈፅመው መገኘታቸውን የጋራ ሪፖርቱ አመላክቷል።
ተፈፅመዋል የተባሉ ጥሰቶች ፦
• ከሕግ ውጪ ግድያና ርሸና፣
• ማሰቃየት፣
• ወሲባዊና ጾታዊ ጥቃቶች፣
• በስደተኞች ላይ የተፈጸሙ ግፎች እንዲሁም ሰላማዊ ሰዎችን በኃይል ማፈናቀል ይገኙበታል።
በጋራ የምርመራ ሪፖርቱ ከቀረቡት ክስተቶች መካካል በጥቂቱ ፦
በማይካድራ "ሳምረ" በተባለ ቡድን የተፈጸመ ጥቃት ይገኝበታል ፤ ምንም እንኳን ቁጥሩን እርግጠኛ ለመሆን ባይቻልም ከ200 በላይ ሰዎች በዚህ ጥቃት ተገድለው በጅምላ መቃብሮች መቀበራቸውን ተመላክቷል።
የመከላከያ ሠራዊት እና የአማራ ልዩ ኃይል ከተማውን በተቆጣጠሩባቸው ቀጣይ ቀናት የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የማይካድራ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የበቀል ግድያዎች መፈጸማቸውን እና የፋኖ ሚሊሺያዎችም በግድያው መሳተፋቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል።
በአክሱም ከተማ የኤርትራ ሠራዊት አባላት ከ100 በላይ ሲቪሎችን መግደላቸውን፤ በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ግድያዎቹ ሲፈጸሙ ጣልቃ ሳይገቡ መቅረታቸውን ሪፖርቱ ገልጿል።
በቦራ አምደውሃ ፣ በቦራ ጫማላ እና ማኢ ሊሃም ከተሞች ከ70 በላይ ሲቪሎች በመከላከያ ሠራዊት መገደላቸውን የጋራ ሪፖርቱ ገልጿል።
እነዚህን እና ሌሎች የግድያ ማስረጃዎችን በመያዝ የሕግ ትንታኔ የሰጠው የምርመራ ቡድኑ በዚህ ጦርነት ውስጥ "የጦር ወንጀሎች" ተፈጽመው ሊሆን እንደሚችል ጠቁሟል።
#EHRC #OHCHR
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ... ድርጊቶቹ ከሞራል ወይም ከሰብዓዊነት ያፈነገጡ ናቸው " - አምነስቲ ኢንተርናሽናል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር የህወሓት ታጣቂዎች በአማራ ክልል የነፋስ መውጫ ከተማ ላይ ጥቃት በፈጸሙበት ጊዜ የአስገድዶ መድፈር፣ ዘረፋ እና አካላዊ ጥቃቶች በነዋሪዎች ላይ መፈጸማቸውን ገለጸ። አምነስቲ ባወጣው ሪፖርት በከተማዋ ነዋሪ የሆኑና ያናገራቸው 16 ሴቶች በህወሓት አማጺያን የአስገድዶ…
#ሪፖርት
አምነስቲ ኢንተርናሽናል የህወሓት ታጣቂዎች በአማራ ክልል የነፋስ መውጫ ከተማ ላይ ጥቃት በፈጸሙበት ጊዜ ከአስገድዶ መድፈር ፣ ዘረፋ እና አካላዊ ጥቃቶች በተጨማሪ አዋራጅ ንግግር ሲናገሩ እንደነበር ሪፖርት አድርጓል።
አስገድዶ መደፈረ የተፈፀመባቸው ሁሉም ሴቶች ፈጻሚዎቹን ህወሓቶች መሆናቸውን መለየት የቻሉት በአነጋገር ዘያቸው እና በሚሰነዝሩት ብሔርን መሠረት ባደረገ ስድብ እንዲሁም ደግሞ በግልጽ ህወሓቶች መሆናቸውን በመናገራቸው መሆኑን ለአምነስቲ ኢንተርናሽናል ተናግረዋል።
ታጣቂዎች በሴቶቹ ላይ የአስገድዶ መድፈር ከመፈፀማቸው በተጨማሪ ሰብዓዊነትን የሚያጣጥል የብሔር ማንነታቸው ላይ ያነጣጠሩ ስድቦችንና ማዋረድን ይፈጽሙ ነበር ብሏል አምነስቲ።
በአንዳንድ ሁኔታዎች ውስጥ ደግሞ አስገድደው የሚደፍሩት በፌደራል ኃይሎች በትግራይ ሴቶች ላይ የተፈጸመውን ተመሳሳይ ድርጊት ለመበቀል መሆኑን ይናገሩ ነበር ብለዋል።
ምን ያህል ሴቶች ተደፈሩ ?
አምነስቲ ኢንተርናሽናል በንፋስ መውጫ ነዋሪ የሆኑና ያናገራቸው 16 ሴቶች በህወሓት አማጺያን የአስገድዶ መደፈር ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል።
ከአስራ ስድስቱ መካከል አስራ አራቱ በቡድን የተደፈሩ ናቸው።
አንድ ለአምነስቲ ሪፖርት ያደረጉ የክልሉ ባለሥልጣን ለአምነስቲ እንደገለጹት ደግሞ አማጺያኑ በንፋስ መውጫ ከተማ ከ70 በላይ ሴቶችን መድፈራቸው ሪፖርት አድርገዋል።
የፌደራል ፍትህ ሚኒስቴር መረጃ ደግሞ አሃዙ 73 እንደሆነ ያመለክታል።
ሙሉ ሪፖርት : https://www.amnesty.org/en/latest/news/2021/11/ethiopia-survivors-of-tplf-attack-in-amhara-describe-gang-rape-looting-and-physical-assaults/
@tikvahethiopia
አምነስቲ ኢንተርናሽናል የህወሓት ታጣቂዎች በአማራ ክልል የነፋስ መውጫ ከተማ ላይ ጥቃት በፈጸሙበት ጊዜ ከአስገድዶ መድፈር ፣ ዘረፋ እና አካላዊ ጥቃቶች በተጨማሪ አዋራጅ ንግግር ሲናገሩ እንደነበር ሪፖርት አድርጓል።
አስገድዶ መደፈረ የተፈፀመባቸው ሁሉም ሴቶች ፈጻሚዎቹን ህወሓቶች መሆናቸውን መለየት የቻሉት በአነጋገር ዘያቸው እና በሚሰነዝሩት ብሔርን መሠረት ባደረገ ስድብ እንዲሁም ደግሞ በግልጽ ህወሓቶች መሆናቸውን በመናገራቸው መሆኑን ለአምነስቲ ኢንተርናሽናል ተናግረዋል።
ታጣቂዎች በሴቶቹ ላይ የአስገድዶ መድፈር ከመፈፀማቸው በተጨማሪ ሰብዓዊነትን የሚያጣጥል የብሔር ማንነታቸው ላይ ያነጣጠሩ ስድቦችንና ማዋረድን ይፈጽሙ ነበር ብሏል አምነስቲ።
በአንዳንድ ሁኔታዎች ውስጥ ደግሞ አስገድደው የሚደፍሩት በፌደራል ኃይሎች በትግራይ ሴቶች ላይ የተፈጸመውን ተመሳሳይ ድርጊት ለመበቀል መሆኑን ይናገሩ ነበር ብለዋል።
ምን ያህል ሴቶች ተደፈሩ ?
አምነስቲ ኢንተርናሽናል በንፋስ መውጫ ነዋሪ የሆኑና ያናገራቸው 16 ሴቶች በህወሓት አማጺያን የአስገድዶ መደፈር ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል።
ከአስራ ስድስቱ መካከል አስራ አራቱ በቡድን የተደፈሩ ናቸው።
አንድ ለአምነስቲ ሪፖርት ያደረጉ የክልሉ ባለሥልጣን ለአምነስቲ እንደገለጹት ደግሞ አማጺያኑ በንፋስ መውጫ ከተማ ከ70 በላይ ሴቶችን መድፈራቸው ሪፖርት አድርገዋል።
የፌደራል ፍትህ ሚኒስቴር መረጃ ደግሞ አሃዙ 73 እንደሆነ ያመለክታል።
ሙሉ ሪፖርት : https://www.amnesty.org/en/latest/news/2021/11/ethiopia-survivors-of-tplf-attack-in-amhara-describe-gang-rape-looting-and-physical-assaults/
@tikvahethiopia
#ሪፖርት
ከቀናት በፊት የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር /TPLF/ ታጣቂዎች በአማራ ክልል ውስጥ የፈፀሟቸውን ግፎች በሪፖርቱ ያሳወቀው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ትላንት ሌላ ኢትዮጵያን የሚመለከት ሪፖርት ይዞ ወጥቷል።
ይኸው ሪፖርት በአዲስ አበባ ከተማ የትግራይ ተወላጆችን ትኩረት ያደረገ እስር እየተካሄደ መሆኑን የሚገልፅ ነው።
አምነስቲ በዚህ ሳምንት በኢትዮጵያ ጉዳይ ሪፖርት ሲያቀርብ ይህ 2ኛው ነው።
አምነስቲ በትላንት ሪፖርቱ በአ/አ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ላይ ያነጣጠረ እስር እየተካሄደ ነው ፤ እስሩ የተባባሰው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ በኃላ መሆኑን ገልጿል።
ሰዎች ከቤት ወደ ቤት በሚደረግ አሰሳ በቁጥጥር ስር ይውላሉ ፤ በአዲስ አበባ የሚገኙ የፖሊስ ጣቢያዎች በመሙላታቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ የመንግስት ሰራተኞች፣ የኦርቶዶክስ ቄስ እና የህግ ጠበቃን ጨምሮ ሌሎች እስረኞች በወጣቶች ማእከላት እና ሌሎች መደበኛ ባልሆኑ የማቆያ ጣቢያዎች ታስረዋል ብሏል አምነስቲ ኢንተርናሽናል።
ሙሉ ሪፖርቱ : https://www.amnesty.org/en/latest/news/2021/11/ethiopia-tigrayans-targeted-in-fresh-wave-of-ethnically-motivated-detentions-in-addis-ababa/
ከቀናት በፊት #ኢሰመኮ በአ/አ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከታወጀ ጀምሮ ሰዎች ከስራ ቦታቸው፣ ከመኖሪያ ቤታቸው እና ከመንገድ ላይ ጭምር በቁጥጥር ስር ውለው በተለያዩ የከተማዋ ፖሊስ ጣቢያዎች ተይዘው እንደሚገኙ አረጋግጫለሁ ሲል ሪፖርት ማድረጉ አይዘነጋም።
