ደራርቱ ውሳኔዋን አጥፋለች!
ደራርቱ ቱሉ ከኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ራሷን ለማግለል ያሳለፈችውን ውሳኔ አጠፈች። በደብረ ብርሀን ከተማ በሚደረው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከሥራ አስፈፃሚነት ለመልቀቅ መወሰኗን የተናገረችው ደራርቱ በጠቅላላ ጉባኤው በርካታ ሰዎች ውሳኔዋን እንድታጥፍ ግፊት ማሳደራቸውን የስፖርት ጋዜጠኛ ኦምና ታደለ ለጀርመን ራድዮ ተናግሯል። ኦምና እንደሚለው ደራርቱ ግፊት ያሳደሩ ሰዎችን #ማሳዘን አልፈለገችም።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በፕሬዝዳንትነት የምትመራው ደራርቱ በውሳኔ አሰጣጥ ረገድ የምትመለከታቸውን ሕጸጾች ከዚህ በኋላ የማይታረሙ ከሆነ ከኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚነት ራሷን እንደምታገል አስጠንቅቃለች።
በሁለት የኦሎምፒክ ውድድሮች የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ የነበረችው ደራርቱ ዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ ከሚመሩት የኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚ አባልነት መልቀቋን ያሳወቀችው በዛሬው ዕለት ነበር። «ከዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ እና እርሳቸው ከሚመሩት የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በተፈጠረ መቃቃር ምክንያት» ከኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚነት ደራርቱ ራሷን ለማግለል አስገድዷት ነበር።
ዶክተር አሸብር ሥመ-ጥሩዋን የሩጫ ንግሥት ወደ ሥራ አስፈፃሚነቷ ለመመለስ ቃል ገብተው ነበር። የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ በአማራ ክልል ደብረ ብርሀን ከተማ ጠቅላላ ጉባኤ እያካሔደ ነው።
Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደራርቱ ቱሉ ከኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ራሷን ለማግለል ያሳለፈችውን ውሳኔ አጠፈች። በደብረ ብርሀን ከተማ በሚደረው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከሥራ አስፈፃሚነት ለመልቀቅ መወሰኗን የተናገረችው ደራርቱ በጠቅላላ ጉባኤው በርካታ ሰዎች ውሳኔዋን እንድታጥፍ ግፊት ማሳደራቸውን የስፖርት ጋዜጠኛ ኦምና ታደለ ለጀርመን ራድዮ ተናግሯል። ኦምና እንደሚለው ደራርቱ ግፊት ያሳደሩ ሰዎችን #ማሳዘን አልፈለገችም።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በፕሬዝዳንትነት የምትመራው ደራርቱ በውሳኔ አሰጣጥ ረገድ የምትመለከታቸውን ሕጸጾች ከዚህ በኋላ የማይታረሙ ከሆነ ከኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚነት ራሷን እንደምታገል አስጠንቅቃለች።
በሁለት የኦሎምፒክ ውድድሮች የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ የነበረችው ደራርቱ ዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ ከሚመሩት የኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚ አባልነት መልቀቋን ያሳወቀችው በዛሬው ዕለት ነበር። «ከዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ እና እርሳቸው ከሚመሩት የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ጋር በተፈጠረ መቃቃር ምክንያት» ከኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥራ አስፈፃሚነት ደራርቱ ራሷን ለማግለል አስገድዷት ነበር።
ዶክተር አሸብር ሥመ-ጥሩዋን የሩጫ ንግሥት ወደ ሥራ አስፈፃሚነቷ ለመመለስ ቃል ገብተው ነበር። የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ በአማራ ክልል ደብረ ብርሀን ከተማ ጠቅላላ ጉባኤ እያካሔደ ነው።
Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia