TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የፌዴራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ጥያቄ አላቀረብንም " - አቶ ጌታቸው ረዳ
የፌዴራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ጥያቄ አላቀረብንም ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አስታውቀዋል።
ክልሉ ላይ " የህግ ተቀባይነት ያጡ እና ከጦርነት ትርፍ እናገኛለን የሚሉና በጥቅም የተሳሰሩ የተወሰኑ የህወሃት አንጃዎች የተወሰኑ ከፍተኛ መኮንኖችን በመያዝ ክልሉን አደጋ ላይ እየከተቱ ነው " ብለዋል።
" ይህ እንቅስቃሴ ትግራይን ወደ ሌላ የትርምስ ምእራፍ እየወሰደ ይገኛል " ሲሉ ገልጸዋል።
ይህንን አስመልክቶ የፌዴራል መንግስት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ጊዜያዊ አስተዳደሩ ስራውን እንዲሰራ ደጋፍ እንዲያደርግ እንጂ ጦር አዝምቶ ጣልቃ እንዲገባ ጥያቄ አላቀረብንም ብለዋል።
በዚህ ደረጃ ጥያቄ ለማቅረብ የሚያስችል ሁኔታም የለም ሲሉ ገልጸዋል።
" ክልሉ ወደ ሌላ ጦርነት መግባት የለበትም። ጊዜያዊ አስተዳደሩ የፌዴራል መንግስቱ ውሳኔ አካል ነው። የፌዴራል መንግስቱ አግባብነት ያለው ሃላፊነት መውሰድ ይኖርበታል " ብለዋል።
የትግራህ ህዝብ ዳግም ወደ ግጭት እንዳይገባና ሰላምን መፍጠር የሚቻልባቸው እድሎችን ማጽናት እንደሚገባ ጠቁመዋል። #EPA
@tikvahethiopia
የፌዴራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ ጥያቄ አላቀረብንም ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አስታውቀዋል።
ክልሉ ላይ " የህግ ተቀባይነት ያጡ እና ከጦርነት ትርፍ እናገኛለን የሚሉና በጥቅም የተሳሰሩ የተወሰኑ የህወሃት አንጃዎች የተወሰኑ ከፍተኛ መኮንኖችን በመያዝ ክልሉን አደጋ ላይ እየከተቱ ነው " ብለዋል።
" ይህ እንቅስቃሴ ትግራይን ወደ ሌላ የትርምስ ምእራፍ እየወሰደ ይገኛል " ሲሉ ገልጸዋል።
ይህንን አስመልክቶ የፌዴራል መንግስት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ጊዜያዊ አስተዳደሩ ስራውን እንዲሰራ ደጋፍ እንዲያደርግ እንጂ ጦር አዝምቶ ጣልቃ እንዲገባ ጥያቄ አላቀረብንም ብለዋል።
በዚህ ደረጃ ጥያቄ ለማቅረብ የሚያስችል ሁኔታም የለም ሲሉ ገልጸዋል።
" ክልሉ ወደ ሌላ ጦርነት መግባት የለበትም። ጊዜያዊ አስተዳደሩ የፌዴራል መንግስቱ ውሳኔ አካል ነው። የፌዴራል መንግስቱ አግባብነት ያለው ሃላፊነት መውሰድ ይኖርበታል " ብለዋል።
የትግራህ ህዝብ ዳግም ወደ ግጭት እንዳይገባና ሰላምን መፍጠር የሚቻልባቸው እድሎችን ማጽናት እንደሚገባ ጠቁመዋል። #EPA
@tikvahethiopia