ኢሰመኮ እስሩ ማንነት/ብሄርን መሰረት ባደረገ መልኩ በሚመስል ሁኔታ መከናወኑን ማሳወቁ ይታወሳል ፤ (ምንም እንኳን በግልፅ እስሩ የቱን ብሄር መሰረት እንዳደረገ ባይገልፅም) ።
@tikvahethiopia
ከቀናት በፊት የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር /TPLF/ ታጣቂዎች በአማራ ክልል ውስጥ የፈፀሟቸውን ግፎች በሪፖርቱ ያሳወቀው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ትላንት ሌላ ኢትዮጵያን የሚመለከት ሪፖርት ይዞ ወጥቷል።
ይኸው ሪፖርት በአዲስ አበባ ከተማ የትግራይ ተወላጆችን ትኩረት ያደረገ እስር እየተካሄደ መሆኑን የሚገልፅ ነው።
አምነስቲ በዚህ ሳምንት በኢትዮጵያ ጉዳይ ሪፖርት ሲያቀርብ ይህ 2ኛው ነው።
አምነስቲ በትላንት ሪፖርቱ በአ/አ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ላይ ያነጣጠረ እስር እየተካሄደ ነው ፤ እስሩ የተባባሰው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ በኃላ መሆኑን ገልጿል።
ሰዎች ከቤት ወደ ቤት በሚደረግ አሰሳ በቁጥጥር ስር ይውላሉ ፤ በአዲስ አበባ የሚገኙ የፖሊስ ጣቢያዎች በመሙላታቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ የመንግስት ሰራተኞች፣ የኦርቶዶክስ ቄስ እና የህግ ጠበቃን ጨምሮ ሌሎች እስረኞች በወጣቶች ማእከላት እና ሌሎች መደበኛ ባልሆኑ የማቆያ ጣቢያዎች ታስረዋል ብሏል አምነስቲ ኢንተርናሽናል።
ሙሉ ሪፖርቱ : https://www.amnesty.org/en/latest/news/2021/11/ethiopia-tigrayans-targeted-in-fresh-wave-of-ethnically-motivated-detentions-in-addis-ababa/
ከቀናት በፊት #ኢሰመኮ በአ/አ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከታወጀ ጀምሮ ሰዎች ከስራ ቦታቸው፣ ከመኖሪያ ቤታቸው እና ከመንገድ ላይ ጭምር በቁጥጥር ስር ውለው በተለያዩ የከተማዋ ፖሊስ ጣቢያዎች ተይዘው እንደሚገኙ አረጋግጫለሁ ሲል ሪፖርት ማድረጉ አይዘነጋም።
ኢሰመኮ እስሩ ማንነት/ብሄርን መሰረት ባደረገ መልኩ በሚመስል ሁኔታ መከናወኑን ማሳወቁ ይታወሳል ፤ (ምንም እንኳን በግልፅ እስሩ የቱን ብሄር መሰረት እንዳደረገ ባይገልፅም) ።
@tikvahethiopia
Amhara Region Report AMHARIC.pdf
1.8 MB
#ሪፖርት
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በአማራ ክልል በጦርነት በተጎዱ አካባቢዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶችና የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶች ምርመራ ሪፖርት ይፋ አደረገ።
ኢሰመኮ በደረሱት መረጃዎች መነሻነት በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ እና ደቡብ ጎንደር ዞኖች እንዲሁም በአንዳንድ የትግራይ ክልል ደቡባዊ አካባቢዎች በጦርነት አውድ ውስጥ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች እና የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶችን በተመለከተ ከነሐሴ 22 እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2013 ዓ.ም. ምርመራ አካሂዷል።
ከላይ ምርመራው ውጤት ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በአማራ ክልል በጦርነት በተጎዱ አካባቢዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶችና የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶች ምርመራ ሪፖርት ይፋ አደረገ።
ኢሰመኮ በደረሱት መረጃዎች መነሻነት በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ እና ደቡብ ጎንደር ዞኖች እንዲሁም በአንዳንድ የትግራይ ክልል ደቡባዊ አካባቢዎች በጦርነት አውድ ውስጥ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች እና የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶችን በተመለከተ ከነሐሴ 22 እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2013 ዓ.ም. ምርመራ አካሂዷል።
ከላይ ምርመራው ውጤት ተያይዟል።
@tikvahethiopia