TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#OFC #OLF

ትናንት እና ከትናንት በስቲያ በመቐለ ከተማ ፌደራል ስርዓቱንና ህገ-መንግሥቱን መጠበቅ በሚል በተካሄደው የውይይት መድረክ ጥቂት የማይባሉ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጥሪውን ውድቅ ማድረጋቸው ተገልጿል፡፡

ከእነዚህ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ነው፡፡ የፓርቲው የወጣቶች ዘርፍ ተጠሪ አቶ አዲሱ ቡላላ ህውሐት ከዚህ በፊት የፌደራል ስርዓቱን በስርዓት ሲመራ ስላልነበር ዛሬ የፌደራል ስርዓቱ ተቆርቋሪ ነኝ ማለቱ የሚታመን አይደለም ይላሉ፡፡

በተመሳሳይ ጥሪውን ውድቅ ያደረገው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ ነው፡፡ የግንባሩ ቃል አቀባይ አቶ ቶሌራ ደግሞ ከዚህ በፊት እኛን ሲያሳድድ ከነበረ ሃይል ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት ሊኖረን አይችልም ብለው ከመድረኩ ቀርተዋል፡፡ በትግራይ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎችም ጥሪው ስላልተደረገላቸው ቀርተዋል ተብሏል፡፡

በትግራይ ክልል ከሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች አንዱ የሆነው የአረና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አምዶም ገብረስላሴ ጥሪ እንዳልተደረገላቸው ለቢቢሲ ሬድዮ አማርኛ ክፍል ተናግረዋል፡፡

አያይዘውም ከትግራይ ክልል የተገኙት ሁለት ፓርቲዎች ብቻ ናቸው ብለዋል፡፡ ህውሐት የፌደራል ስርዓቱና የህገ-መንግሥቱ ጠባቂ ነኝ የሚለው ሌሎች ላይ ጫና ለማሳደር እንደሆነም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

(AHADURADIO)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia