TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
" ከየካቲት 24 በኋላ የፋይዳ መታወቂያ የሌለው ደንበኛ የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር ትኬት መቁረጥ አይችልም " - የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር

የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር ለመንገደኞች የጉዞ ትኬት የሚያገኙበትን መንገድ ከሰኞ የካቲት 17/2017 ዓ/ም ጀምሮ  ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ማድረጉን ገልጿል።

ከሁለት ቀን በፊት የተጀመረውን በኦንላይን ትኬት የመቁረጥ ሂደት አገልግሎቱን ለማግኘት የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ መደረጉን የኢትዮጵያ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር የኮምዩኒኬሽን ባለሞያ የሆኑት ወ/ሮ እስራኤል ወልደ መስቀል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ወ/ሮ እስራኤል " ማስታወቂያዎችን ስንሰራ የቆየን በመሆኑ የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ ነው ነገር ግን ይሄንን ሳምንት ልዩ በሆነ መንገድ እና ሰውም የአጠቃቀም ጉድለት ስላለ የጉዞ ትኬት እየቆረጥን እንገኛለን ከሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ በኃላ ግን ያለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የባቡሩን ትኬት ማግኘት አይቻልም " ብለዋል።

ክፍያው የሚፈጸመው በቴሌ ብር ሲሆን አገልግሎቱን ለማግኘት ለሃገር ውስጥ ተጠቃሚዎች የፋይዳ የምዝገባ ቁጥራቸውን ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ተጠቃሚዎች ደግሞ ፓስፖርታቸውን በመጠቀም ትኬት ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል።

ባለሞያዋ በትኬት ዋጋ ላይ ምንም አይነት ጭማሪ አለመኖሩን አንስተው በነባሩ ዋጋ ዲጂታላይዝ ብቻ መደረጉን ጠቁመዋል።

ከዚህ ቀደም አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ፉሪ የሚገኙ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎች አሰራሩ ዲጂታላይዝ ስለሆነ የመንገደኞችን የአገልግሎት ትኬት የመቁረጥ ስራ እንደማይሰሩ ወ/ሮ እስራኤል ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
“ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር ነው የሚሸጠው ” - የጋሞ ልማት ማኀበር

በተለይ የውጪ አገር የገበያ ትስስር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ ከአዞ ሽያጭ እስከ 60 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ እያጣች መሆኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባምንጭ የጋሞ ልማት ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

ከሦስት ዓመታት በፊት ትንሽ የአዞ ስጋና ቆዳ ለውጪ አገራት ይሸጥ እንደነበር፣ ከዚያ በኋላ በገበያ ትስስር ክፍተት ገቢው በመቀዛቀዙ እንደ አዲስ ለማንሰራራት እየተሰራ መሆኑን ማኀበሩ አስረድቷል።

ስለአዞ ሽያጭ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው የማህበሩ አርባምንጭ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ዳኘ፣ “ ከ3 አመታት በፊት 10፣ 15 ነበር የሚሸጠው። ከ3000 እስከ 5000 አዞዎች ሲሸጡ የነበረው ከ10 ዓመት በፊት ነው። እየቀሰ መጥቷል ” ብለዋል።

የማኀበሩ ሥራ የአርባምንጭ አስኪያጅ አቶ ዲዊት ዳኘ ምን አሉ ?

“ የአዞ ቆዳ የሽያጭ ሂደቱ ተቀዛቅዞ ቆይቶ አሁን ሽያጭ አልተጀመረም። አሁን በማኀበሩ ተወስዶ እየተሰራ ነው። ቆዳቸው ለሽያጭ የደረሱ ከ2500  በላይ አዞዎች አሉን። እንዴት እንደሚቀጥል ከአገር ውስጥ ካምፓኒዎች ጋር እያወራን ነው።

አሁን ተነጋግረን የውል ሂደት ላይ ነው ያለነው እሱን ጨርሰን ሽያጩ ይካሄዳል ብለን እናስባለን። በፊት ሲሸጥ የነበረው ቆዳው ብቻ ነው። ግን የአዞ ስጋው፣ ጥርሱ፣ ይፈለጋል። ስጋው በሌሎች አገራት በጣም ይፈለጋል።

አሁን 4,000 የአዞ ጫጩቶችን ለመሰብሰብ እንቁላል ዝግጁ ሆኖ ነው ያለው። ከሦስት ወራት በኋላ ጫጩት ከተፈለፈለ በኋላ ከሀይቁ ወደ ማኀበር ይመጣሉ።

የአዞ ቆዳና ስጋ በጣም ዋጋው ውድ ነው። ስለዚህ ትክክለኛ ማርኬት ሊንኬጅ ተፈጥሮ ስርዓቱ ቢዘረጋ እንደ አገር ትልቅ ገቢ እናገኛለን። በተለይ በዘርፉ የሚሰሩ የውጪ አገር ካምፓኒዎችን እያነጋነርን ነው ” ብለዋል።

ከ2,500 በላይ አዞዎች ለሽያጭ ቢቀርቡ ምን ያክል ገቢ ማግኘት ይቻላል ? ስንል የጠየቅናቸው አቶ ዳዊት፣ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር እንደሚሸጥ፣ የአንድ አዞ ቆዳ እስከ 45 ሴንቲሜትር እንደሚሆን፣ አንድ አዞ በትንሹ እስከ 22 ሺሕ ብር እንደሚሸጥ፣ በጠቅላላ ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ሊገኝ እንደሚችል አስረድተዋል።

በማኀበሩ ስንት ሠራተኞች አሉ ? የአዞ ስጋ ምግብነት ላይ ይውላል ወይ ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ስጋ ይበላል። በኛ አልተለመደም። ግን የኛ ሰዎች የ40 ዓመት ልምድ አላቸው። ብራንቹ ተቋቁሞ 41 ዓመቱ ነው። ረጅም ልምድ ያላቸው ሰዎች አዞ የመመገብ ልምድ አላቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

አቶ ዳዊትና አንድ የማኀበሩ አስጎብኝ በኢትዮጵያ ብዙ እንዳልተለመደ፣ ኬኒያን ጨምር በሌሎች አካባቢዎች አዞ ለምግብነት እንደሚውል ተናግረዋል።

አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ሬስቶራንት ለመክፈት ” እንዳሰቡ ገልጸው፣ “ ፈረንጆች ይመጣሉ እዚህ ይመገባሉ፤ ቀስ በቀስ የኛ ሰዎችም እያዩ እየተመገቡ ይሄዳሉ ” ነው ያሉት።

አክለው፣ በማኀበሩ ወደ 35 ገደማ ሠራተኞች እንዳሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ሲሆን፣ የማኀበሩ አስጎብኝ በሰጡት ገለጻ ደግሞ፣ “60 በመቶ የሚሆኑት ሰራተኞች የአዞ ስጋ ይመገባሉ” ብለዋል።

አንድ አዞ ለሽያጭ ለመቅረብ ብቁ እስከሚሆን ድረስ 62 ኪሎ ግራም ስጋ እንደሚመገብ፣ አዞ የሚመገበው የአሳ፣ የአዞ ስጋ እንደሆነ፣ አሳማ ሌሎች የእንስሳት ዝርያዎች እንዳሉ፣ የህክምናና ሌሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ማኀበሩ በአመት እስከ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚደረግ ተመልክቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፐርፐዝብላክ ° " ሥራ ላይ የነበሩ ሱቆችም የቤት ኪራይ መክፈል ስላልተቻለ ሊዘጉ ነው " - የፐርፐዝ ብላክ ባለአክሲዮኖች ° " በፍርድ ቤት የተያዘ ጉዳይ ስላለ ምንም  አይነት መግለጫ አንሰጥም " - ድርጅቱ የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ባለአክሲዮኖች፣ የድርጅቱ አካላት መታሰራቸውን ተከትሎ ድርጅቱ ላይ ባላቸው ሼር ላይ ሥጋትና ቅሬታ እንዳደረባቸው፣ ለቅሬታቸው አፋጣኝ ምላሽ  እንዲሰጣቸው በቲክቫህ…
“ ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል ” - የፐርፐዝ ብላክ ባለአክሲዮኖች

ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ሕብረት ባንክ ካለው ገንዘብ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለውን ገንዘብ እንዲያንቀሳቅስ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢሰጥም በዐቃቢ ህግ ይጎባኝ ውሳኔው መታገዱን የፍርድ ቤት ሰነድና ባለአክሲዮኖች አመለከቱ።

ሁነቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዱት ባለአክሲዮኖች የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንት ለሰባት ወራት ተዘግቶ መቆየቱን፣ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለደመወዝና ሥራ ማስኬጃ ክርክር ሲካሄድ ቆይቶ እንደነበር ገልጸዋል።

በክርክር ሂደቱም፣ ፍርድ ቤት ሕብረት ባንክ ከተቀመጠው ገንዘቡ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለው የፐርፐዝ ብላክ ገንዘብ እንዲንቀሳቀስ፣ ለማንቀሳቀስ አስተዳዳሪ እንዲሾም ወስኖ እንደነበር አስረድተዋል።

“ነገር ግን ዐቃቤ ሕግ ውሳኔውን በመቃወም ይግባኝ ጠይቆ የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ አሳግዶታል” ብለዋል።

“ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል” ያሉት ባለክሲዮኖቹ፣ “ድርጅቱ የሚፈርስ እንኳን ከሆነ አግባብ ባለው መንገድ መፍረስ ነበረበት እጅግ ከባድ ሁኔታ ተፈጥሯል” ሲሉ አማረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ሰነድ፣ “መዝገቡ ከቀጠሮ በፊት የቀረበው ይግባኝ ባይ በቀን 10/6/2017 ዓ/ም በተፃፈ አቤቱታ ያቀረዝነው ይግባኝ ታይቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የፌ/ከፍ/ፍርድ ቤት በወ/መ/ቁ 326384 የሰጠው ውሳኔ ታግዶ እንዲቆይ እንዲታዘዝልን በሚል ባቀረበው አቤቱታ ነው” ይላል።

አክሎም፣ ይግባኝ ቅሬታ ለመስማት ለ20/06/2017 ዓ/ም የተያዘው ቀጠሮ ተሰብሮ የእግድ አቤቱታውን በመመርመር ዝርዝር ትዕዛዝ መስጠቱን ያስረዳል።

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንቶች መዘጋታቸው፣ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሃ እሸቱ (ዶ/ር) አገር መውጣታቸው አይዘነጋም።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
“ የጤና መድን ክፍያ በሚል ማህበረሰቡ ከ3,000 ብር  በላይ በግዴታ እንዲከፍል እየተደረገ ነው ” - የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች

የጤና መድን ክፍያ በሚል ማህበረሰቡ ከ3,000 ብርና ከዚያ በላይ፣ ለኮሪደር ልማት ከ500 እስከ 20 ሺሕ ብር  በግዴታ እንዲከፍል እየተደረገ መሆኑን የባሕር ዳር ከተማ ነዋረዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

“ ከትንንሽ ምግብ ቤት ጀምሮ በማንኛውም የንግድ ሥራ የተሰማራ ቤተሰብ የሌለውንም ጨምሮ ነው እያስገደዱና የማይከፍለውን እያሸጉ ያሉት ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ከዚህ ቀደም ትዳር መስርቶ፣ ወልዶ የሚኖር ሰው አባል ሆኖ የአባልነት ክፍያ ነበር የሚከፍለው ለጤና መድን አሁን ግን ትዳር የሌላቸው በንግድ ሥራ የተሰማሩ ወጣቶችን ጭምር አባል ሳያደርጉ ብር ብቻ እያስከፈሉ ነው ” ብለዋል።

በሌላ በኩል፣ “ ለኮሪደር ልማት በሚል በማንኛውም ንግድ ሥራ የተሰማራ ሰው ተገዶ እንዲከፍል እየተደገ ነው ” ሲሉ ነዋሪዎቹ አማረዋል።

አክለውም ፦

“ ነዋሪውበኑሮ ውድነት እየተሰቃየ ነው ያለው። በአነስተኛ ንግድ የተሰማራው ነጋዴም ስራ ቆሞበታል። ምክንያቱም ተጠቃሚ የለም።

ህዝቡ ግብር ከፍሎ እንደገና ‘ለኮሪደር ልማት፣ ለጤና መድን’ ሲጨምርበት ከአቅም በላይ ሆኖበታል። ይሄ ነገር ከተጀመረ ቆይቷል። ግዳጁ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል። 

የማህበረሰቡም፣ ‘የኑሮ ውድነት ጫናው ቢኖርብንም በህግ አግባብ የተጣለብንን ግብር በሰዓቱ እየከፈልን ነው የምንሰራው። አሁን ላይ ስራ ተቀዛቅዟል። ተጨማሪ ክፍያ የመክፈል አቅም የለንም’ የሚል ቅሬታ አለው።

የኮሪደር ልማቱን ክፍያ በሚመለከት የከተማ አስተዳደሩ ከከፍተኛ ባለሀብቶች ጋር ውይይት አድርጎ ልማቱን እንደሚደግፉ ተስማምተዋል። ነገር ግን ዝቅተኛ ነጋዴዎች ተሳታፊ አልነበሩም። እነሱም ቢሆኑ ልማቱን ይደግፋሉ ነገር ግን ክፍያው አቅምን ያገናዘበ አይደለም።

በካሬታ ውሃና ሌሎች ሥራዎችን የማጓጓዝ ስራ ከሚሰሩ ልጆች ጀምሮ እስከ ቤት አከራይ ለኮሪደር ልማት መዋጮ እየተጠየቀ ነው። ዝቅተኛው 500 ብር ሲሆን፣ እስከ 20,000 ብር የተጠየቁ አሉ። 20 ሺሕ ብር አከራይ ብቻ ነው የሚከፍለው ” ሲሉ አማረዋል።

ነዋሪዎቹ ቅሬታውን ምላሽ እንዲሰጥበት የባሕርዳር ከተማ አስተዳደርን የጠቆሙ ሲሆን ምን ምላሽ እንዳላቸው የጠየቅናቸው  የከተማው ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ቅሬታውን ከሰሙ በኋላ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ጤና መድን አገልግሎትን የጠየቀ ሲሆን፣ ምላሹ ሲገኝ የሚቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#የአርሶአደሮችድምጽ🔈

🔴 “ ለሦስት ዓመታት ምንም የካሳ ክፍያ አልተከፈለንም፡፡ የምንመገበው አጥተን ለልመና ተዳርገናል” - አርሶ አደሮች

➡️ “ ክፍያዎቹን በተገቢው በሚፈለገው አግባብ እየከፈልን አይደለም ” - የአማራ ክልል መንገዶች
ቢሮ

በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ ከቸና እስከ መካነ ኢየሱስ ከተማ ባለው የመንገድ ፕሮጀክት መሬት የተወሰደባቸው ወደ 40  አርሶ አደሮች ለ3 ዓመታት የካሳ ባለመከፈሉ ለልመና መዳረጋቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

አርሶ አደሮቹ ስለቅሬታቸው ምን አሉ?

“ ከቸና እስከ መካነ ኢየሱስ ከተማ ድረስ ባለው ፕሮጀክት ለተወሰደው መሬት 2014 ዓ/ም የካሳ ክፍያ ብናውቅም 40 አርሶ አደሮች ለ3 ዓመታት ካሳ አልተከፈለም፡፡

በአሰራሩ መሰረት የካሳ ክፍያ እንደወቅቱ ሁኔታ እየታዬ በየስድስት ወሩ ማሻሻያ ይደረግበታል ክፍያ ሳይፈጸም ከቆዬ። የኛ ግን ለ3 ዓመት ማሻሻያ አልተደረገበትም፡፡

ከዓመታት በፊት የተገመተው ካሳ አሁንም ባለበት ነው። ከ3 ዓመታት በፊት የነበረው የገንዘብ ዋጋ ከአሁኑ ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት አለው። ያም ሆኖ ግን ከዓመታት በፊት የነበረው ካሳም እየተከፈለን አይደለም፡፡

የመካነ ኢየሱስ ከተማ ነዋሪም ቤቱን ሽጦ እንዳይመገብ መስመር ዳር ሊፈርስ ምልክት ስለተደረገበት መሸጥ አይቻልም፡፡ የገጠሩ አርሶ አደርም የተወሰደብን መሬት የአትክልት ማምረቻ ጭምር ማሳ ነው፡፡

አርሶ አደሩ እስከ 3 ማሳ ነበረው በግራና ቀኝ መንገድ ፕሮጀክቱ የደረደበት፡፡ አርሶ አደሩ ወይ አርሶ አልተጠቀመ ወይ የካሳ ክፍያ አላገኘ፡፡ አትክልቱ እንኳ አድጎ ጥቅም እንዳይሰጥ በለጋው ተቀጭቷል ” ብለዋል።


በ2014 ዓ/ም በነበረው የካሳ ተመን መሰረት ከ200 ሺሕ እስከ 1 ሚሊዮን ብር በላይ የተገመተላቸው አርሶ አደሮች እንዳሉ ገልጸው፣ በአሁኑ የገንዘብ የመግዛት አቅም ዋጋ ተተምኖ በቶሎ ካሳው እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለምን የአርሶ አደሮቹ ካሳ በወቅቱ አልተከፈለም፣ መቼስ ይከፈላለቸዋል? ሲል የአማራ ክልል መንገዶች ባለስልጣንን ጠይቋል።

የአማራ ክልል መንገዶች ቢሮ ምን መሰለ?

“ የወሰን ማስከበር ክፍያዎች በመንግስት በጀት ከምንከፍላቸው ክፍያዎች አንዱ ነው። ግን ክፍያዎቹን በተገቢው በሚፈለገው አግባብ እየከፈልን አይደለም።

ይሄ ደግሞ የተፈጠረው ለመስሪያ ቤታችን ከመንግስት በሚለቀቀው በጀት ጋር ተያይዞ እየገጠመን ባለው የበጀት ችግር ነው።

ይሄን ችግር እናውቀዋለን። ለመፍታት እየታገልን ያለነው ነው። ስለዚህ የበጀት ችግሩ እንደተፈታልን፣ መፈታት ብቻም ሳይሆን እንደተቃለልን ቀሪ ክፍያዎችን ባለው ፕራዮሪቱ ኦርደር መሠረት እንከፍላለን ” ብሏል።

(ጉዳዩን እስከመጨረሻው የምንከታተለው ይሆናል
)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#የሠራተኞችድምጽ🔈

🔴 “ የምናደርገው አጥተን ነው ተማረን በእንባ የወጣነው። 3 ልጆች አሉኝ  በ1,000 ብር ደመወዝ ነው የምተዳደረው፤ አሁን የት እንውደቅ ? ” - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች

➡️ “ ፕሬዚዳንቱ ተስፋ አስቆረጠን። 'እናንተን ዩንቨርሲቲው እንጂ የቀጠራችሁ የመንግስት ሰራተኞች አይደላችሁም' አለን ” - የ1,100 ብር ደሞዝተኛ

እስከ 20 ዓመታት ' አገለገልን ' ያሉ ከ800 በላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምገባና የሌሎች ሠራተኞች " ዩኒቨርሲቲው ከሥራ ሊያሰናብተን ነው " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ስሞታ አሰሙ።

ሠራተኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?

አንድ አባት ፥ “ ከ2004 ዓ/ም ጀምሮ ከከተማው ተደራጅቼ በመስተንግዶና ሁለገብ ሥራ ግቢው እንደፈለገ ነው የምሰራው። የአባቶች እግራቸው ተሰብሯል፤ ጥርሳቸው ወልቋል፤ እጃቸው በእሳት ተቃጥሏል ” ብለዋል።

“ የዩኒቨርሲቲ ዋናው ፕሬዚዳንት ‘መንግስት መዋቅር እያስተካከለ ነው። ይህ ሂደት ካለቀ በኋላ ማኀበራትን ሁሉ ያሰናብታል። መንግስት ከዚህ ግቢ አያውቃችሁም’ ብሏል። እንደ አሮጌ እቃ ቆጥረውናልና መፍትሄ የሚሰጠን የህግ አካል መጥቶ ይመልከተን ” ሲሉም ተማጽነዋል።

ልላኛው አባት፣ “ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከ16 ዓመታት በላይ ከባልደረቦቻችን ጋር እንጨት እየፈለጥን እየተሸከምን ብዙ የሥራ ጫና ነበረብን ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ወድቄ ከተሰበርኩ ከአንድ ዓመት በላይ ሆኖኛል፤ ነገር ግን ህክምና አላገኘሁም። ሦስት ልጆች አሉኝ በ1000 ብር ደመወዝ ነው የምንተዳደረው። አሁን የት እንውደቅ ? የት እንግባ ? ” ሲሉም ጠይቀዋል።

ሌላኛው ቅሬታ አቅራቢም፣ “ 9 ቤተሰብ የቤት ኪራይ እየከፈልኩ አስተዳድራለሁ። እኔ ራሴ መማር እፈልጋለሁ። ግን በገንዘብ ማነስ ምክንያት አልቻልኩም። 1,100 ብር ነው የሚከፈለኝ። ይቺን 1100 ብር ታዲያ ወስጄ ምንድን ነው የማደርጋት ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

ሌላኛዋ እናት፣ “ ለፍተን እየሰራን ቆይተን አሁን ሁለት ፀጉር አብቅለን በሽተኛ ከሆንን በኋላ ጅብ ይብላችሁ ጎዳና ውጡ ተብለናል።  አራት፣ አምስት ወራት የቆዩትን ቋሚ አድርጎ 20 ዓመት በላይ ቆይታ እያለን ምንም አንዳልጠቀምን ተደርገናል ” ብለዋል።

“ 7 ልጆች አሉኝ ደመወዜ 1000 ብር ነች ከሌሎቹ እኩል አድርጉን እኛም ኢትዮጵያዊ ነን፤ አዋጁ ይመለከተናል፤ ይጨምርልን ስላልን ነው ‘ውጡ’ የተባልነው አንዲያውም አረጋውያን ይደገፉ እንጂ ይጣሉ አይባልም ነበር ” ሲሉም ወቅሰዋል።

ሌላኛዋ ቅሬታ አቅራቢ፣ “ 17 ዓመት ከጅብ ጋር እየተጋፋን እንደ ሻማ ቀልጠን አገልግለናል። ደመወዝ ጭማሪ ስንጠይቅ ‘እንዲያውም እስካሁን አገልግላችኋል አንፈልጋችሁም’ ተባልን ” የሚል ወቀሳ አቅርበዋል።

አክለው፣ “ እኔስ ቆሜ በሚዲያ ተናገርሁ ስንቱ ነው እግሩ የተቀደደው! ስንቱ ነው ሰባራ ሆኖ በየቤቱ ያለው። ቋሚ ሰራተኛ አድርጉን አላልንም ደመወዝ ይጨመርልን ነው የኛ ጥያቄ ” ነው ያሉት።

ሌላኛዋ እናት፣ “ ሙሉ 30 ቀናት ነው አፈር ግጠን የምንሰራው። ስንቀጠር 330 ብር ነበር ትንሽ፣ ትንሽ እየተጨመረልን 1100 ደረሰ። በኋላ ይጨመረናል ብለን ስንጠብቅ አዲሱ ፕሬዚዳንት ጭራሽ ተስፋ አስቆረጠን። ‘እናንተን ዩንቨርስቲው ነው እንጂ የቀጠራችሁ የመንግስት ሠራተኞች አይደላችሁም’ አለን ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ዩኒቨርስቲው ትንሽ፣ ትንሽ እየጨመረ ቆይቷል፤ አሁንስ ለምን አይጨምርም? ኑሮ ውድነቱ በኛስ አልጨመረም ወይ? ብለን ስንጠይቅ፥ ‘እናንተን አናወቃችሁም። እንዲያውም ተንሳፋፊ ሰራተኛ ተመድቦ ይሰራል። እናንተን እናስወጣለን ብዙ ስላገለገላችሁ ይበቃችኋል’ አለን ” ብለዋል።

አክለው፣ “ የምናደርገው አጥተን ነው ተማረን በእንባ የወጣነው ” ያሉ ሲሆን፣ ልላኛው አባትም፣ “ ከ2002 ጀምሬ ነው ዩኒቨርሲቲ ላይ በመስተንግዶ የሰራሁት። በሳምንት፤ በሁለት ሳምንታት ህክምና ለልዩ ልዩ ነገሮች ይኖራሉ። ሁሉን ትተን እየሰራን ቆይተናል ” ብለዋል።

“ ልጆች እናስተምራለን፤ የቤት ኪራይ አንከፍላለን በወር 1,100 በቀን 33 ብር እየተከፈለው በዚህ ኑሮ ውድነት ሰው እንዴት ይኖራል? ብለን ጥያቄ ስናቀርብ ‘በኔ በኩል ጨርሻለሁ ወደ ሚመለከተው ሂዱ የምታመጡት ነገር የለም’ ነው ያለን ፕሬዝዳንቱ ” ሲሉም አማረዋል። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቅሬታው ምላሽ ለመጠየቅ ወደ ዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

(ጥረቱ ይቀጥላል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

🔴 " ሙሉ ፓትሮል መኪና መጣብን፡፡ እኛ ሮጠን አመለጥን ሌሎች 5 ሰዎች ታስረዋል " - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች

➡️ " እየለፉ እስከሆነ ድረስ ቢጨመርላቸው ደስ ይለናል " - የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ

⚫️ " የማውቀው ጉዳይ የለም " - የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን

ከማኀበራት ተውጣጥተው በሀዋሳ የኒቨርሲቲ በምገባና ሌሎች ስራዎች ለዓመታት ሰራን ያሉ ወደ 800 ሠራተኞች ደመወዝ እንዲጨመርና ቋሚ ቅጥረኛ እንዲሆኑ ጥያቄ በማቅረባቸው፣ ዩኒቨርሲቲው ከሥራ ሊያሰናብታቸው መሆኑን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አቤት ብለው ነበር።

ሠራተኞቹ ዛሬ በሰጡን ቃልስ ምን አሉ ?

“ ደመወዝን በተመለከተ ቅሬችንን ለመግለጥ ወደ ደቡብ ኤፍኤፍ እየሄድን በነበረበት የተወሰኑ ሰዎች ታስረዋል መብታቸውን ስለጠቁ ታስረዋል፡፡ አንዱ ታሳሪ ታሟል፡፡

ጠዋት ደቡብ ኤፍኤም ቀጥሮን ነበር፡፡ 2 ሰዓት ተኩል ወደ ጣቢያው ስንሄድ ሙሉ ፓትሮል መኪና መጣብን፡፡ እኛ ሮጠን አመለጥን ሌሎች 5 ሰዎች ታደስረዋል፡፡ ጠዋት ነው የታሰሩት አሁን ስንሄድ ቃላቸውን የሚቀበላቸው የለም። እኛንም እየፈለጉን ነው ካፓስ ውጪ ነን። 

ሰዎቹ የታሰሩት ሀዋሳ 01 ፖሊስ ጣቢያ ነው፡፡ ምንም አላጠፋንም፡፡ ‘ለምን ተሰባሰባችሁ’? ሲሉን የደመወዝ ጭማሪ አልደረሰንም፡፡ በ1,000 ብር ደመወዝ እየሰራን ኑሮ ውድነቱን መቋቋም አልቻልንም፡፡ መንግስት እንዲመለከተን ለሚዲያ ቃላችንን ልንሰጥ ነው የመጣነው አልናቸው፡፡

ከዚያ በኋላ ‘እንዴት ስማችን ይጠፋል? ለምንድን ነው የምታስተላልፉት’? ብለው ነው ወንዶቹን አተኩረው ያሰሯቸው። የታሰሩት ሠራተኞች እንጨት ሲፈልጡ ለትርፍ አንጀት በሽታ ተጋልጠው ቀዶ ጥገና የተሰሩ ናቸው፡፡ አንዱ መኪና ላይ ሲወረውሩት ራሱን አያውቅም።

መንግስት ይየን፡፡ ፍትህ ይደረግልን፡፡ የኑሮ ውድነት እኛን አልነካም? እኛ ልጆች የሉንም? ለምንድን ነው መንግስት የማያየን? የኑሮ ወድነቱን አልቻልንም፡፡ ተንከራተን ነው የምንኖረው፡፡ ልጆቻችን እየተራቡ፣ እየተጠሙ ነው፡፡

24 ሰዓት ነው ግቢ ውስጥ የምንሰራው፡፡ ከግቢ ወጥተን ሌላ ሥራ ለመስራትም ጊዜ የለንም፡፡ ሁሉም በችግር ላይ ነው። በዛ ላይ ወጥ የተደፋባቸው፣ እጃቸውን ማሽን የቆረጣቸው አሉ። አካል ጉዳተኞቹንም ለማሳየት ነበር ወደ ሚዲያ የሄድነው፡፡ ግን መብታችን ተረግጧል፡፡ ዲሞክራሲም የለም፡፡

አካል ጉዳተኞች 50 በላይ ይሆናሉ፡፡ እናቶች መንቀሳቀስ ስለማይችሉ ቤት ውስጥ ነው ያሉት፡፡ የሚያሰሩት ሰዎችን 600 ብር ቀጥረው ነው፡፡ መስራት ስላማችሉ፡፡ ከታሰረው እንዱ ራሱ ወጥ ተደፍቶበት እግሩ ተቃጥሏል፡፡

እንጨት ከጫካ ተሸክመን አምጥተን ፈልጠን በዬኩሽናው እናደርስ ነበር። እንደዚህ ደክሞን ውለን የምንታጠብበት ሳሙና አልነበረንም። ችግር ከትክሻችን አልወርድ አለ። 

ለሌሎች ደመወዝ ሲጨመር የኛስ ድካም ለምን አይታይም? ልጆች እናስተምራለን፣ የቤት ኪራይ አለብን። 'ደመወዝ ተጨምሯል' ሲባልም የቤት ኪራይ ተጨምሮብን 'ቅድሚያ ካልከፈላችሁ ውጡ’ እየተባልን ነው፤ ተጨንቀናል ” ሲሉ ቅሬታ አቅራቢዎች አማረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የሠራተኞችን ቅሬታ ይዞ ፤ ሰዎቹ የመብት ጥያቄ ስላነሱ ለምን ታሰሩ ? ይህን ማድረግ አግባብ ነው ? ሲል የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮን ጠይቋል።

አንድ የቢሮው አካል በሰጡት ምላሽ፣ የደመወዝ ጭማሬና ቋሚ ሰራተኛ መሆንን በተመለከተ ዩኒቨርሲቲው የራሱ መተዳደሪያ ደንብ እንዳለው፣ ጭማሬው ለቋሚ ሠራተኞች እንጅ ለጊዜያዊ እንደማይሆን ገልጸዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ለሰዎቹ ደመወዝ የመጨመርና ቋሚ ሠራተኛ ማድረግን የሚመለከተው ዩኒቨርሲቲው ሆኖ እያለ፣ ሠራተኞቹ የመብት ጥያቄ በማቅረባቸው መታሰታቸው አግባብ ነው ? ሲል ለእኝሁ አካል በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል፡፡

እሳቸው በምላሻቸው፣ ከክልል ይታሰሩ እንዳልተባለ ገልጸው፣ " አንተ እንዳልከው እኛ ደመወዝ ይጨመርላቸው፤ አይጨመርላቸው የመተዳደሪያ ደንብ ስላላቸው እነርሱ ናቸው የሚያስተካክሉት " ብለዋል፡፡

" ቢጨምሩላቸው እኛም ደስ ይለናል፡፡ እየለፉ እስከሆነ ድረስ ቢጨመርላቸው ደስ ይለናል፡፡ ግን እነዚህ ሰዎች ታስረዋል ? ማነው ያሰራቸው ? የሚለውን ለመጠየቅ እየሞከርኩኝ ነው፡፡ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ናቸው፡፡ ሲወጡ እንዴት ታሰሩ ? የሚለውን አጣራለሁ " ብለዋል፡፡

በተጨማሪም፣ ሠራተኞችን ለምን እንደታሰሩ ማብራሪያ  የጠየቅናቸው የሲዳማ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ካሳ ጩቦ በሰጡን ቃል፣ " የማውቀው ነገር የለም " የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።
 
(የክልሉ ፓሊስና ጸጥታ ቢሮ ተጨማሪ አጥጋቢ ምላሽ  ከሰጡን የምናቀርብ ሲሆን፣ ጉዳዩንም እስከ ጥግ እንከታተለዋልን)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ገልጿል፡፡

እግድ የተጣለባቸው 62 ግለሰቦች በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል  ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ተብሏል።

" በስም ከተለዩት ግለሰቦች መካከል ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ዜጎችም ይገኙበታል ዕዳቸውን የማይከፍሉ ከሆነም አዋጁ በሰጠን ሥልጣን መሰረትም በቀጣይ የንብረት እግድ እና ንብረታቸውን በሃራጅ የመሸጥ እርምጃዎች ይወሰዳሉ " ሲሉ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ እግድ የተጣለባቸው ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡

የ62ቱ ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተላከው በትላንትናው ዕለት ነው።

አቶ ሰውነት " በህጉ መሰረት የተቀመጠ ቀነ ገደብ አለ በአዋጁ በተቀመጠው ቀነ ገደብ መሰረት መጥተው እስካልከፈሉ ድረስ ለእዳው ማካካሻ በሚሆን መሰረት ንብረታቸው በሃራጅ ተሽጦ እዳው ይሸፈናል " ብለዋል።

ቢሮው የግብር ዕዳቸውን ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በ2017 በጀት ዓመት እንደ አዲስ አዋቅሯል።

በዚህም መሰረት ባለፉት 6 ወራት ከ 6.4 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ እዳ መሰብሰቡን አቶ ሰውነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
ከጀርባዋ " ኤሌክትሮኒክ ቁስ ተሸክማ ስትበር ተያዘች " የተባለችው ወፍ ምንድነች ?

🔴 “ ምርመራ እየተደረገ ነው ፤ ገና አላለቀም ” - የቤንሻንጉል ክልል ፓሊስ ኮሚሽን

➡️ “ ምርመራ እየተደረገ ነው። ሲያልቅ እናሳውቃለን ” - የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን እና ሰላምና ጸጥታ ቢሮ 


በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ ጉሬ ቀበሌ “ በጀርባዋ ላይ ኤሌክቶርኒክስ ቁስ ተገጥሞባታል ” የተባለችና ከወትሮው ለየት ያለች ወፍ ስትበር መያዟን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአካባቢው ነዋሪዎች ሰምቷል።

በገለጻው መሠረት፣ ወፏ በጉሬ ቀበሌ ሰማይ ስር ስትበር የተገኘችው ከቀናት በፊት ሲሆን፣ ኤሌክትሮኒክስ ቁስ የተገጠመላት ከመሆኗ ባሻገር፣ ሙሉ አካሏ በአርቲፊሻል የተሞላ፣ በሁለት እግሯቿም ቀለበቶች እንዳላት ተመላክቷል።

እንዲህ አይነት ወፍ ከዚህ በፊት በአካባቢው ዝር ብሎ እንደማያውቅ የተናገሩት ነዋሪዎች በተለይ ወፏ እግር ላይ ያሉት ቀለበቶችና በጀርባዋ ተገጥሞላታል የተባለው ኤሌክትሮኒክ ቁስ “ ምን የያዘ ነው ? ” በሚል ስጋትን እንደደቀነባቸው ጠቁመዋል።

አንዳንዶችም ጉዳዩ “ ከህዳሴ ግድቡ ጋ ሊገናኝ ይችል ይሆን ? ” የሚል መላምት ሲያስቀምጡም ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመልክቷል።

በተለይም ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ወፏ ላይ ምርመራ ለማድረግ በጸጥታ አካላት ወፏ ወደ አሶሳ ከተማ ሳትወሰድ እንዳልቀረች ተነግሯል።

በዚህም ስለጉዳዩ የተጠየቅነው የአሶሳ ፓሊስ መምሪያ፣ ጉዳዩን እንደሰማ፣ ነገር ግን ሁነቱ ከከተማው ውጪ በመሆኑ ምርመራው እንደማይመለከተው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተጨማሪም፣ በማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ ሰማይ ስር ስትበር ታየች የተባለችው ቀለበትና ኤሌክትሮኒክ ቁስ በጀርባዋ እንዳላት የተነገረላት ወፍን ምንነት አውቀው እንደሆን የክልሉ ፓሊስ፣ ኮሚዩኒኬሽን፣ ሰላምና ጸጥታ ቢሮዎችን ጠይቋል።

አንድ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ፓሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራር በሰጡት ምላሽ፣ “ መከላከያ ጋር ነው፤ ምርመራ እየተካሄደ ያለው። ምርመራው ገና ለላለቀም ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። 

ስለጉዳዩ የጠየቅናቸው አንድ የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አካል ደግሞ መረጃው እንደደረሳቸው ገልጸው፣ “ ምርመራ እየተደረገ ነው። ሲያልቅ እናሳውቃለን ” የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።

ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረብንለት የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ በበኩሉ፣ ወፏን በተመለከተ ምርመራ እየተደረገ እንደሆነ፣ ምርመራው ሲጠናቀቅ ማብራሪያ እንደሚሰጠን ቃል ገብቷል።


(ጉዳዩን ተከታትለን በቀጣይ መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 " ሙሉ ፓትሮል መኪና መጣብን፡፡ እኛ ሮጠን አመለጥን ሌሎች 5 ሰዎች ታስረዋል " - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች ➡️ " እየለፉ እስከሆነ ድረስ ቢጨመርላቸው ደስ ይለናል " - የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ⚫️ " የማውቀው ጉዳይ የለም " - የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን ከማኀበራት ተውጣጥተው በሀዋሳ የኒቨርሲቲ በምገባና ሌሎች ስራዎች ለዓመታት ሰራን ያሉ ወደ 800 ሠራተኞች ደመወዝ እንዲጨመርና…
#Update

🔴 “ የታሰሩት ተፈትተዋል፡፡ የመብት ጥያቄ በማቅረብችን ነው ያሰሩን፡፡ 10 ሠራተኞች ሥራ ተከልክለናል ” - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች

➡️ “ ቅሬታ እንዳለባቸው አውቃለሁ፡፡ ያንን ማሰማት መብታቸው ነው፡፡ የሰሩት ወንጀል የለም ” - የከተማው ጸጥታ መምሪያ

በዛ ቢባል 1,100 ብር ደመወዝተኛ ለ20 ዓመታት ምገባና ሌሎች ሥራዎችን የሰሩ 800 የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ እንዲደረግላቸው ዩኒቨርሲቲውን ሲጠይቁ ‘እንዲያውም አሰናብታችኋላሁ’ እንዳላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቀናት በፊት ተናግረው ነበር።

ሠራተኞቹ ከዚያ በኋላ በገለጹት መሰረት፣ ቅሬታቸውን ለሚዲያ ለማቅረብ በሄዱበት ወቅት ደግሞ የተወሰኑት ሠራተኞች በፖሊስ እንደታሰሩ ነበር የነገሩን።

የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ ጉዳዩን እንደሚያጣራና ሠራተኞቹ ደመወዝ ቢጨመርላቸውም እንደማይከፋው፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ጉዳዩን እንደማያውቅ ስለጉዳዩ ከቲክቫህ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተው ነበር።

ታሰሩ የተባሉት ሠራተኞች ተፈቱ ?

የታሰሩት ሠራተኞች ትላንት ጠዋት በዋስ እንደተፈቱ፣ ገና ወደ ሥራ እንዳልገቡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ታስረው ከነበሩና ከቅሬታ አቅራቢ ሠራተኞቹ ገለጻ ለማወቅ ችሏል፡፡

ሠራተኞቹ በሰጡን ቃል፣ “የታሰሩት ተፈትተዋል፡፡ የመብት ጥያቄ በማቅረብችን ነው ያሰሩን፡፡ ከ10 በላይ ሠራተኞች ሥራ ተከልክለናል” ነው ያሉት።

የመብት ጥያቄ ለማቅረብ ከመሞከር ውጪ ጥፋት እንዳልፈጸሙ፣ ሆኖም በዩኒቨርሲቲ በሚገኘው 01 ቀበሌ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ከቆዩ በኋላ በመታወቂያ ዋስ እንደተለቀቁ ሠራተኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል፣ ቅሬታ ካቀረቡት የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች መካከል 10 የሚሆኑት “ወደ ዩኒቨርሲቲው ለሥራ አትግቡ” ተብለው እንደተከለኩ ገልጸው፣ መብታቸው እንዲከበርላቸው በድጋሚ ጠይቀዋል፡፡

ታሳሪዎቹን በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጥ ሰሞኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲጠይቀው የነበረው የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ፣ ጉዳዩን አጣርቶ ምላሽ ለመስጠት ገልጾ ነበር፡፡

መምሪያው ትላንት በሰጠን ምላሽ፣ “ምንም የታሰረ አካል የለም፡፡ የተፈጠረ ነገርም የለምኮ ለምንድን ነው የሚያታሰሩት?” ብሏል።

“ ቅሬታ እንዳለባቸው አውቃለሁ፡፡ ያንን ማሰማት መብታቸው ነው፡፡ የሰሩት ወንጀል የለም፡፡ የሚያሳስራቸው ጉዳይም የለም ” ሲል ተናግሯል።

የተፈጠረ ነገርማ አለ፤ ሠራተኞች እንደታሰሩ ተናግረዋል፣ ለመሆኑ ከከተማው 01 ቀበሌ ፖሊስ ጣቢያ ሄዳችሁ አጣርታችሁ ነበር ? ስንል ላቀረብለት ጥያቄ ደግሞ፣ “ ቼክ አድረገናል፡፡ ወንጀል የለባቸውም፡፡ ዩኒቨርሲቲውም ለኛ ያመለከተን ጉዳይ የለም ” ብሏል።

ሠራተኞቹ በበኩላቸው፣ “ እነርሱማ እውነት ነው አይሉም ” ሲሉ ወቅሰዋል።

(ክትትሉ ይቀጥላል)


#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከጀርባዋ " ኤሌክትሮኒክ ቁስ ተሸክማ ስትበር ተያዘች " የተባለችው ወፍ ምንድነች ? 🔴 “ ምርመራ እየተደረገ ነው ፤ ገና አላለቀም ” - የቤንሻንጉል ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ➡️ “ ምርመራ እየተደረገ ነው። ሲያልቅ እናሳውቃለን ” - የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን እና ሰላምና ጸጥታ ቢሮ  በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ ጉሬ ቀበሌ “ በጀርባዋ ላይ ኤሌክቶርኒክስ ቁስ ተገጥሞባታል ” የተባለችና…
#Update

“በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዕዋፋት ይመጣሉ። ባለፍኩበት የስራ ዘመን እንደዚህ አይነቱን አሰራር ለስለላ ተጠቅመውበት አያውቁም” - በዘርፉ 40 ዓመታት የሰሩ የአዕዋፍ ሳይንቲስት

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማኦ እና ኮሞ ልዩ ወረዳ በጀርባዋ የኤሌክትሮኒክ ቁስ ተሸክማ ስትበር ተገኘች የተባለችው ወፍ የብዙዎችን ቀልብ ስባለች።

ብዙዎች “ለስለላ የተላከች ወፍ ነች” የሚል ስጋታቸውን በማኀበራዊ ሚዲያ ሲያንጸባርቁ የተስተዋሉ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም የክልሉን አካላት ስለጉዳዩ ጠይቆ ገና በምርመራ መሆናቸውን ከመግለጽ ውጪ ያሉት የለም።

የወፏ ጉዳይ እውነትም ስለላ ሊሆን ይችላል ይሆን ? እስከዛሬ በነበሩ መሰል ክስተቶች በወፍ አማካኝነት ስለላ ተደርጎ ያውቃል ? ስንል የአዕዋፋት ሳይንቲስት አቶ ይልማ ደለለኝን ማብራሪያ ጠይቋል። 

በዘርፉ የ40 ዓመት ልምድ ያላቸው ባለሙያ ምን መለሱ ?

አሁን በግላቸው የአካባቢ ጥበቃ ላይ፣ ከዚህ ቀደም በዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የሰሩት አቶ ይልማ እንዳሉት፣ ሰምንኛው የወፏ ጉዳይ በየዓመቱ የሚስተዋልና ሥጋት ሊደቅን የማይችል የተለመደ ሁነት ነው።

ባለሙያው፣ ከጀርባቸው ሶላር ጂፒኤስ፣ ከእግራቸው ቀለበት የተገጠመላቸው ወፎች የሆነ ወቅት ቅዝቃዜን በመሸሽ ከአውሮፓ ሀገራት 7000 ድረስ ኪሎ ሜትር አቋርጠው በየዓመቱ የሚመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ወፎች ላይ ቀለበትና ሶላር ጂፒኤስ ገጥሞ መላክ ታዲያ ለምን አስፈለገ? የሚለውን ጥያቄ ሲያብራሩም፣ ከጀርባቸው ያለው ሶላር ጂፒኤስ ወፎች የት እንዳሉ፣ በምን ያህል ከፍታ እየበረሩ እንደሆነ፣ ወደየትኛው አገር እንደሄዱ አውሮፓያውያኑ የሚከታተሉበት እንደሆነ አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ባለዎት ልምድ መሰረትና እንደብዙኅኑ ስጋት ቀለበትና ሶላር ጂፒኤስ በተገጠመላቸው ወፎች ስለላ ተደርጎ አያውቅም? የሚል ጥያቄ ለባለሙያው አቅርቧል።

አቶ ይልማ ምን መለሱ ?

ሰዎች ይህንን ከፖለቲካ ጋር ያያይዙታል። ነገር ግን ፒዩርሊ የሳይንስ ስራ ነው። እኔም ብዙ ጊዜ ወፎች ላይ ቀለበትና ጂፒኤስ ትራከር አስሪያለሁ። 

ኢትዮጵያ እንኳን በሚመጡበት ወቅት ያን ቀለበትና ጂፒኤስ አስረን የት ድረስ እንደሚሄዱ የምንከታትልበት ሲስተም አለ። ሳይንቲስቶች ከእውቀት ጉጉት የሚያደርጉት ነው እንጂ በፍፁም የስለላ ተግባር እንዳልሆነ ነው የምረዳው። 

ያው ኢትዮጵያ ውስጥ ያን ያክል ጥልቅ እውቀት ስለሌለና አሁን ያለንበት የሰላም ሁኔታ ጋር ተደማምሮ ሰዎች እንደዚህ እንዲያስቡ አድርጓቸዋል። እውነት ለመናገር ለስለላ ቢሆን ኖሮ ወፍ ሳይሆን ድሮን ላይ በተገጠመ ነበር። ምክንያቱም የተፈጥሮ ወፍን እንቅስቃሴ መቆጣጠር አይቻልም።

በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዕዋፋት ይመጣሉ። እነርሱ (አውሮፓውያኑ) ከኛ የተሻለ ፍለጎቱ፣ እውቀቱ፣ አቆርቦቱ፣ የገንዘብ አቅሙም ስላላቸው በአዕዋፍ እንደዚህ ያደርጋሉ እንደዚህ ዓይነቱ ስራ ደግሞ ከገንዘብ በተጨማሪ ብዙ ጊዜና ክትትል ይፈልጋል።

ከዚህ ቀደምም በደርግ ዘመን የኢትዮ - ኤርትራና የካራማራ ጦርነት በነበረበት ወቅት ደርግም ደግሞ ኮሚኒስት ከመሆኑ የተነሳ ከአሜሪካና ከአውሮፖ ሀገራት ‘የተላከ ሰላይ ነው’ በሚል ብዙ ጭንቅላት የሚያዞር ችግር ነበር፤ እኛም ይህን ለማስረዳት ሞክረናል። 

አሁንም ሰዎች ይህን ቢሉ እኔ አልፈርድም ምክንያቱም እኛ ባለሙያዎችም ብንሆን እንደዚህ አይነቱን ነገር ቀድመን ለማህበረሰቡ ማሳወቅ ይጠበቅብናል።

ባለፍኩበት የስራ ዘመን እንደዚህ አይነቱን አሰራር ለስለላ ብዙም ተጠቅመውበት አያውቁም። በእርግጥ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የወፎች እግር መልዕክት ይደረግላቸውና መልዕክት የሚላላኩትን ሰዎች ቤት እርግቧ ስለምታውቅ ከአንዱ ወደ ልላኛው ስታስተላልፋል።

በዛ ጊዜ የተጠቀለለ ወረቀት በትንሽየ እቃ አድርገው በወፍ ጀርባ ላይ ያደርጉትና ለሚፈለገው አካል ይደርስ ነበር። ምክንያቱም ወፍ ላይ መልዕክት ይኖራል ተብሎ ስለማታይ ጠላት ባለበት ጎራም አልፈው ወገን ጋር ሊያደርሱ ይችላሉ።

በወፎች ስለሚደረገው ስለላ ይህን ብቻ ነው የማውቀው ይኸውም ያኔ እንደአሁኑ ቴሌግራም፣ ፌስቡክን የመሳሰሉ የመልዕክት መለዋወጫዎች ስላልነበሩ ነው። አሁን ወፎች ለስላላ ጥቅም አይውሉም፤ አንዲያውም ጂፒኤስ የሚደረግባቸው ወፎች ረጅም ርቀት በመጓዝ በመጓዛቸው፣ በርሀብና በጥም ምክንያት 75% ይሞታሉ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 “ መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ ከእገታው የወጡት ኢትዮጵያዊያንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል ” - ቤተሰብ 🔵 “ እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም? ” - ኢትዮጵያዊ በታይላንድ ➡️ “ ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው ” - የወላጆች ኮሚቴ ሰርተው ለመለወጥ ሲሉ ተታለው ወደ ታይላንድ…
🔈#የኢትዮጵያውያንድምጽ

“ ወደ 29 ኢትዮጵያውያን ይበልጥ የከፋ ቦታ ተወስደዋል። ” - ኢትዮጵያዊያን በማይናማር

ካሉበት ችግር እንዲያወጣቸው መንግስትን በተደጋጋሚ የተማጸኑ ፣ ማይናማር “ ታይሻንግ ካምፕ ” ታግተው የነበሩ 29 ኢትዮጵያውያን እስከዛሬ ሲደርስባቸው ከነበረው የከፋ ስቃይ ወዳለበት ስፍራ ተገደው መወሰዳቸውን ጓደኞቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

የተወሰዱት “ ዋልዋይ ” የተሰኘ ማይናማር ላይ ያለ ቦታ እንደሆነ፣ የድረሱልን ተማጽኖ ቢያስሙም የሚደርስላቸው ባለመገኘቱ ራሳቸውን እስከማጥፋት ሙከራ እያደረጉ እንዳሉ ታውቋል።

በአካባቢው ባሉ ካምፓች የነበሩ ሌሎች ሰዎች ከእገታ እየወጡ እንደሆነ፣ " ዋልዋይ " ካምፕ የሚገኙትን ታጋቾች ግን እንዳይወጡ አጋቾቹ በድብቅ እንደያዟቸው ተመልክቷል።

ኢትዮጵያዊያኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በተጨማሪ ምን አሉ ?

“ በማይናማር ካምፕ የነበሩ 29 ኢትዮጵውያን ካምፓኒው ‘ወደ ሌላ ቦታ ልውስዳችሁ’ ሲላቸው ለደኀነታቸው አስተማማኝ ስላልሆነ እዚሁ ነው መቆት የምንፈልገው ብለው ነበር፡፡

ነገር ግን ካምፓኒው የጸጥታ ኃይሎችን ወዳነበሩበት ካምፕ በማምጣት እጃቸውን በግዴታ እየጎተተ በመኪና አሳፍሮ በማይናማር 'ዋልዋይ' የሚባል ቦታ ወስዷቸዋል፡፡

የተወሰዱት ገና አዲስ በመሰራት ባለ ኮምፓውንድ ነውና በጣም ከፍተኛ የሆነ ስቃይ እየደረሰባቸው ይገኛሉ፡፡ ኮምፓውንዱ ህግ እና ስርዓት የለውም። በጋንግስተሮች ብቻ የሚተዳደር ነው። ለደኅንነታቸው የሚጮህላቸው የለም።

ሴቶችን ፀጉራቸውን ላጭተዋቸዋል። ወንዶችና ሴቶችን በኤሌክትሪክ ይገርፏቸዋል፤ በጨለማ ክፍል በማስገባት ከሦስት ቀናት በላይ ምግብ በመከልከል በሰንሰለት ያንጠለጥሏቸዋል።

እናም በማይናማር የነበሩ ወደ 29 ኢትዮጵያውያን ይበልጥ የከፋ ቦታ ተወስደዋል። እንዲያውም ራሳቸውን ለማጥፋት ሙከራ እያደረጉ ነው። በሰጡን መረጃ መሰረት።

እዚያ ከሄዱ በኋላ ይበልጥ ከባድ ችግር እየገጠማቸው ነው። ለካምፓኒው ሥራ ቢሰሩም ባይሰሩም ሁሌም ይቀጠቀጣሉ፡፡ ተስፋ ወደ መቁረጥ ደርሰዋል፡፡ የተወሰኑ ሰዎች ራሳቸውን የማጥፋት ሙከራ አድርገዋከል ” ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል፥ በማይናማር ታግተው አስከፊ ጊዜ ያሳለፉና ከወር በፊት ከእገታ የወጡ፣ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የኢትዮጵያ መንግስትን የቪዛና ሌሎች ጉዳዮች ይሁንታ እየጠበቁ ታይላንድ ከሚገኙ ከ250 በላይ ዜጎች መካከል ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የተረጋገጠላቸው ለመመለስ ትኬት ያላቸው 40 ሰዎች ብቻ መሆናቸውን ኢትዮጵያውያኑ ነግረውናል፡፡

ሌሎች ወደ ኢትዮጵያ መግባት የሚችሉት በራሳቸው ሙሉ ወጪ ትኬት ሲቆርጡ መሆኑን እንደተናገሩ፣ የደርሶ መልስ ቪዛና ለትኬት መቁረጫ ገንዘብ የሌላቸው በርካቶች ጭንቀት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

🔴 " ዛሬ ጠዋት 32 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል " - የወላጆች ኮሚቴ

➡️ " የታይላንድ መንግስት ያልተቀበላቸው ወደ 300 ልጆች ማይናማር ካምፕ ውስጥ አሉ። 32 ልጆች መጥተናል " - ተመላሽ ኢትዮጵያዊ

ከማይናማሩ እገታ ወጥተው ታይላንድ ካምፕ ከነበሩት ኢትዮጵያውያን መካከል 32 የሚሆኑት ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን የወላጆች ኮሚቴና ተመላሾቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

የወላጆች ኮሚቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ " ዛሬ ጠዋት 32 ኢትዮጵያውን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል " ብሏል።

ልጆቹን ለሀገራቸው እንዲበቁ ላደረጓቸው ምስጋና አቅርቦ፣ ከእገታ ወጥተው በታይላንድ ያሉ፣ በማይናማር ገና ከእገታ ያልወጡና ወጥተው ወደ ታይላንድ ያልተሻገሩ፣ ጭራሹንም ያሉበት የማይታወቅ በርካታ ኢትዮጵያውያንን መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቋል።

ከተመላሾቹ መካከል አንዱ፣ 32 ልጆች መምጣታቸውን አረጋግጦ፣ " የታይላንድ መንግስት ያልተቀበላቸው ወደ 300 ልጆች ማይናማር ካምፕ ውስጥ አሉ። 32 ልጆች መጥተናል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

የውጩ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፣ 32 ልጆች እንደመጡ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት አረጋግጧል። 

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ፣ ከማይናማሩ እገታ ወጥተው ወደ ታይላንድ ከተሻገሩ 133 ኢትዮጵያ መካከል 32ቱ ዛሬ ወደ አገራቸው ገልጾ፣ " 43  ኢትዮጵያውያንን ደግሞ ዛሬ ምሽት ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል " ብሏል።

" ቀሪዎቹ በታይላንድ ማቆያ የሚገኙ 58 ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው ለመመለስ ኤምባሲው ጥረት እያደረገ ይገኛል " ሲልም አክሏል።

ጃፓን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን ወደ ታይላንድ በማሻገር ወደ  አገራቸው ለመመለስ  ጥረት እያደረገ ይገኛል ሲልም አክሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia