TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#update አቶ በረከት ስምዖን⬇️

የAssociated Press ጋዜጠኛ #ኤልያስ_መሰረት ከአቶ በረከት ስምዖን ጋር ያደረገው ቃለ-ምልልስ።

(ከእንግሊዘኛ የተተረጎመ)
በኤልያስ መሰረት(AP)
=====☆☆☆======☆☆☆=====

▪️#ጥያቄ: በመጀመርያ ብአዴን ሰሞኑን እርስዎ ላይ ስለወሰደው እርምጃ እናውራ። እርምጃው የተወሰደበት አካሄድ ምን ይመስል ነበር? እርስዎስ እንዴት ያዩታል? ተቀብለውታል?

▫️አቶ በረከት : መሰረተቢስ እርምጃ ነው። እንዲታወቅ የምፈልገው እኔ ስብሰባው ላይ እንዳልነበርኩ እና ይህንንም ለእነርሱ ማሳወቄን ነው። ይህም የሆነው በአሁኑ ሰአት በክልሉ ላይ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ነው። በአሁን ሰአት ክልሉ ላይ የህግ የበላይነት የለም። እርግጥ እየሆነ ያለው የደቦ ፍርድ (mob justice) ነው። ይህንንም የክልሉ መንግስት መቆጣጠር የቻለበት ሁኔታ አይታይም። የተጠቀሰውን የንግድ ድርጅት በተመለከተ ስለተባለው ጉዳይ ያለኝ ሪከርድ ይመሰክራል።

በእኔ አስተዳደር ምንም #የጠፋ ነገር የለም። እንደ እኔ አስተሳሰብ ይሄ እርምጃ የመጣው አንደኛ ምክትል ጠ/ሚሩን በቅርቡ በተካሄደው የመተካካት ወቅት አለመደገፌ፣ በአቋሜ የማልደራደር ስለሆነ እና ፊት ለፊት ስለምናገር እንዲሁም የማጥራት አካሄድ (cleansing move) ነው። ምክንያቱም በረከት ከተለየ አካባቢ የመጣ ነው ስለሚባል ነው። እርግጥ ቤተሰቦቼ የኤርትራ ስር መሰረት ቢኖራቸውም እኔ ተወልጄ ያደግኩት ጎንደር ነው። የንግድ ድርጅቱን በተመለከተ አመታዊ የኦዲት ሪፖርት አለው። የእኛ ድርጅት ከኤፈርት ድርጅቶች አንደኛ ነው ታክስን በመክፈል ጨምሮ። በዚህ እኔ እርግጠኛ ነኝ።

▪️#ጥያቄ: በብአዴን የተወሰደውን እርምጃ ሲሰሙ አዘኑ፣ ደነገጡ ወይስ ሌላ ስሜት አጫረቦት?

▫️አቶ በረከት: ይሄ የሚጠበቅ ነገር ነበር። ይሄ ገና የመጀመርያቸው ነው (just a tip of the iceberg)። ወደፊት ሌሎች ተመሳሳይ ጉዳዮች ይመጣሉ ብዬ እገምታለሁ። እኔ ላይ ግን ምንም ችግር ይመጣል ብዬ አልፈራም ምክንያቱም ንፁህ ነኝ በዛ ላይ ለመብቴ እታገላለሁ።

▪️#ጥያቄ: የጠ/ሚር አብይን ፈጣን ለውጦች እንዴት ያዩዋቸዋል?

▫️አቶ በረከት: በእርግጥ ጠ/ሚሩ እየተገበሩት ያለው ለውጥ ኢህአዴግ ባለፈው ዲሴምበር ያሳለፈውን ነው። ሁላችንም የዚህ ለውጥ አካል ነበርን። ስለዚህ ስለ ለውጥ አስፈላጊነት ምንም ጥርጥር የለኝም። ጥሩ ለውጦች እያየን ነው።

▪️#ጥያቄ: ከሳምንታት በፊት እርሶ አሉበት ተብሎ የታሰበ በአማራ ክልል የሚገኝ ሆቴል እና መኪና ጥቃት ደርሶበት ነበር። ጥቃቱ አላስደነገጥዎትም? እርስዎስ በወቅቱ እዛ ነበሩ?

▫️አቶ በረከት: በወቅቱ እኔ #እቤቴ እንጂ እዛ #አልነበርኩም። ይህ የሚሳየው ግን በክልልሉ ያለው አስተዳደር ቁጥጥር ማጣቱን ነው። ህግ ያለው በቡድኖች እጅ ሆኖዋል።

▪️#ጥያቄ: የወደፊት የፖለቲካ ህይወቶ ምን ሊመስል ይችላል? ወይስ ፖለቲካ በቃዎት?

▫️አቶ በረከት: አሁን ያለው የፖለቲካ ሁኔታ ከእኔ ግለ- አስየሳሰብ ጋር አብሮ ስላማይሄድ አልቀጥልም። I'm thinking of coping with it Lidetu's style (የልደቱን ስታይል ለመከተል እያሰብኩ ነው)። አሁን ያለው ሁናቴ ፖለቲካን fair በሆነ መልኩ ለማካሄድ ያመቻል ብዬ አላምንም።

▪️#ጥያቄ: በቅርቡ የቀድሞው ጠ/ሚር ታምራት ላይኔ ባለቤት እርስዎ ላይ ወቀሳ ሰንዝረዋል። እርሳቸው በመታሰራቸው በእርግጥ ደስተኛ ነበሩ? ከሆነስ ለምን?

▫️አቶ በረከት: የእርሱ ጉዳይ በፍርድ ቤት ተወስኖ ከዛ ደሞ በህግ መሰረት ተፈቷል። 12 አመት ትምህርት ካላስተማረው እኔ ምንም ማረግ አልችልም። እስር ላይ የቆየው ባላደረገው ነገር አይደለም። ማንም ጣቱን ወደ እኔ አሁን ላይ ቢቀስር ለእኔ ምንም ማለት አይደለም።

▪️#ጥያቄ: አንድ ምክር ለጠ/ሚር አብይ ለግሷቸው ብልዎት እርሱ ምን ይሆናል?

▫️አቶ በረከት: እኔ እየሰራህ ያለውን ጥሩ ስራ ቀጥልበት ነው የምለው። ቃል የገባሀቸውን ነገሮችም ፈፅማቸው ልለው እወዳለሁ። ይህ የይቅርታ እና ምህረት ግዜ ወደፊትም መቀጠል አለበት። ዋናው ግን ይህ ሀገር sensetive ስለሆነ የ balance ስራ ሁሌ መሰራት አለበት። ጠ/ሚሩ እንዲሳካላቸው እመኛለሁ።

▪️#ጥያቄ: ጠ/ሚሩ ሹመት ሊሰጥዎ አስበዋል እንበል። ሹመቱን ይቀበላሉ ወይስ በተቃራኒው?

አቶ በረከት: በፍፁም! የእስካሁኑ ይበቃኛል።

📌ማሳሰብያ: ይህ ለAP ዜና ታስቦ የተደረገ እና አንድ ሁለት ፓራግራፍ ከእሳቸው ለማግኘት ታስቦ የተደረ ቃለ መጠይቅ ነው። ስለዚህ አላማው ለአለም አቀፍ ዜና መሆኑን ተረድታችሁ ይሄንን ሳይጠይቅ፤ ያንኛውን ሳያነሳ እንደማትሉ ተስፋ አረጋለሁ።

©ኤልያስ መሰረት(የAP ጋዜጠኛ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ በረከት ስምዖን ከBBC ጋር⬇️

#ጥያቄ፦ የታገዱባቸውን ምክንያቶች ያምኑባቸዋል?

▪️አቶ በረከት፦ አላምንባቸውም። ምክንያቱም ሁለቱም [ክሶች] መሠረተ ቢስ ናቸው። የአማራ ሕዝብን አይጠቅሙም። የለውጥ ኃይሎች
አይደሉም። ጥረትንም ችግር ፈጥረውበታል ነው የሚሉት። ሁሉም መሠረተ ቢስ ናቸው። ለአማራ ሕዝብ አይጠቅሙም የሚለው እኛ ዕድሜ ልካችንን ለራሳችን ሳናስብ በአማራ ክልል ነው ስንታገል የኖርነው። 'ክልሉ ተለውጧል፤ አድጓል፤ ተሻሽሏል፤ ባለፉት 25 ዓመታት ወደፊት ተራምዷል'፥ ሲሉ የነበሩ ሰዎች ይህን [ለውጥ] ወይ ብቻችን አምጥተነዋል ማለት አለባቸው፥ ወይ ደግሞ አብረን ነው ያመጣነው ማለት አለባቸው።

የለውጥ ኃይሎች አይደሉም የተባለውም መሠረተ ቢስ ነው። ሰው አሁን ነው ድምጹ መሰማት የጀመረው። አሁን ሦስት አራት አምስት ወራት። እኛ ከ2002 ጀምሮ "በከባድ ሁኔታ ችግር ላይ ነን፤ ድክመታችን በዝቷል፤ አገሪቱንም ወደ ቀውስ የሚያመሩ ነገሮች ተበራክተዋል፤
መሻሻል አለብን' ብለን የለውጥ ሐሳቡን ያመጣነው እኛ ነን። ለዚህም ከባድ ዋጋ ክፈለናል። ያልከፈልነው ነገር የለም።

የለውጥ ኃይሎች አይደሉም የሚባለው፥ የለውጥ ጀማሪዎች ቀስቃሾች እኛ ነን። ግን ወጥተን እንዲህ አድርገናል ማለት አልወደድንም።

ጥረትን በተመለከተ ለመነሻ የተሰጠን ገንዘብ 20 ሚሊዮን እና 31 ያረጁ ኤንትሬዎች ማርቼዲሶች ከጦርነቱ የተራረፉ ናቸው። አሁን 11 ቢሊዮን ብር የሚያወጡ 20 ኩባንያዎች ለአማራ ክልል አስረክበናል። ከምስጋና ጋር ሊሸኙን ይገባ ነበር። ጽድቆ ቀርቶ በወጉ በኮነንኝ አንዲሉ በወጉ እንኳ አላሳናበቱንም።

ኦዲትን ሪፖርት አለን። ሁሉም ነገር አለን። በኢትዮጵያ ውስጥ ኢንዶውመንት ተብሎ የግብር ከፋይ ምሳሌ ይጠቀስ ቢባል ጥረትን ያክል ግብር ከፋይ ተምሳሌት የሆነ ድርጅት የለም። ስለዚህ በዚህ ደረጃ ያነሱትም ነገር መሠረተ ቢስ ነው።

#ጥያቄ፦ ከማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ የቀራችሁበት ምክንያት ምንድነው?

▪️አቶ በረከት ፦ ሁለታችንም ጥሪው ደርሶናል። እኔ ደርሶኛል፤ ታደሰ ኢሜሉ ስለተዘጋ አልደረሰውም። የጥረት ኢሜሉ ነው የነበረው፤ [እሱም] ተዘግተቷል። እኔ እንደደረሰኝ ዐይቼ ምን እናድርግ ተባባልን። ብንሳተፍ ጥሩ ነበር፤ ግን ክልሉ ውስጥ የሚካሄደው ስብሰባ የጸጥታ አስተማማኝነት በሌለበት ሁኔታ ነው የሚካሄደው፤ ስለዚህ እንንገራቸው ተባባልን። ጠየቅን እነሱም ችግር አለ፤ የጸጥታ ዋስትና ግን አንሰጣችሁም አሉ። ስለዚህ ልንሳተፍ አንችልም። የኛ ችግር አይደለም።

#ጥያቄ፦ እርስዎ አሉበት በተባለ ሆቴል ጥቃት ተሰንዝሮ ነበር፤ ከዚያም በኋላ በደቦ የሚፈጸም ሕገወጥነት የሚመስል ነገር በክልሉ ይስተዋላል። ይህን የመሰሉ ጥቃቶች ብአዴን ማስቆም ለምን አቃተው?

▪️አቶ በረከት፦ ብአዴን በሕዝብ ተመርጦ ክልሉን እያስተዳደረ ያለ ድርጅት ነው። መንግሥት የመሠረተው እሱ ነው። መንግሥት ባለበት አገር የሕግ የበላይነት ሊከበር አልቻለም። ሥርዓት አልበኝነት በየቦታው አለ። ይሄ እኔን ብቻ የሚመለከት አይደለም። ብዙ ሰው ለአደጋ የተጋለጠበት ሁኔታ ነው ያለው።
ረዘም ላለ ዓመታት ማንነቱ ያልታወቀ ኃይል ሱቅ ዝጉ ይላል፣ ያዘጋል፤ ክፈቱ ይላል፣ ያስከፍታል። መንገድ ዝጉ ይላል፣ ያዘጋል። መንገድ ክፈቱ ይላል፣ ያስከፍታል። [ብአዴን] በክልሉ ውስጥ ሕግና ሥርዓት የሚያስከብር በዚያ ደረጃ አቅሙ ተጠናክሮ የሚገኝ መንግሥት ሆኖ አይታየኝም።

#ጥያቄ፦ ማንን ተጠያቂ ያደርጋሉ ታዲያ?

▪️አቶ በረከት፦ ዞሮ ዞሮ አመራሩ ነዋ። የአገራዊ ሕገ መንግስቱም የክልላዊ መንግሥቱም የማስተዳደር ኃይል ይሸከማል። እርቀ ሰላም ሊኖር ይችላል። መታረቅ መጥፎ ነው የሚል አቋም የለኝም። ግን ሥርዓት አልበኝነት መስፈን አለበት ማለት አይደለም። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደጋግመው 'ዲሞክራሲን ነጻነትን ስንፈልግ ሕግና ሥርዓት እየጣስን አይደለም' ብለው አስቀምጠዋል። ይሄ ነው ትክክለኛው መልስ። በክልሉ ይሄን መርህ የሚያረጋግጥ ነገር አይደለም የማየው።

#ጥያቄ፦ ቀደም ሲል ራስዎን አግልለው ነው በድጋሚ የተመለሱት። አሁን ይቆጮታል። ያኔ እንደወጣሁ በቀረሁ ኖሮ በሚል?

▪️አቶ በረከት፦ በአቶ ኃይለማርያም ጊዜ ነው ጥያቄ ያቀረብኩት። በአካሄዱ ብዙ አልተስማማሁም። ብዙ ጥፋት ይፈጸም ነበር። በዛው ውስጥ አብሮ መቀጠል የማልችለበት ሁኔታ እየተበራከተ ሲመጣ ጥያቄ አቅርቢያለሁ። በመጨረሻ ደግሞ ነባሮች ተሳተፉ ተብለን ስንሳተፍና በኛም
አስተዋጽኦ ጭምር የለውጥ እንቅስቃሴ ሲጀመር አብረን እንቀጥል ተባለ፤ አብረን እንቀጥላለን አልን። የራሱ ጉዳይ ብለህ ጥለከው የምትሄደው ነገር አይደለም።፥ በዙ መስዋእትነት ስለተከፈለበት።

የብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴም የካቲት ላይ 'እባክህ ተመለስ' ብሎ 'በቃ እኛን ጥለህ የት ትሄዳለህ' ብለውኝ ነው የተመለስኩት። አሁን 6 ወር ባልሞላ ጊዜ በሌለንበት የለውጥ ኃይል አይደለህም ብለው ተባረሀል ብለውኛል ወይ አግደውኛል። የካቲት ላይ በተካሄደ ስብሰባ 'እባክህን በቃ ደስ እንዲለን ተመለስ' ብለውኝ እንጂ እኔ ይበቃኛል ብዬ ነበር።

#ጥያቄ፦ ለምን ይመስልዎታል እንደዚህ ዓይነት ውሳኔ የተላለፈብዎ?

▪️አቶ በረከት፦ የኛ ክልል አይደሉም ብለው የሚያስቧቸውን ሰዎች ማጥቃት፤ በዚያ መልክ የተያዘ አለ። ተሳስታችኋል አትሠሩም ስንፍና አለባችሁ ብለን ወቀሳ ያቀረብንባቸው ሰዎች ይቀየማሉ።

ሦስተኛ ብልሽት አለ የሚልዋቸውን ሰዎች፣ በራሳቸው እምነት በነጻነት ቆመው የሚናገሩ ሰዎችን አለመውደድ አለ። እነዚህን ሰዎች ነው እየተበቀሉ ያሉት። ይሄ በጣም አደገኛ ነው።

#ጥያቄ፦ ወይዘሮ አና ጎሜዝ በትዊተር ገጻቸው ላይ ስለሰጡት አስተያየት ምን ምላሸ ይሰጣሉ?

▪️አቶ በረከት፦ ወይዘሮ አና ጎሜዝ ፖርቹጋላዊት ናቸው። ፖርቹጋል የአውሮፓ አፍሪካ ነው የምትባለው። በደንብ ካልለሙት አገሮች አንዷ ናት። ሴትየው በቁም ነገር የሚያስቡ ከሆነ ስለ ፖርቹጋል ቢያስቡ፤ ጊዜያቸውን የአገራቸውን ችግር በመፍታት ቢያውሉት። ኢትዮጵያ ሉአላዊት አገር ናት። ሿሚ ሻሪ የአገሬው ሕዝብ ነው። 'እርስዎን አያገባዎትም። አርፈው ይቀመጡ። #ፖርቹጋልን ቢያግዙ ይሻሎታል' በልልኝ። ይሄ በሉአላዊት አገር ጣልቃ መግባት የድሮ የፖርቹጋል የቅኝ አገዛዝ አስተሳሰብ አለቀቃቸውም።

#ጥያቄ፦ ከፖለቲካ ራስዎን አገለሉ ማለት ነው?

▪️አቶ በረከት፦ በፖለቲካ መተካካት ሂደት አያት ሆነናል። የኛን ትውልድ አመራር እንደ አያት ብትወስድ፥ የአቶ ኃይለማርያምን እንደ አባት፤ የዐብይን እንደ ልጅ ብትወስድ አያት ሆነናል። እንደ አያት ራቅ ብለህ ተረት የምታወራብት ጊዜ ላይ ነው ያለነው። ተረት ለማውራት ፖለቲከኛ መሆን አይጠይቅም።

#ጥያቄ፦ በዋናነት ምን ላይ ይሳተፋሉ ከዚህ በኋላ?

▪️አቶ በረከት፦ አሁን እንኳ ባለው ሁኔታ ከልጆቼ ጋር ቤቴ ውስጥ ቁጭ ብዬ መጽሐፎቼ ጋር እየተጫወትኩ ማለፍ ነው የምፈልገው። ጥቃቱ ስለተደጋገመብኝ ብቻ ነው እንጂ… ከሚዲያም ከሁሉም ነገር ርቄ ታጥቤ ተለቃልቄ መኖር ነው የምፈልገው።

©BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል ምክር ቤት 5ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ‼️

የክልል ጥያቄን በተመለከተ፡-

"የሲዳማ ዞን ክልል የመሆን ህገ-መንግስታዊ #ጥያቄ ህገ-መንግስታዊ ሂዴቱን ተከትሎ እንዲፈፀምና #የሌሎች የክልላችን ህዝቦች ጥያቄዎችና ቀጣይ ሁኔታ የህዝቦችን ትስስር በሚያጠናክር መልኩ በባለሙያዎች ቡድን ጥልቅ ጥናት ተደርጎ እንዲታይ ምክር ቤቱ
መክሮበታል።"

ምንጭ፦ የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ‼️

ከበርካታ የሀገራችን #ከፍተኛ_ትምህርት_ተቋማት ተማሪዎች በተደጋጋሚ ከሚመጡልኝ ጥቆማዎች መካከል አንዱ የተማሪዎች ንብረት መዘረፍ ነው። እነዚህ ተደጋጋሚ የዘረፋ ጥቆማዎች ተቋማት ለተማሪዎቻቸው የሚያደርጉት ደህንነት እና ጥበቃን #ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው።

ለማንኛውም ትላንት የ5 ኪሎ ተማሪዎች የሚኖሩበት 6 ኪሎ ግቢ ውስጥ እንዲህ ሆኗል፦

አጠቃላይ ግምታቸው 85,000 ብር የሚያወጡ ላፕቶፖች እና samsung ታብሌት ከህንፃ ቁጥር 52 ከማደሪያ ክፍል 322 መዘረፉን ተማሪዎች ጠቁመዋል። የጠፉት ንብረቶች በውስጣቸው ተማሪዎቹ በቅርቡ የሚያስረክቧቸው ፕሮጀክቶችን የያዙ ናቸው።

ተማሪዎቹ ስለሁኔታው ሲያስረዱ፦

"ትላንት ምሽት እራት ለመመገብ በራችንን ቆልፈን ወጣን በሩን ስለመቆለፋችን እርግጠኞች ነን፤ ስንመለስ በሩ ዝግ ነው፤ አጠቃላይ ንብረታችን ግን የለም፤ #ተዘርፈናል!! የተዘረፍነው 7 ላፕቶፕ እና 1 ሳምሰንግ ታብሌት ነው። በጠፉት ላፕቶፖች ውስጥ በቅርቡ የምናስረክባቸው ፕሮጀክቶች አሉ። የተፈጠረውን ነገር ለተቋሙ አሳውቀናል።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia