TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ‼️

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ውዥንብር ውስጥ እና አላስፈላጊ ስጋት ውስጥ የሚከቱ #ግለሰቦች ላይ ከፀጥታ ሀይላት ጋር በመሆን እርምጃ እየወሰድኩ ነው ብሏል። ዩኒቨርሲቲው አጥፊዎች በጥፋታቸው መጠን በዲሲፕሊንና በህግ ይጠየቃሉ ሲል ገልጿል። ለተማሪዎች ደህንነት ሲባልም የግቢው መግቢያ 2 ሰዓት እንዲሆን መደርጉን ከዩኒቨርሲቲው ተሰምቷል። ተማሪዎችም ለዩኒቨርሲቲው የዲሲፕሊን ስርዓት ተገዥ እንዲሆኑ #አጥብቆ አሳስቧል።

በሌላ በኩል...

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የከፍተኛ ትምህርት መማር ማስተማር ሂደት #በሰላማዊ መንገድ እንዲቀጥል ከወትሮው በተለየ ከሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች እና ኮሌጆች ጋር እየሰራ እንደሆነ ባለፈው ሳምንት መግለፁ አይዘነጋም። ፌደራል ፖሊስ በተለያዩ አካባቢዎች ጥብቅ ቁጥጥርና ጥበቃ እያከናወነ እንደሆነም ገልፆ ነበር።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አላማጣ ቆቦ‼️

የትግራይን ክልል ከአማራ ክልል የሚያገናኘው አላማጣ ቆቦ መስመር ለተሽከርካሪዎች ከተዘጋ 5 ቀናት አስቆጥሯል። መንገዱ የተዘጋው በአላማጣ ከተማ #የታሰሩ ሰዎች እንዲፈቱላቸው በጠየቁ የቆቦ ከተማ ወጣቶች ነው ተብሏል።

የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምርያ እንዳስታወቀው ችግሩን #በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት #ውይይት እየተካሄደ ነው።

የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው - መንገዱ በመዘጋቱ ለስራቸውን #እንቅፋት እየፈጠረባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ(የትላንት ምሽት ዘገባ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia