TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
በዘፈቀደ የሚተገበረው የታክሲ ታሪፍ፦

በአዲስ አበባ የትራንስፖርት መጨናነቅና እጥረት መኖሩ ታክሲዎች በዘፈቀደ እንዲያስከፍሉ ምክንያት ከሆነ ሰንብቷል፡፡ በአብዛኛዎቹ የትራንስፖርት ቦታዎች ላይ የሚታዩ የተለያዩ ችግሮችን ተቋቁመው አገልግሎቱን ለማግኘት የሚጋፉ ሰዎችም ለስርቆት ሲዳረጉ ማየቱ የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡

በአገሪቱ የሚታዩ ክፍተቶችን በመጠቀም ዋጋ መጨመርና ኅብረተሰቡን ማማረር የተለመደ ከሆነባቸው ዘርፎች አንዱ ትራንስፖርት ነው፡፡ የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ከሜክሲኮ ዓለም ባንክ ለመሄድ ተሠልፈው ያገኘናቸው አቶ ኬራሚድ ሙራድ፣ በተለያዩ ቦታዎች መሄድ የሚፈልጉ ተሳፋሪዎችን እንግልት በመመልከት፣ መንግሥት ካወጣው ታሪፍ በላይ በመጠየቅ ተሳፋሪውን አማራጭ የሚያሰጡ፣ በኑሮ ውድነት ላይ ሰውን የሚያማርሩ የታክሲ ትራንስፖርት ሰጪዎች መበራከታቸውን ይገልጻሉ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ #ሪፖርተር_ጋዜጣ👇
https://telegra.ph/AA-07-28-3
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አዲሱን የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን ደንብ ማስፈጸሚያ መመርያ አስተያየት እንዲሰጥበት ለተቋማት ላከ!

ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በቅርቡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያፀደቀውን የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን ደንብ ማስፈጸሚያ መመርያ አርቅቆ፣ ለክልሎችና ለተለያዩ ተቋማት አስተያየት እንዲሰጡበት አሠራጨ፡፡

ከአሁን ቀደም ከ40 ዓመታት በላይ ሲሠራበት የቆየውን የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን ከዘጠኝ ደረጃዎችና ከአሥራ ሁለት እርከኖች ወደ ሃያ ሁለት ደረጃዎች ብቻ በመወሰን፣ እያንዳንዱ ደረጃ ከአንድ እስከ 12 የሚደርሱ መደቦችን እንዲይዝ የሚያደርገውን ደንብ በሚኒስትሮች ምክር ቤት የፀደቀው ከሳምንት በፊት ነበር፡፡

ከዚህ በተጨማሪም መመርያው ከአሁን ቀደም በመንግሥት ተወስነው ይሠራባቸው የነበሩ ከ70 በላይ የደመወዝ ስኬሎችን ወደ አንድ ስኬል የሚቀይር ሲሆን፣ ቀድሞ የነበረው ስኬል ይሠራበታል ቢባልም በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች የተለያዩ ስኬሎች በመኖራቸው፣ ከ150 በላይ እንዲሆኑ ያደረገውን አሠራርም ይለውጣል፡፡

በዚህም መሠረት በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ለተመሳሳይ ሥራዎች የተለያዩ ክፍያዎች ይፈጸሙ ስለነበር፣ የክፍያ ኢፍትሐዊነት እንዲንሰራፋ በማድረጉና ለእኩል ሥራዎች እኩል ክፍያ የሚያጎናጽፈውን ሕጋዊ መብት ወደ ጎን ያለ አሠራር ነበር ተብሎ የቀድሞው ይተቻል፡፡ አዲሱ የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን በአገር አቀፍ ደረጃ ሥራዎችን በመስፈርት በመመዘን፣ እኩል የሆኑ ሥራዎች እኩል ክፍያ እንዲያገኙ ያስችላልም ተብሏል፡፡

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-08-28
አቶ መለስ ዓለሙ የደቡብ ክልል ፕሬዘዳንት ሆነው ሊሾሙ ይችላሉ!

ከአሁን ቀደም የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉት አቶ መለስ ዓለሙ፣ ለክልሉ ምክር ቤት በፕሬዚዳንትነት ሊሾሙ እንደሚችሉ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ አቶ መለስ በአሁኑ ወቅት በሚኒስትር ማዕረግ የኢሕአዴግ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ማዕከል ምክትል ዋና አስተባባሪ በመሆን በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-08-28-2