TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#update የፀረ ሽብር ህግ⬇️

የጠቅላይ አቃቢ ህግ፣ የጸረሽብር ጉባኤ ጽ.ቤት እና የሲቪክ ማህበራት በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት የጸረ ሽብር ህጉ እና የሲቪክ ማህበራት አሰራር ችግር ያለባቸው በመሆኑ ከህዝቡ #ሃሳብ ተሰብስቦ #ይሻሻላል፡፡

የጸረ ሽብር ህጉን ለማሻሻል ከነሃሴ 25 ጀምሮ በዋና ዋና ከተሞች ላይ ህዝባዊ ውይይት ተደርጎ ሃሳብ እንደሚሰበሰብ ነው በጋዜጣዊ መግለጫው የተመለከተው፡፡

በሲቪክ ማህበራት አሰራር ላይ ያሉትን አሰራሮች ለማሻሻል ደግሞ ከመስከረም 10 እስከ 14 ድረስ ከህብረተሰቡ ጋር ውይይቶች ይካሄዳሉ፤ በዚህም ህብረተሰቡ ሰፊ ተሳትፎ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የሲቪክ ማህበራት አሰራርን ችግሮች የሚያጠና ቡድን ተቋቁሞ ስራ ጀምሯል ነው የተባለው በመግለጫው፡፡

©AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia