TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
የቺኩንጉንያ ወረርሽኝ በድሬዳዋ!

በድሬዳዋ አስተዳደር የተከሰተውን የቺኩንጉንያ ወረርሽኝ ለመከላከል እየሰራ መሆኑን የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ አስታውቋል። የጤና ቢሮው በዛሬው እለት በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ ቺኩንጉንያ የተባለው የበሽታ ምልክት እስካሁን በ3 ሺህ 756 ሰዎች ላይ ተስተውሏል።

ሆኖም ግን በሽታው ከወባ እና ከደንጌ ጋር ተመሳሳይነት ስላለው ሁሉም ታማሚዎች ቺኩንጉንያ በተባለው በሽታ ስለመያዛቸው ሙሉ በሙሉ እንዳልተረጋገጠም ነው ቢሮው ያስታወቀው። የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ፉአድ ከድር እንደተናገሩት፥ በ10 ናሙናዎች ላይ በተደረገ ናሙና አራቱ ቺኩንጉንያ መሆናቸው በመለየቱ በሽታው በወረርሽኝ መልክ መከሰቱን ተረጋግጧል። #ከበሽታው ጋር በተያያዘ ግን እስካሁን የተመዘገበ ሞት እንደሌለም አስታውቀዋል። ቺኩንጉንያ የተባለው በሽታ “ኤደስ” በተባለች ነብሳት አማካኝነት የሚተላለፍ መሆኑንም ነው ዶክተር ፉአድ ያስታወቁት።

https://telegra.ph/DDC-08-13

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia