TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#Breaking ባለቤትነቱ የትራንስፖርት ኔሽን ኤርዌይስ የሆነ አንድ ሄሊኮፕተር ከቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተነስቶ በመብረር ላይ ሳለ ከኤርፖርቱ በቅርብ ርቀት ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ #መከስከሱ ታውቋል።

Via #reporter
ፎቶ-የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሚድሮክ ሄሊኮፕተር ተከሰከሰ‼️

ባለቤትነቱ የትራንስ ኔሽን ኤርዌይስ የሆነ አንድ ሄሊኮፕተር ከቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተነስቶ በመብረር ላይ ሳለ ከኤርፖርቱ በቅርብ ርቀት ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ መከስከሱ ታወቀ፡፡ በበረራው ላይ የነበሩ ተሳፋሪዎች ላይ የከፋ ጉዳት እንዳልደረሰም ከምንጮች ለማወቅ ተችሏል፡፡

ትራንስ ኔሽን ኤርዌይስ በሚድሮክ ቴክኖሌጂ ግሩፕ ሥር የሚተዳደር ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የግል አየር መንገዶች መካከል አንዱ ነው፡፡

ከሁለት ዓመታት በፊት የዚሁ አየር መንገድ ንብረት የሆነ አንድ ሄሊኮፕተር በቦሌ አካባቢ መከስከሱ ይታወሳል፡፡

Via #reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ👆ዛሬ ጥዋት የተከሰከሰው ሂሊኮፕተር የወደቀው በመኖሪያ ቤት ላይ ሲሆን፤ የተከሰከሰበት ምክንያትም የሞተር መጥፋት እንደሆነ ነው የታወቀው።

#reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢትዮ ቴሌኮም ሃብቱን በውጭ ኩባንያ እያስመረመረ መሆኑን ሪፖርተር አስነብቧል፡፡ መርማሪው የእንግሊዙ ፕራይስ ወተር ሃውስ ኩፐር የተባለው ኩባንያ ነው፡፡ ኩባንያው ካሁን በፊት የኢትዮ ቴሌኮምን የፋይናንስ አስተዳደርና የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት አደራጅቷል፡፡ ጥናቱ እስከ 6 ወራት ሊፈጅ ይችላል፡፡ የሃብት ግምቱ ሲጠናቀቅ ዲሊዮት የተባለ የእንግሊዝ ኩባንያና ኧርነስት ኤንድ ያንግ የተባለ የአሜሪካ ኩባንያ ደሞ ኢትዮ ቴሌኮም በሙሉ ወይም በከፊል ወደ ግል ባለሃብቶች ሲዘዋወር የአክሲዮን አወቃቀርና ሽያጭን በተመለከተ እንዲያማክሩ ተቀጥረዋል፡፡ የአማካሪ ኩባንዎችን ወጭ ዐለም ባንክና ለጋሽ ሀገራት ይሸፍናሉ፡፡ አጠቃላይ ሂደቱ የሚመራበት ረቂቅ ሕግ ገና በፓርላማ አልጸደቀም፡፡

Via #reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia