#FDREDefenseForce
"የመከላከያ ሠራዊት ባለፉት ዓመታት ለህዳሴ ግድቡ ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል" - የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር ኀይሉ አብርሃም እንደተናገሩት መከላከያ ሠራዊት ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ለግድቡ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ለግድቡ የጀመረውን ድጋፍም አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
መላው ኢትዮጵያውያን ለህዳሴ ግድቡ 15 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ መደገፋቸውን ያስታወሱት አቶ ኃይሉ መከላከያ ሠራዊት ሉዓላዊነትን እና ሰላም ከማረጋገጡም ባሻገር ባለፉት አስር ዓመታት ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል ብለዋል፡፡
መከላከያ ሠራዊት የግድቡን አካባቢ ከሌሎች የሰላም ኃይሎች ጋር ተቀናጅቶ በመጠበቅ ሀገራዊ አደራውን በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
ግድቡ በአሁኑ ላይ ከ80% በላይ ደርሷል፤ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ተርባይኖችም የሙከራ ምርታቸውን መስጠት እንደሚጀምሩ መግለፃቸውን የሀገር መከላከያ ሰራዊት በፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
"የመከላከያ ሠራዊት ባለፉት ዓመታት ለህዳሴ ግድቡ ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል" - የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር ኀይሉ አብርሃም እንደተናገሩት መከላከያ ሠራዊት ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ለግድቡ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ለግድቡ የጀመረውን ድጋፍም አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡
መላው ኢትዮጵያውያን ለህዳሴ ግድቡ 15 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ መደገፋቸውን ያስታወሱት አቶ ኃይሉ መከላከያ ሠራዊት ሉዓላዊነትን እና ሰላም ከማረጋገጡም ባሻገር ባለፉት አስር ዓመታት ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል ብለዋል፡፡
መከላከያ ሠራዊት የግድቡን አካባቢ ከሌሎች የሰላም ኃይሎች ጋር ተቀናጅቶ በመጠበቅ ሀገራዊ አደራውን በመወጣት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
ግድቡ በአሁኑ ላይ ከ80% በላይ ደርሷል፤ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ተርባይኖችም የሙከራ ምርታቸውን መስጠት እንደሚጀምሩ መግለፃቸውን የሀገር መከላከያ ሰራዊት በፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce
የመከላከያ ሚኒስቴር የ33ኛ ዙር ምልምል ወታደሮችን በአሁኑ ሰዓት በማስመረቅ ላይ ይገኛል።
በብርሸለቆ መሠረታዊ ውትድርና ማሠልጠኛ ት/ቤት ሲሰለጥኑ የነበሩ ወታደሮች የተሰጣቸውን ስልጠና አጠናቀዋል።
ተመራቂዎቹ ከመደበኛው ሠራዊቱ ጋር በመቀላቀልከ ውስጥ እና ከውጭ የሚቃጣን ወረራ በመመከት እንዲሁም የኢትዮጵያን አንድነት አጠናክው ያስቀጥላሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል የሀገር መከላከያ ሰራዊት አሳውቋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት
@tikvahethiopia
የመከላከያ ሚኒስቴር የ33ኛ ዙር ምልምል ወታደሮችን በአሁኑ ሰዓት በማስመረቅ ላይ ይገኛል።
በብርሸለቆ መሠረታዊ ውትድርና ማሠልጠኛ ት/ቤት ሲሰለጥኑ የነበሩ ወታደሮች የተሰጣቸውን ስልጠና አጠናቀዋል።
ተመራቂዎቹ ከመደበኛው ሠራዊቱ ጋር በመቀላቀልከ ውስጥ እና ከውጭ የሚቃጣን ወረራ በመመከት እንዲሁም የኢትዮጵያን አንድነት አጠናክው ያስቀጥላሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል የሀገር መከላከያ ሰራዊት አሳውቋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት
@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce
በአሚሶም ሴክተር 6 የሚገኘው የ5ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ ዓመታዊ የሜዳሊያ በዓሉ አከበረ።
በፕሮግራሙ ላይ የጁባ ላንድ ምክትል ፕሬዝዳት የሆኑት አቶ መሃመድ ሰይድ ተገኝተው ነበር።
ም/ፕሬዝዳት አቶ መሃመድ በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል አልሸባብን ለማጥፋት ያደረገው የግዳጅ አፈፃፀም ይበል የሚያሰኝ እንደሆነ ተናግረዋል።
አክለው ፤ ሰራዊቱ በድስፕሊኑ የታነፀ ከህዝቡ ጋር ጥሩ የሆነ ግንኙነት ያለውና በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ላሳየው ቁርጠኝነት ሜዳሊያው በክብር እንደተሰጠው ግልፀዋል።
የሴክተር 6 አዛዥ የሆኑት ብ/ጄ አበባው ሰይድ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ፣ የኬንያና የሴራሊዮን የፖሊስ ሃይል እንዲሁም የUN አጋዥ ሃይሎች ዓመቱን ሙሉ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ሰላም በማስከበር ረገድ ስመ ጥር ሃገር እንደሆነች እና በተለይ በሶማሊያ የአልሸባብን ሃይል በማጥፋት እንዲሁም የገንዘብ ምንጩን በማዳከም የሶማሊያን ሰላም በማጠናከር ትልቁን ሚና እየተወጣች መሆኑን አሳውቀዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ነው።
@tikvahethiopia
በአሚሶም ሴክተር 6 የሚገኘው የ5ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ ዓመታዊ የሜዳሊያ በዓሉ አከበረ።
በፕሮግራሙ ላይ የጁባ ላንድ ምክትል ፕሬዝዳት የሆኑት አቶ መሃመድ ሰይድ ተገኝተው ነበር።
ም/ፕሬዝዳት አቶ መሃመድ በፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል አልሸባብን ለማጥፋት ያደረገው የግዳጅ አፈፃፀም ይበል የሚያሰኝ እንደሆነ ተናግረዋል።
አክለው ፤ ሰራዊቱ በድስፕሊኑ የታነፀ ከህዝቡ ጋር ጥሩ የሆነ ግንኙነት ያለውና በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን ላሳየው ቁርጠኝነት ሜዳሊያው በክብር እንደተሰጠው ግልፀዋል።
የሴክተር 6 አዛዥ የሆኑት ብ/ጄ አበባው ሰይድ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ፣ የኬንያና የሴራሊዮን የፖሊስ ሃይል እንዲሁም የUN አጋዥ ሃይሎች ዓመቱን ሙሉ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ሰላም በማስከበር ረገድ ስመ ጥር ሃገር እንደሆነች እና በተለይ በሶማሊያ የአልሸባብን ሃይል በማጥፋት እንዲሁም የገንዘብ ምንጩን በማዳከም የሶማሊያን ሰላም በማጠናከር ትልቁን ሚና እየተወጣች መሆኑን አሳውቀዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ነው።
@tikvahethiopia