#updateሀዋሳ ዶ/ር ዐብይ⬇️
የኢህአዴግ ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በ11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ ለተሳተፍ #ሀዋሳ ከተማ ገብተዋል።
11ኛው የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ድርጅታዊ ጉባዔ “ሀገራዊ አንድነት ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል ከነገ ጀምሮ በሀዋሳ ከተማ ይካሄዳል።
በድርጅታዊ ጉባዔው ላይ ለመሳተፍም የኢህአዴግ ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዛሬው እለት ሀዋሳ ከተማ ገብተዋል።
በተጨማሪም የኢህአዴግ ምክትል ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን ድርጅታዊ ጉባዔው ላይ ለመሳተፍ ሀዋሳ ደርሰዋል።
እንዲሁም የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባኤ ተሳታፊዎችም ሃዋሳ ከተማ መድረሳቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ልዩ ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ አስታውቀዋል።
11ኛው የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) 11ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ ነገ ጠዋት ላይ በሀዋሳ ከተማ እንደሚጀምር ይጠበቃል።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢህአዴግ ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በ11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ ለተሳተፍ #ሀዋሳ ከተማ ገብተዋል።
11ኛው የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ድርጅታዊ ጉባዔ “ሀገራዊ አንድነት ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል ከነገ ጀምሮ በሀዋሳ ከተማ ይካሄዳል።
በድርጅታዊ ጉባዔው ላይ ለመሳተፍም የኢህአዴግ ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዛሬው እለት ሀዋሳ ከተማ ገብተዋል።
በተጨማሪም የኢህአዴግ ምክትል ሊቀ መንበርና የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን ድርጅታዊ ጉባዔው ላይ ለመሳተፍ ሀዋሳ ደርሰዋል።
እንዲሁም የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባኤ ተሳታፊዎችም ሃዋሳ ከተማ መድረሳቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ልዩ ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ አስታውቀዋል።
11ኛው የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) 11ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ ነገ ጠዋት ላይ በሀዋሳ ከተማ እንደሚጀምር ይጠበቃል።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ⬆️
የኢሕአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ የመጡ ከፍተኛ የመንግሥትና የፓርቲ ኃላፊዎች ጭምር ተፈትሸው ነው ወደ አዳራሽ የገቡት።
©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢሕአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ የመጡ ከፍተኛ የመንግሥትና የፓርቲ ኃላፊዎች ጭምር ተፈትሸው ነው ወደ አዳራሽ የገቡት።
©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ⬆️የኢህአዴግ 11ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ ባደረጉት ንግግር በይፋ ተከፍቷል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ የኢህአዴግ ሊቀመንበር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ በ11ኛው የግንባሩ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች ፡-
• 11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ በለውጥ ምሁዋር ውስጥ በገባንበት ወቅት መካሄዱ ታሪካዊ ያደርገዋል፡፡
• ኢህአዴግ ከዚህ ቀደም የሚያጋጥሙትን ፈተናዎች እያሸነፈ እንደመጣው ሁሉ የሚገጥሙትን ችግሮች እየፈታ የለውጡ ሞተር ሆኖ አገር መምራቱን ይቀጥላል፡፡
• ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ነገዋን በመፈለግ ላይ ያለች፣ በተፈጥሮ ሀብት የበለፀገች አገር ናት፡፡
• የሽግግር ሂደቱን የአገራችን አርሶአደር “የበሬውን ብልሃት እና የወይፈኑን ጉልበት አቀናጅቶ” …እንደሚለው ሁሉ በእኛም ዘንድ ተተኪዎችን በጎ ልምድ ካላቸው በማስተሳሰር አገራዊ ለውጡን ለማሳካት ኢህአዴግ ይታትራል፡፡
• አገር የምታድገው በቅብብሎሽ ነው፡፡
• ያለትላንት ዛሬ አልተገኘምና የትናቱን ትውልድ ማመስገን ያስፈልጋል፡፡ እኛም በተራችን በተተኪ ትውልድ መተካታችን አይዘነጋምና፡፡
• መተካካት የታቀደ ሂደት እንጂ ድንገተኛ ሆኖ እልቂት እንዳያመጣ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
• ይህ ትውልድ ስልጣንን በእጁ አስገብቶ ቀድሞ የነበረውን ነገር በማስፍረስ የተጠመደ መሆን አይገባውም፡፡
• ትላንት እና ዛሬን ያጣጣመች ኢትዮጵያን ለመገንባት ተግቶ መስራት ያስፈልጋል፡፡
• ኢትዮጵያ በላቀ ተግበራቸው ያገነኗት መሪዎች እንደነበሯት ሁሉ፣ ውድቀት የዳረጓትም ነበሩ፡፡ ለጠላቶቿ የሰጧት መሪዎችም ነበሩ፡፡
• ያለመተማማን በማስፋት፣ በጠብና በጦርነት ሊተላለቁ የነበሩ ልጆቿን አስታርቀው ወደ ልዩ ምዕራፍ ያስገቧት ነበሩ፡፡
• በአሁኑ ጊዜ ያለው አመራርስ የትኛውን ታሪክ ይደግማል? የሚለው ጥያቄ ለእኛ ቀርቧል፡፡
• የአገራችን እጣ ፈንታ አሁን እድሉን ባገኙት ፖለቲከኞች እንዲሁም በህዝቧ እጅ ነው፡፡
• ዘመናዊና ስልጡን አገር ለመፍጠር ህዝብን የስልጣን ልዕልና መገለጫ አድርጎ የሚቀበል ስርዓት መፍጥር ሲሳካልን ነው፡፡
• ህዝብ የሚያምናቸውና የሚከተላቸው ልዩ ልዩ የማህበረሰብ መሪዎችን ካገኘን በእምነት፣ በባህል፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በፖለቲካ፣ በጦር አመራር፣ በምህንድስና፣ በስፖርትና ኪነጥበብብ፣ በሌሎች ዘርፎችም ጭምር ከተዋጣልን አገር የተሳካ ጉዞ አድርጋ በከፍታ ጉዞ ላይ ትደርሳለች፡፡
• የምንፈልጋትን አገር መምሰልና መሆን የሚገባን እኛው ራሳችን ነን፡፡
• የበለፀገች የጋራ ቤታችንን ለጋራ ልጆቻችን ማድረስ የምንፈልግ ከሆነ ዝርፊያውንነና መጠላለፉን ትተን በጋራ መስራት አለብን፡፡
• ዘርና ሀይማኖትን መሰረት አድርገን ሌሎችን ከመቆስቆስ ይልቅ ለጋራ ጥቅምና ድል እንስራ፡፡
• ከመካከላችን ማንም እስከተጎዳ ድረስ ሁላችንም እንጎዳለን፤ ስለዚህ ለሁላችንም የምትሆን አገር በመደመር መገንባት ግድ ይለናል፡፡
• ኢትዮጵያ በሁላችንም ላብና ደም የተሰራች አገር በመሆኗ ባለቤቶቿ ሁላችንም ነን፡፡ አዲሲቷንም ኢትዮጵያ በጋራ ልንገነባ ይገባል፡፡
• ኢህአዴግ ከዳር እሰከዳር የሚሳተፉበት ድርጅት እንዲሆን መስራት ያስፈለጋል፡፡
• ኢህአዴግ አጋር ፓርቲዎችን ወደ ግንባሩ ለማስገባት አቅዶ ቢንቀሳቀስም በአገራዊ ሁኔታው በጥናት እንዲመለስ የቀረበውን ጥናት ማድረስ ባመቻሉ፣ ይህን ምላሽ እንዲያገኝ የሚያስችል ውሳኔ ላይ ይደረሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
• የተጀመረውን የፖለቲካ ምህዳር የማስፋቱ ሂደት የይስሙላ ባለመሆኑ በሁሉም መስክ ተጠናክሮ ይገፋበታል፡፡
• የተፎካካሪዎቻችን ሀሳብ ላይሳማማን ይችላል፣ ነገር ግን የነሱን ሀሳብ በመገደብ ሳይሆን የነሱን ሀሳብ የሚያሸነፍ ሀሳብ ይዘን በመቅረብ ብቻ እንዲሆን እንሰራለን፡፡
• ዛሬ ላይ ሁነን የትላንትናውን ሁነታችንን መቀየር አንችልም፣ ይሁን እንጂ የነገዋን ኢትዮጵያ ተስማምተን መገንባት እንችላለን፡፡
• አዲስ ታሪክ ለመፃፍና ለመስራት በሚያስችል የዘመን አካፋይ አንጓ ላይ እንገኛለን፡፡
• ክልላዊ አስተዳደርን ከብሄር ማንነት ጋር ሳናምታታ ፌደራሊዝሙን ከተገበርነው ለአኛ አውድ ተመራጭነቱ አያጠያይቅም፡፡
• ሰዎች በየትኛው የአገሪቱ ክፍል ተንቀሳቅሰው የመስራት መብታቸው ተረጋግጦ ኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ የምትሆንበት ገፅታም ሊረጋገጥ ይገባል፡፡
• እስካሁን የብሄር ማንነት እና ኢትዮጵያዊ ማንነት ሚዛን ጠብቀው የመጡ ባለመሆናቸው የህዝብ ለህዝብ መድረኮች፣ የባህል መድረኮችና ሌሎች መድረኮችን በማዘጋጀት ከፍ ከፍ የሚያርገንን ስራ መስራት ያስፈልገናል፡፡
• መደመር ሁሉም የየራሱን ጥንካሬ ይዞ ከሆነ እምቅና አዲስ ታሪክ መፃፍ ያስችለናል፡፡
• አገራችን የገጠማት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያው ቀውስ መስኤው ከግብርገብነት ቀውስ የሚመነጭ ነው፡፡
• በሞራልና ግብረገብ የወደቀ ማህበረሰብ ውስጥ ሆነን ሰላም፣ ፍትህ፣ ብልፅግናን ማረጋገጥ ከባድ ነው፡፡
• በሞራል ልዕልና፣ በስነ ምግባር ምሳሌ በመሆን የሀይማኖት ፣ የጎሳና ማህበረሰብ መሪዎች መሪ በመሆን አርዓያነትን በማሳየት ከችግራችን እንዲንወጣ ያስፈልጋል፡፡
• ዜጎች የሚገጥማቻውን መሰረታዊ አገልግሎት የመልካም አስተዳደር ችግር ብሎ መግለፅ አይመጥነውም፡፡
• ስራ አጥነት መቀነስ፣ የዜች የኑሮ ደረጃን ማሳደግ፣ የህግ የበላይነት ማረጋገጥ ላይ ትኩረት የሰጠ ጉባኤ ሆኖ እንደሚቀጥል እምነቴ ነው፡፡
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
• 11ኛው የኢህአዴግ ጉባኤ በለውጥ ምሁዋር ውስጥ በገባንበት ወቅት መካሄዱ ታሪካዊ ያደርገዋል፡፡
• ኢህአዴግ ከዚህ ቀደም የሚያጋጥሙትን ፈተናዎች እያሸነፈ እንደመጣው ሁሉ የሚገጥሙትን ችግሮች እየፈታ የለውጡ ሞተር ሆኖ አገር መምራቱን ይቀጥላል፡፡
• ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ነገዋን በመፈለግ ላይ ያለች፣ በተፈጥሮ ሀብት የበለፀገች አገር ናት፡፡
• የሽግግር ሂደቱን የአገራችን አርሶአደር “የበሬውን ብልሃት እና የወይፈኑን ጉልበት አቀናጅቶ” …እንደሚለው ሁሉ በእኛም ዘንድ ተተኪዎችን በጎ ልምድ ካላቸው በማስተሳሰር አገራዊ ለውጡን ለማሳካት ኢህአዴግ ይታትራል፡፡
• አገር የምታድገው በቅብብሎሽ ነው፡፡
• ያለትላንት ዛሬ አልተገኘምና የትናቱን ትውልድ ማመስገን ያስፈልጋል፡፡ እኛም በተራችን በተተኪ ትውልድ መተካታችን አይዘነጋምና፡፡
• መተካካት የታቀደ ሂደት እንጂ ድንገተኛ ሆኖ እልቂት እንዳያመጣ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
• ይህ ትውልድ ስልጣንን በእጁ አስገብቶ ቀድሞ የነበረውን ነገር በማስፍረስ የተጠመደ መሆን አይገባውም፡፡
• ትላንት እና ዛሬን ያጣጣመች ኢትዮጵያን ለመገንባት ተግቶ መስራት ያስፈልጋል፡፡
• ኢትዮጵያ በላቀ ተግበራቸው ያገነኗት መሪዎች እንደነበሯት ሁሉ፣ ውድቀት የዳረጓትም ነበሩ፡፡ ለጠላቶቿ የሰጧት መሪዎችም ነበሩ፡፡
• ያለመተማማን በማስፋት፣ በጠብና በጦርነት ሊተላለቁ የነበሩ ልጆቿን አስታርቀው ወደ ልዩ ምዕራፍ ያስገቧት ነበሩ፡፡
• በአሁኑ ጊዜ ያለው አመራርስ የትኛውን ታሪክ ይደግማል? የሚለው ጥያቄ ለእኛ ቀርቧል፡፡
• የአገራችን እጣ ፈንታ አሁን እድሉን ባገኙት ፖለቲከኞች እንዲሁም በህዝቧ እጅ ነው፡፡
• ዘመናዊና ስልጡን አገር ለመፍጠር ህዝብን የስልጣን ልዕልና መገለጫ አድርጎ የሚቀበል ስርዓት መፍጥር ሲሳካልን ነው፡፡
• ህዝብ የሚያምናቸውና የሚከተላቸው ልዩ ልዩ የማህበረሰብ መሪዎችን ካገኘን በእምነት፣ በባህል፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በፖለቲካ፣ በጦር አመራር፣ በምህንድስና፣ በስፖርትና ኪነጥበብብ፣ በሌሎች ዘርፎችም ጭምር ከተዋጣልን አገር የተሳካ ጉዞ አድርጋ በከፍታ ጉዞ ላይ ትደርሳለች፡፡
• የምንፈልጋትን አገር መምሰልና መሆን የሚገባን እኛው ራሳችን ነን፡፡
• የበለፀገች የጋራ ቤታችንን ለጋራ ልጆቻችን ማድረስ የምንፈልግ ከሆነ ዝርፊያውንነና መጠላለፉን ትተን በጋራ መስራት አለብን፡፡
• ዘርና ሀይማኖትን መሰረት አድርገን ሌሎችን ከመቆስቆስ ይልቅ ለጋራ ጥቅምና ድል እንስራ፡፡
• ከመካከላችን ማንም እስከተጎዳ ድረስ ሁላችንም እንጎዳለን፤ ስለዚህ ለሁላችንም የምትሆን አገር በመደመር መገንባት ግድ ይለናል፡፡
• ኢትዮጵያ በሁላችንም ላብና ደም የተሰራች አገር በመሆኗ ባለቤቶቿ ሁላችንም ነን፡፡ አዲሲቷንም ኢትዮጵያ በጋራ ልንገነባ ይገባል፡፡
• ኢህአዴግ ከዳር እሰከዳር የሚሳተፉበት ድርጅት እንዲሆን መስራት ያስፈለጋል፡፡
• ኢህአዴግ አጋር ፓርቲዎችን ወደ ግንባሩ ለማስገባት አቅዶ ቢንቀሳቀስም በአገራዊ ሁኔታው በጥናት እንዲመለስ የቀረበውን ጥናት ማድረስ ባመቻሉ፣ ይህን ምላሽ እንዲያገኝ የሚያስችል ውሳኔ ላይ ይደረሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
• የተጀመረውን የፖለቲካ ምህዳር የማስፋቱ ሂደት የይስሙላ ባለመሆኑ በሁሉም መስክ ተጠናክሮ ይገፋበታል፡፡
• የተፎካካሪዎቻችን ሀሳብ ላይሳማማን ይችላል፣ ነገር ግን የነሱን ሀሳብ በመገደብ ሳይሆን የነሱን ሀሳብ የሚያሸነፍ ሀሳብ ይዘን በመቅረብ ብቻ እንዲሆን እንሰራለን፡፡
• ዛሬ ላይ ሁነን የትላንትናውን ሁነታችንን መቀየር አንችልም፣ ይሁን እንጂ የነገዋን ኢትዮጵያ ተስማምተን መገንባት እንችላለን፡፡
• አዲስ ታሪክ ለመፃፍና ለመስራት በሚያስችል የዘመን አካፋይ አንጓ ላይ እንገኛለን፡፡
• ክልላዊ አስተዳደርን ከብሄር ማንነት ጋር ሳናምታታ ፌደራሊዝሙን ከተገበርነው ለአኛ አውድ ተመራጭነቱ አያጠያይቅም፡፡
• ሰዎች በየትኛው የአገሪቱ ክፍል ተንቀሳቅሰው የመስራት መብታቸው ተረጋግጦ ኢትዮጵያ ህብረ ብሄራዊ የምትሆንበት ገፅታም ሊረጋገጥ ይገባል፡፡
• እስካሁን የብሄር ማንነት እና ኢትዮጵያዊ ማንነት ሚዛን ጠብቀው የመጡ ባለመሆናቸው የህዝብ ለህዝብ መድረኮች፣ የባህል መድረኮችና ሌሎች መድረኮችን በማዘጋጀት ከፍ ከፍ የሚያርገንን ስራ መስራት ያስፈልገናል፡፡
• መደመር ሁሉም የየራሱን ጥንካሬ ይዞ ከሆነ እምቅና አዲስ ታሪክ መፃፍ ያስችለናል፡፡
• አገራችን የገጠማት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያው ቀውስ መስኤው ከግብርገብነት ቀውስ የሚመነጭ ነው፡፡
• በሞራልና ግብረገብ የወደቀ ማህበረሰብ ውስጥ ሆነን ሰላም፣ ፍትህ፣ ብልፅግናን ማረጋገጥ ከባድ ነው፡፡
• በሞራል ልዕልና፣ በስነ ምግባር ምሳሌ በመሆን የሀይማኖት ፣ የጎሳና ማህበረሰብ መሪዎች መሪ በመሆን አርዓያነትን በማሳየት ከችግራችን እንዲንወጣ ያስፈልጋል፡፡
• ዜጎች የሚገጥማቻውን መሰረታዊ አገልግሎት የመልካም አስተዳደር ችግር ብሎ መግለፅ አይመጥነውም፡፡
• ስራ አጥነት መቀነስ፣ የዜች የኑሮ ደረጃን ማሳደግ፣ የህግ የበላይነት ማረጋገጥ ላይ ትኩረት የሰጠ ጉባኤ ሆኖ እንደሚቀጥል እምነቴ ነው፡፡
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ⬆️የኢህአዴግ 11ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የመክፈቻ ስነስርዓት እንደቀጠለ ይገኛል።
ፎቶ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ 11ኛውን የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔን የሚመሩ አራት #የፕሬዚዲየም አባላት ተመርጠዋል።
የፕሬዚዲየም አባላት ሆነው የተመረጡት የአራቱ እህት ድርጅቶች ሊቃነመናብርት ናቸው። በዚህም መሰረት፦
1. የኦዴፓ ሊቀመንበር ዶክተር አብይ አህመድ
2. የአዴፓ ሊቀመንበር አቶ ደመቀ መኮንን
3. የደኢህዴን ሊቀመንበር ወይዘሮ መፈርያት ካሚል
4. የህወሃት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ናቸው።
በጉባዔው የኢህአዴግ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር የጉባኤውን ዝግጅት ሪፖርትን ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርቱም ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፕሬዚዲየም አባላት ሆነው የተመረጡት የአራቱ እህት ድርጅቶች ሊቃነመናብርት ናቸው። በዚህም መሰረት፦
1. የኦዴፓ ሊቀመንበር ዶክተር አብይ አህመድ
2. የአዴፓ ሊቀመንበር አቶ ደመቀ መኮንን
3. የደኢህዴን ሊቀመንበር ወይዘሮ መፈርያት ካሚል
4. የህወሃት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ናቸው።
በጉባዔው የኢህአዴግ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር የጉባኤውን ዝግጅት ሪፖርትን ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርቱም ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ የኢህአዴግ ጉባኤ⬇️
ኢህአዴግ በ11ኛው ጉባኤው #በርዕዮተ_ዓለም ለውጥ ላይም ሆነ በአርማ ለውጥ ላይ #እንደማይወያይ ተገልጿል። የጉበኤውን ውሎ በተመለከተ መግለጫ የሰጡት የጉባኤው ቃል አቀባይ አቶ ፍቃዱ ተሰማ እንደገለፁት ጉባኤው አጀማመሩ ያማረና ከሌላው ጊዜ በበለጠ በርካቶችን ያሳተፈ ነበር ብለዋል።
የተፎካከሪ ፓርቲዎች መሳተፍ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓና የእስያ ሀገራትን የወከሉ የፓርቲ አመራሮችም በመክፈቻው መገኘታቸው ጉባኤውን #ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል።
ጉባኤው ከመክፈቻ ፕሮግራሙ በኋላ በጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ የቀረበለት ሪፖርት ላይ መወያየቱን እና ይህ በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።
ጉባኤው በቆይታው የሚመክርባቸው በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም በርዕዮተ ዓለም ለውጥም ሆነ በስምና አርማ ለውጥ ላይ እንደማይመክር ግን ቃል አቀባዩ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አስታውቀዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢህአዴግ በ11ኛው ጉባኤው #በርዕዮተ_ዓለም ለውጥ ላይም ሆነ በአርማ ለውጥ ላይ #እንደማይወያይ ተገልጿል። የጉበኤውን ውሎ በተመለከተ መግለጫ የሰጡት የጉባኤው ቃል አቀባይ አቶ ፍቃዱ ተሰማ እንደገለፁት ጉባኤው አጀማመሩ ያማረና ከሌላው ጊዜ በበለጠ በርካቶችን ያሳተፈ ነበር ብለዋል።
የተፎካከሪ ፓርቲዎች መሳተፍ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓና የእስያ ሀገራትን የወከሉ የፓርቲ አመራሮችም በመክፈቻው መገኘታቸው ጉባኤውን #ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል።
ጉባኤው ከመክፈቻ ፕሮግራሙ በኋላ በጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ የቀረበለት ሪፖርት ላይ መወያየቱን እና ይህ በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።
ጉባኤው በቆይታው የሚመክርባቸው በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም በርዕዮተ ዓለም ለውጥም ሆነ በስምና አርማ ለውጥ ላይ እንደማይመክር ግን ቃል አቀባዩ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አስታውቀዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#updateሀዋሳ የኢህአዴግ ጉባኤ⬇️
-የኢሕአዴግ ጉባዔ ለውጡን #በአዎንታዊነት የገመገመ መሆኑ ተገለጸ።
- መፈጸም የማይችሉ አመራሮችም ሆኑ የግንባሩ አባል ፓርቲዎች መቀጠል #የለባቸውም የሚል #ቀይ_መስመር ተለይቷል
▪️የኢሕአዴግ 11ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ የጥልቅ ተሃድሶ ያለበትን ደረጃና የመጀመሪያ ደረጃ ትሩፋቶችን በማድነቅ እየገመገመ መሆኑንና ቀጣይ የለውጡ አቅጣጫን በተመለከተ በመወያየት ላይ እንደሚገኝ የጉባዔው ቃል አቀባይ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ፡፡
በተለይም ኢሕአዴግ የአመራር ለውጥ ከማድረጉ በፊት ራሱ ግንባሩና አገሪቱ በመስቀለኛ መንገድ ላይ እንደነበሩ፣ በአገሪቱም #የመበተን አደጋ ተጋርጦ እንደነበር መገምገሙን አክለዋል፡፡
የአመራር ለውጥ ከተደረገ በኋላ ግን ብዝሃነትን፣ #ኢትዮጵያዊነትንና በማኅበረሰቡ ላይ ተስፋን የሚጭሩ የፖለቲካ ተግባራት መፈጸማቸውን፣ ይህም በአገሪቱ የፖለቲካ መረጋጋት መፍጠሩ በጉባዔው እንደተገመገመ ገልጸዋል፡፡
በዚሁ ጉዳይ ላይ ግምገማው እንደቀጠለ የወደፊት የፖለቲካ ሪፎርሙ አቅጣጫ ተቋማዊ መልክ እንዲይዝና በግምባሩ አባል ድርጅቶችና አመራሮች መካከል መልካም ግንኙነትና የዓላማ አንድነት መፍጠር የጸጸት ዶሴውን መዝጋት፣ በይቅርታና ቅን ልቦና ወደፊት መሄድ እንደሚገባ መገምገሙንና ውይይቱም መቀጠሉን ቃል አቀባዩ አስረድተዋል፡፡
በመደመር ፍልስፍና ላይ ግልጽነት የፈጠረ ውይይት መደረጉንና የማይታለፉ ቀይ መስመሮችን በተመለከተ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከቀይ መስመሮቹ መካከል መፈጸም የማይችሉ አመራሮችም ሆኑ የግንባሩ አባል ፓርቲዎች እንደማይቀጥሉ፣ ሥርዓት
አልበኝነትን አለመታገስ እንደሚገኙበት ገልጸዋል፡፡ ቃል አቀባዩ በጉባዔው ላይ የተነሱ የልዩነት ሐሳቦችን ሳይጠቅሱ ያለፉ ሲሆን፣ ከጋዜጠኞች ሊነሱ የሚችሉ ጥያቄዎችን #እንደማይቀበሉ በመግለጽ መግለጫውን አጠናቀዋል፡፡
ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
-የኢሕአዴግ ጉባዔ ለውጡን #በአዎንታዊነት የገመገመ መሆኑ ተገለጸ።
- መፈጸም የማይችሉ አመራሮችም ሆኑ የግንባሩ አባል ፓርቲዎች መቀጠል #የለባቸውም የሚል #ቀይ_መስመር ተለይቷል
▪️የኢሕአዴግ 11ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ የጥልቅ ተሃድሶ ያለበትን ደረጃና የመጀመሪያ ደረጃ ትሩፋቶችን በማድነቅ እየገመገመ መሆኑንና ቀጣይ የለውጡ አቅጣጫን በተመለከተ በመወያየት ላይ እንደሚገኝ የጉባዔው ቃል አቀባይ አቶ ፍቃዱ ተሰማ ገለጹ፡፡
በተለይም ኢሕአዴግ የአመራር ለውጥ ከማድረጉ በፊት ራሱ ግንባሩና አገሪቱ በመስቀለኛ መንገድ ላይ እንደነበሩ፣ በአገሪቱም #የመበተን አደጋ ተጋርጦ እንደነበር መገምገሙን አክለዋል፡፡
የአመራር ለውጥ ከተደረገ በኋላ ግን ብዝሃነትን፣ #ኢትዮጵያዊነትንና በማኅበረሰቡ ላይ ተስፋን የሚጭሩ የፖለቲካ ተግባራት መፈጸማቸውን፣ ይህም በአገሪቱ የፖለቲካ መረጋጋት መፍጠሩ በጉባዔው እንደተገመገመ ገልጸዋል፡፡
በዚሁ ጉዳይ ላይ ግምገማው እንደቀጠለ የወደፊት የፖለቲካ ሪፎርሙ አቅጣጫ ተቋማዊ መልክ እንዲይዝና በግምባሩ አባል ድርጅቶችና አመራሮች መካከል መልካም ግንኙነትና የዓላማ አንድነት መፍጠር የጸጸት ዶሴውን መዝጋት፣ በይቅርታና ቅን ልቦና ወደፊት መሄድ እንደሚገባ መገምገሙንና ውይይቱም መቀጠሉን ቃል አቀባዩ አስረድተዋል፡፡
በመደመር ፍልስፍና ላይ ግልጽነት የፈጠረ ውይይት መደረጉንና የማይታለፉ ቀይ መስመሮችን በተመለከተ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከቀይ መስመሮቹ መካከል መፈጸም የማይችሉ አመራሮችም ሆኑ የግንባሩ አባል ፓርቲዎች እንደማይቀጥሉ፣ ሥርዓት
አልበኝነትን አለመታገስ እንደሚገኙበት ገልጸዋል፡፡ ቃል አቀባዩ በጉባዔው ላይ የተነሱ የልዩነት ሐሳቦችን ሳይጠቅሱ ያለፉ ሲሆን፣ ከጋዜጠኞች ሊነሱ የሚችሉ ጥያቄዎችን #እንደማይቀበሉ በመግለጽ መግለጫውን አጠናቀዋል፡፡
ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia