TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ወንድሙ #የተገደለበት ሁሉ የገዳዮቹን ወንድሞች #ልግደል ካለ ሁላችንም ያለ ወንድም እንቀራለን!!
.
.
.

"በክልላችን በነበረው ብልሹ አስተዳደር ብዙ ችግሮች ተፈጥረዋል። ሁላችንም ተበድለናል። የተፈጸሙትን በደሎችና ችግሮች እንቁጠራቸው ብንል አንችልም። ይቅርታ አድርጉልኝና ማን ማንን እንደሚያጽናና አላውቅም። በደሎቹን ማስታወስና ቁስላችንን መቆስቆስ አያስፈልግም። አልሃምዱሊላህ አሁን ሁሉም አልፏል። ወገኖቼ እምባ ይብቃን፥ ማቃችንን እንጣል፥ በአዲስ መንፈስ እንነሳ። የጥላቻን እና ብቀላን ጦስ እስኪበቃን አይተናል። ወንድሙ የተገደለበት ሁሉ የገዳዮቹን ወንድሞች ልግደል ካለ ሁላችንም ያለ ወንድም እንቀራለን፥ ሁላችንም እንጠፋለን። ጥላቻ #በፍቅር እንጂ በበቀል አይሸነፍም። ስለዚህ #ካለፈው ተምረን #በፍቅር እና #በይቅርታ፥ በአዲስ ሞራል እጅ ለእጅ ተያይዘን ለጋራ ሰላም፥ ዲሞክራሲና ልማት እንረባረብ"

የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር (#ሙስጠፈ_መሀመድ_ኡመር)

©Yoseph Legess
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጳጉሜ 2 - የፍቅር ቀን

#በፍቅር ተደምረን፤ #በይቅርታ እንሻገር!

ክፉ አያግኛችሁ! ሰላም እደሩልኝ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
🕊ዝግጅቱ በሰላም ተጠናቋል🕊

የአዲስ አበባ ወጣቶችም ከተለያዩ የኦሮሚያ ክልል የመጡትን እንግዶች(ቄሮዎች) #በፍቅር እና በአክብሮት እየሸኙ ይገኛሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አርባ ምንጭ! ነገ በአርባ ምንጭ ከተማ በአዲስ አበባ ዙሪያ የተፈፀመው ድርጊት የሚያወግዝ ሰልፍ እንደሚደረገ ሰምቻለሁ። ጨዋው የአርባ ምንጭ ህዝብ ተቃውሞውን እና ሀዘኑን በሰላማዊ መልኩ እንደሚገልፅ ሙሉ እምነት አለኝ። ለዚህ ደግሞ ሰላም ወዳዶቹ የአርባ ምንጭ ወጣቶች ምስክር ናቸው።
.
.
ተጨማሪ...

የጋሞ ጎፋ ዞን አስተዳደር ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ለጊዜው የ1 ሚሊየን ብር ድጋፍ እንደሚያደርግ የተጠቆመ ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ የተፈፀመውን ድርጊት በእጅጉ ኮንኗል። ጋሞ ጎፋ ዞን ብሔር ብሔረሰቦች ተቻችለው #በፍቅር የሚኖርበት ዞን በመሆኑ መላው የዞኑ ህዝብ በትግስት እና #አኩሪ ዕሴቱን በመጠበቅ እንዲሁም በህግ #ተቀባይነት የሌለው ተግባር #በላመፈጸም እንዲተባበር ከዞኑ ጥሪ ቀርቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደብረ ማርቆስ⬆️

ኢትዮጵያና ኤርትራ ለሁለት አስርት ዓመታት ያህል ያሳለፉትን ኩርፊያ ይበቃል በማለት የሰላምና የወዳጅነት ስምምነት መፈረማቸውን ተከትሎ በርካታ በጎ ተግባራትን በመስማት ላይ እንገኛለን፡፡

ከወደ ደብረማርቆስ የተሰማው ጉዳይም የዚሁ አዲስ ጅምር አንዱ አካል ነው፡፡

የደብረማርቆስ ህዝብ ከዓመታት መለያየት በኋላ #ከኤርትራ የመጡ አብሮ አደጎቹን ተቀብሏል፡፡

ከ20 ዓመታት በፊት ኑሯቸውን በደብረ ማርቆስ ከተማ አድርገው ነበር፤ የወቅቱ አስከፊ የፖለቲካ ውሳኔ ግን በአካል እንጂ በመንፈስ ካልተለዩት ህዝብ ጋር ሳይፈልጉ ተገደው እንዲለዩ አደረጋቸው፡፡

ዛሬ ታሪክ ተቀይሯል መለያየት በአብሮነት፤ ጥላቻ #በፍቅር ድል ተነስተዋል፡፡

እናም አቶ ተስፋ ሚካኤል ግደይና አቶ መድሃኔ ግደይ ወደ ቀድሞ ከተማቸው ተመልሰዋል፡፡ ደብረ ማርቆስም የትናንት ልጆቿን የዛሬ እንግዶቿን እልል…! ብላ
ተቀብላለች፡፡

ከአቀባበሉ በኋላ ደግሞ የህዝቡን ቃል አክባሪነት እና ታማኝነት ያስመሰከረ አንድ አስገራሚ ዕውነታ ተገለጠ፡፡

ወደ ኤርትራ በሄዱበት ወቅት ትተውት የሄዱት ቤት ተጠብቆ ቆይቶላቸው ነበርና ህዝቡ ለባለቤቶቹ አስረክቧል፡፡

የኢትዮጵዊነት እሴትም በተግባር ታየ በተጨማሪም ህዝቡ ለኤርትራዊያኑ ወንድሞቹ የጋቢ ስጦታም አበርክቶላቸዋል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia