ከ38 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት በበጎፈቃድ መሰብሰብ ተችሏል!
በትምህርት ሚኒስቴር አነሳሽነት የተጀመረው “የእኛ ለእኛ” የበጎ ፈቃደኞች መርኃግብር ላይ ላለፉት 3 ወራት ለተሳተፉ በጎፈቃደኛ ወጣቶች ዛሬ በትምህርት ሚኒስቴር ቅጥር ግቢ ሚኒስትር ዴኤታዋ ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ በተገኙበት የሰርተፍኬት አሰጣጥ መርኃግር ተከናውኗል፡፡ በአጠቃላይ የበጎ ፈቃድ ዘመቻው ከ350 በላይ በጎ ፈቃደኞች የተሳተፉ ሲሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ለሚገኙት በጎፈቃደኞች ይህ መርኃግብር ተዘጋጅቷል፡፡
በሦስት ወር የበጎ ፈቃድ ስራ በትምህርት ቁሳቁስ ከ3 ሚሊየን ዘጠኝ መቶ ሺ በላይ የተሰበሰበ ሲሆን በአልባሳትና በሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ከገቢዎች ሚኒስቴር የተገኘውን ድጋፍ ጨምሮ 30 ሚሊየን የሚቆጠር ድጋፍ ማሰባሰብ ተቻለ ሲሆን በአጠቃላይ ግን በዚህ መርኃግብር 38 ሚሊየን ሀብት መሰብሰብ ተችሏል፡፡ በዚህም በበርካታ ቦታዎች የሚገኙ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ጉዳት ትምህርታቸውን መከታተል ላልቻሉና ችግር ለደረሰባቸው አከባቢዎች ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡ በቀጣይ የትምህርት ሚኒስቴር በእኛ ለእኛ የበጎፈቃድ አገልግሎት ስር “የተማረ ያስተምር” የተሰኘ መርኃግብር የሚጀመር ሲሆን በዚህም በርካታ በጎፈቃደኞች ይሳተፉበታል ተብሎ ይታመናል፡፡
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በትምህርት ሚኒስቴር አነሳሽነት የተጀመረው “የእኛ ለእኛ” የበጎ ፈቃደኞች መርኃግብር ላይ ላለፉት 3 ወራት ለተሳተፉ በጎፈቃደኛ ወጣቶች ዛሬ በትምህርት ሚኒስቴር ቅጥር ግቢ ሚኒስትር ዴኤታዋ ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ በተገኙበት የሰርተፍኬት አሰጣጥ መርኃግር ተከናውኗል፡፡ በአጠቃላይ የበጎ ፈቃድ ዘመቻው ከ350 በላይ በጎ ፈቃደኞች የተሳተፉ ሲሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ለሚገኙት በጎፈቃደኞች ይህ መርኃግብር ተዘጋጅቷል፡፡
በሦስት ወር የበጎ ፈቃድ ስራ በትምህርት ቁሳቁስ ከ3 ሚሊየን ዘጠኝ መቶ ሺ በላይ የተሰበሰበ ሲሆን በአልባሳትና በሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ከገቢዎች ሚኒስቴር የተገኘውን ድጋፍ ጨምሮ 30 ሚሊየን የሚቆጠር ድጋፍ ማሰባሰብ ተቻለ ሲሆን በአጠቃላይ ግን በዚህ መርኃግብር 38 ሚሊየን ሀብት መሰብሰብ ተችሏል፡፡ በዚህም በበርካታ ቦታዎች የሚገኙ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ጉዳት ትምህርታቸውን መከታተል ላልቻሉና ችግር ለደረሰባቸው አከባቢዎች ድጋፍ ማድረግ ተችሏል፡፡ በቀጣይ የትምህርት ሚኒስቴር በእኛ ለእኛ የበጎፈቃድ አገልግሎት ስር “የተማረ ያስተምር” የተሰኘ መርኃግብር የሚጀመር ሲሆን በዚህም በርካታ በጎፈቃደኞች ይሳተፉበታል ተብሎ ይታመናል፡፡
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#WKU ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንትነት ያመለከቱ ተወዳዳሪዎች የመጀመሪያ ዙር የውጤት መግለጫ፦
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia