TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከቀረበባቸው ሁለት ክሶች በነፃ ተሰናበቱ።
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ የሕግ ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀዋሳ ማዕከል ከቀረበባቸው ከባድ የሙስና ወንጀል እና በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ መጠቀም በሚል የቀረበባቸዉን ሁለት ክሶች ላለፉት አንድ ዓመት ሲከታተሉ ቆይዋል።
በዛሬዉ ዕለት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐዋሳና አከባቢዋ ማዕከል በነፃ መሰናበታቸውን ጠበቃቸው ተናግረዋል።
ከቀድሞ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በተጨማሪ ተመሳሳይ ክስ ተመሰርቶባቸዉ የነበሩት የቀድሞ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበራ አሬራም በነፃ መሰናበታቸውን ጠበቃ ገብረመድህን ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከቀረበባቸው ሁለት ክሶች በነፃ ተሰናበቱ።
የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ የሕግ ጠበቃቸው አቶ ገብረመድህን ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀዋሳ ማዕከል ከቀረበባቸው ከባድ የሙስና ወንጀል እና በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ መጠቀም በሚል የቀረበባቸዉን ሁለት ክሶች ላለፉት አንድ ዓመት ሲከታተሉ ቆይዋል።
በዛሬዉ ዕለት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐዋሳና አከባቢዋ ማዕከል በነፃ መሰናበታቸውን ጠበቃቸው ተናግረዋል።
ከቀድሞ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕሮፈሰር ፀጋዬ ቱኬ በተጨማሪ ተመሳሳይ ክስ ተመሰርቶባቸዉ የነበሩት የቀድሞ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበራ አሬራም በነፃ መሰናበታቸውን ጠበቃ ገብረመድህን ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" ምርጫ ማሸነፌ እንደወንጀል ታይቶ 1 ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያለአግባብ ታስሪያሁ " - አቶ አማንያስ ጉሹና
ከሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤዉን አካሂዶ ነበር።
በዚህም ጉባኤ ላይ የኢዜማው ተመራጭ ጉባኤ እንዳይሳተፉ መደረጋቸውን ገልጸዋል።
በክልሉ የዘይሴ ብሔረሰብ ተመራጭ የሆኑት አቶ አማንያስ ጉሹና " ያለአግባብ 4 ወራት ከታሰርኩ በኋላ ያለመከሰስ መብቴ ተነስቶ ለተጨማሪ 7 ወራት በእስር ላይ እንዲቆይና በምክር ቤት ጉባኤ እንዳልሳተፍና ከመንግስት ስራም እንዲሰናበት ተደርጌያለሁ " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ አማንያስ ፤ " ብሔረሰቡ ያለዉን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የመዋቅር ጥያቄ በተለያዩ ጊዜያት ሲጠይቅ የቆዬ ቢሆንም ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘቱ በ6ኛ ሀገራዊ ምርጫ የኢዜማ ፓርቲን በመምረጡ ከምርጫዉ ማግስት ጀምሮ በፓርቲው በአባላትና አመራሮች ላይ የእስርና የማሳደድ ተግባር በይፋ ማካሄድ ተጀምሯል " ብለዋል።
" በአሁኑ ሰዓት ከ2 መቶ በላይ የፓርቲዉ አባላትና አመራሮች በጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤት እየተመላለስን ነዉ " ሲሉ አስረድተዋል።
" ተወዳድረን ምርጫ ማሸነፋችን ሃጥያት ባልሆነበት በገዢዉ ፓርቲ አመራሮች በግልም ሆነ በብሔረሰቡ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እየደረሰብን ነዉ " የሚሉት አቶ አማንያስ " ለአብነትም የደቡብ ክልል ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደዉ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የዜይሴ ብሔረሰብ ያለተወከለበት እና ከሌሎች ብሔሮች ጋር በክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሌሎች ተሳታፊዎች ጋር ያልተሳተፈበት ጉባኤ ነዉ " ሲሉ ወቅሰዋል።
" በዚሁ የፖለቲካ ተፅእኖ ምክንያት ሀገሬን ለ17 ዓመታት ካገለገልኩበት የመምህርነት ሙያ እንድሰናበት ተደርጌያለሁ " ያሉት አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ ደጋግሜ ብጠይቅም 'ያለመከስ መብትህ ሳይነሳ መመለስ አትችልም' የሚል ምላሽ ከትምህርት አስተዳደር መዋቅሮች ተሰጥቶኛል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢዜማ ፓርቲ የሕግና አባላት ጉዳይ ደህንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስዩም መንገሻን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገራቸዉ ሲሆን " በዘይሴ ብሔረሰብ የሕዝብ ተመራጭ አቶ አማኒያስ ጉሹና ላይ የተፈፀመዉ ጉዳይ ኢ-ሕገመንግስታዊ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
በወቅቱ ያለመከሰስ መብታቸዉ ሳይነሳ ታስረዉ መቆየታቸዉንና በአካባቢዉ ያለዉን የሰብአዊ መብት ረገጣና የፖለቲካ ተፅእኖ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በፅሑፍ ማሳወቃቸዉንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደአከባቢዉ ማቅናቱንና የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ አንስተዋል።
" ከስራ የተሰናበቱበትና ወደ ስራ እንዳይመለሱ የሚደረግበት አግባብ ከፍተኛ የፖለቲካ ተፅእኖ ያለበት ነዉ " ያሉት አቶ ስዩም ፤ የኢዜማ ፓርቲ በአከባቢው ያለዉን የፖለቲካ ጫናና ተያያዥ ጉዳዮችን ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በጽሑፍ አቅርቦ ባለድርሻ አካላት የተካተቱበት ግብረሃይል ተዋቅሮ ቦታዉ ድረስ በመሄድ በሰጠዉ አቅጣጫ መሠረት አቶ አማንያስ በዋስ እንዲፈቱ መደረጉን ተናግረዋል።
አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ በተደጋጋሚ ብጠይቅም የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤትና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ' ያለመከሰስ መብትህ እስካልተነሳ ድረስ መመለስ አንችልም ' ተብያለሁ " በሚል ላነሱት ቅሬታ ከከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ጽ/ቤትና ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤዉን አካሂዶ ነበር።
በዚህም ጉባኤ ላይ የኢዜማው ተመራጭ ጉባኤ እንዳይሳተፉ መደረጋቸውን ገልጸዋል።
በክልሉ የዘይሴ ብሔረሰብ ተመራጭ የሆኑት አቶ አማንያስ ጉሹና " ያለአግባብ 4 ወራት ከታሰርኩ በኋላ ያለመከሰስ መብቴ ተነስቶ ለተጨማሪ 7 ወራት በእስር ላይ እንዲቆይና በምክር ቤት ጉባኤ እንዳልሳተፍና ከመንግስት ስራም እንዲሰናበት ተደርጌያለሁ " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ አማንያስ ፤ " ብሔረሰቡ ያለዉን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የመዋቅር ጥያቄ በተለያዩ ጊዜያት ሲጠይቅ የቆዬ ቢሆንም ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘቱ በ6ኛ ሀገራዊ ምርጫ የኢዜማ ፓርቲን በመምረጡ ከምርጫዉ ማግስት ጀምሮ በፓርቲው በአባላትና አመራሮች ላይ የእስርና የማሳደድ ተግባር በይፋ ማካሄድ ተጀምሯል " ብለዋል።
" በአሁኑ ሰዓት ከ2 መቶ በላይ የፓርቲዉ አባላትና አመራሮች በጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤት እየተመላለስን ነዉ " ሲሉ አስረድተዋል።
" ተወዳድረን ምርጫ ማሸነፋችን ሃጥያት ባልሆነበት በገዢዉ ፓርቲ አመራሮች በግልም ሆነ በብሔረሰቡ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እየደረሰብን ነዉ " የሚሉት አቶ አማንያስ " ለአብነትም የደቡብ ክልል ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደዉ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የዜይሴ ብሔረሰብ ያለተወከለበት እና ከሌሎች ብሔሮች ጋር በክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሌሎች ተሳታፊዎች ጋር ያልተሳተፈበት ጉባኤ ነዉ " ሲሉ ወቅሰዋል።
" በዚሁ የፖለቲካ ተፅእኖ ምክንያት ሀገሬን ለ17 ዓመታት ካገለገልኩበት የመምህርነት ሙያ እንድሰናበት ተደርጌያለሁ " ያሉት አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ ደጋግሜ ብጠይቅም 'ያለመከስ መብትህ ሳይነሳ መመለስ አትችልም' የሚል ምላሽ ከትምህርት አስተዳደር መዋቅሮች ተሰጥቶኛል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢዜማ ፓርቲ የሕግና አባላት ጉዳይ ደህንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስዩም መንገሻን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገራቸዉ ሲሆን " በዘይሴ ብሔረሰብ የሕዝብ ተመራጭ አቶ አማኒያስ ጉሹና ላይ የተፈፀመዉ ጉዳይ ኢ-ሕገመንግስታዊ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
በወቅቱ ያለመከሰስ መብታቸዉ ሳይነሳ ታስረዉ መቆየታቸዉንና በአካባቢዉ ያለዉን የሰብአዊ መብት ረገጣና የፖለቲካ ተፅእኖ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በፅሑፍ ማሳወቃቸዉንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደአከባቢዉ ማቅናቱንና የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ አንስተዋል።
" ከስራ የተሰናበቱበትና ወደ ስራ እንዳይመለሱ የሚደረግበት አግባብ ከፍተኛ የፖለቲካ ተፅእኖ ያለበት ነዉ " ያሉት አቶ ስዩም ፤ የኢዜማ ፓርቲ በአከባቢው ያለዉን የፖለቲካ ጫናና ተያያዥ ጉዳዮችን ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በጽሑፍ አቅርቦ ባለድርሻ አካላት የተካተቱበት ግብረሃይል ተዋቅሮ ቦታዉ ድረስ በመሄድ በሰጠዉ አቅጣጫ መሠረት አቶ አማንያስ በዋስ እንዲፈቱ መደረጉን ተናግረዋል።
አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ በተደጋጋሚ ብጠይቅም የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤትና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ' ያለመከሰስ መብትህ እስካልተነሳ ድረስ መመለስ አንችልም ' ተብያለሁ " በሚል ላነሱት ቅሬታ ከከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ጽ/ቤትና ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" በአስር ቀናት ዉስጥ የ19 ሰዎች ሕይወት አልፏል " - የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ
በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን አኮቦ ወረዳ ከቀናት በፊት እንደተከሰተ በተነገረዉ የኮሌራ በሽታ በጥቂት ቀናት ብቻ 19 ሰዎች ሲሞቱ ከ280 በላይ ሰዎች ላይ በበሽታዉ መያዛቸውን የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ከደቡብ ሱዳን እንደገባ በተገመተዉ ይህ የኮሌራ በሽታ የካቲት 3/2017 ዓ/ም በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን ስር ከሚገኙ አምስት ወረዳዎች አንዱ በሆነዉ አኮቦ ወረዳ መከሰቱን የሚናገሩት የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጋትቤል ጌርማል በሽታዉ ቀስ በቀስም በቀሪዎቹ አራት የዞኑ ወረዳዎች በላሬ፣ በመኮይ፣ በዋንቱዋ፣ በጂካዎ ወረዳዎች መከሰቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
በሽታዉ አስቀድሞ የተገኘበት የአኮቦ ወረዳ የሀገራችን ጠረፋና ቦታና በየብስ (በመሬት ላይ) ትራንስፖርት የማይገገባበትና የስልክ አገልግሎት የለሌበት አከባቢ በመሆኑ መረጃ ለመሰብሰብም ሆነ አፋጣኝ የሕክምና እርዳታ ለማድረስ አዳጋች ማድረጉን ጠቁመዉ ከላይ በተጠቀሰዉ በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች ቁጥር የአኮቦ ወረዳ መረጃ አለመካተቱን ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አቤል አስፋዉ በበኩላቸዉ በአሁኑ ወቅት በሽታዉ ከአምስቱ የኑዌር ዞን ወረዳዎች በተጨማሪ በጋምቤላ ከተማና የጋምቤላ ዙሪያ ወረዳ እንዲሁም በክልሉ ባሉ ሶስት የስደተኞች ካምፖች በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸዉን ተናግረዉ በአሁኑ ወቅት የበሽታዉን ስርጭት መግታት ከክልሉ አቅም በላይ መሆኑን ገልፀዋል።
አሁን ላይ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚደረገዉን ርብርብ የባለሙያዎች ቁጥር ማነስና የአካባቢዎቹ መልካምድራዊ አቀማመጥ አስቸጋሪ መሆን በተለይም በሽታዉ አስቀድሞ ወደተከሰተበት የአኮቦ ወረዳ ለመሄድ ብቸኛዉ አማራጭ የጀልባ ላይ ጉዞ በመሆኑና በአከባቢዉ የስልክ ኔትወርክ ባለመኖሩ በደቡብ ሱዳን ኔትወርክ መረጃ መለዋወጥ ስራዉ አዳጋች አድርጎታል ብለዋል።
ዶ/ር አቤል አክለዉም የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የበሽታዉን ስርጭት ለመግታት እንዲያግዝ 1.6 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው መድኃኒቶችና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉንና የፌዴራልና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸዉን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን አኮቦ ወረዳ ከቀናት በፊት እንደተከሰተ በተነገረዉ የኮሌራ በሽታ በጥቂት ቀናት ብቻ 19 ሰዎች ሲሞቱ ከ280 በላይ ሰዎች ላይ በበሽታዉ መያዛቸውን የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ከደቡብ ሱዳን እንደገባ በተገመተዉ ይህ የኮሌራ በሽታ የካቲት 3/2017 ዓ/ም በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን ስር ከሚገኙ አምስት ወረዳዎች አንዱ በሆነዉ አኮቦ ወረዳ መከሰቱን የሚናገሩት የኑዌር ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ጋትቤል ጌርማል በሽታዉ ቀስ በቀስም በቀሪዎቹ አራት የዞኑ ወረዳዎች በላሬ፣ በመኮይ፣ በዋንቱዋ፣ በጂካዎ ወረዳዎች መከሰቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
በሽታዉ አስቀድሞ የተገኘበት የአኮቦ ወረዳ የሀገራችን ጠረፋና ቦታና በየብስ (በመሬት ላይ) ትራንስፖርት የማይገገባበትና የስልክ አገልግሎት የለሌበት አከባቢ በመሆኑ መረጃ ለመሰብሰብም ሆነ አፋጣኝ የሕክምና እርዳታ ለማድረስ አዳጋች ማድረጉን ጠቁመዉ ከላይ በተጠቀሰዉ በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች ቁጥር የአኮቦ ወረዳ መረጃ አለመካተቱን ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አቤል አስፋዉ በበኩላቸዉ በአሁኑ ወቅት በሽታዉ ከአምስቱ የኑዌር ዞን ወረዳዎች በተጨማሪ በጋምቤላ ከተማና የጋምቤላ ዙሪያ ወረዳ እንዲሁም በክልሉ ባሉ ሶስት የስደተኞች ካምፖች በበሽታዉ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸዉን ተናግረዉ በአሁኑ ወቅት የበሽታዉን ስርጭት መግታት ከክልሉ አቅም በላይ መሆኑን ገልፀዋል።
አሁን ላይ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የሚደረገዉን ርብርብ የባለሙያዎች ቁጥር ማነስና የአካባቢዎቹ መልካምድራዊ አቀማመጥ አስቸጋሪ መሆን በተለይም በሽታዉ አስቀድሞ ወደተከሰተበት የአኮቦ ወረዳ ለመሄድ ብቸኛዉ አማራጭ የጀልባ ላይ ጉዞ በመሆኑና በአከባቢዉ የስልክ ኔትወርክ ባለመኖሩ በደቡብ ሱዳን ኔትወርክ መረጃ መለዋወጥ ስራዉ አዳጋች አድርጎታል ብለዋል።
ዶ/ር አቤል አክለዉም የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የበሽታዉን ስርጭት ለመግታት እንዲያግዝ 1.6 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው መድኃኒቶችና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉንና የፌዴራልና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸዉን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር ቱርካናና ዳሰነች አከባቢ በተከሰተዉ ግጭት እስካሁን 5 ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል " - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር
⚫️ " በአከባቢዉ ዛሬ ከማለዳዉ 2 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ከፍተኛ ተኩስ ነበር ! "
በጎረቤት ሀገር ኬንያ ቱርካና እና ኢትዮጵያ ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች አከባቢ በአሳ ማጥመጃ ጀልባና መረብ ስርቆቶች እንደተነሳ በተገለጸ የአርብቶ አደሮች ግጭት ባለፉት ሶስት ቀናት 5 ኢትዮጵያዊያን መገደላቸውን የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ 28 ቀበሌዎች ከጎረቤት ሀገር ኬንያ ጋር ድንበር የሚጋሩ ሲሆን በአከባቢዉ በሁለቱ ሀገራት አዋሳኝ ላይ ከሚገኘው የቱርካና ሀይቅ አሳ በማስገር ስራ የአከባቢው አርብቶ አደሮች በጋራ ሲጠቀሙ የቆዩ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ በኢትዮጵያ በኩል የአሳ ምርት መበራከቱንና የኬንያ አርብቶ አደሮች ወደ ኢትዮጵያ ዘልቀዉ የመግባትና የአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባዎች (ዛተራ) የመስረቅ አዝማሚያዎች እየተበራከቱ መምጣታቸውን የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።
ይህን ተከትሎም ባሳለፍነዉ ሳምንት በኬንያ ቱርካና ግዛት የአከባቢው አስተዳዳሪዎች ጋር በመነጋገር መግባባት ላይ በመድረስና ከሁለቱም አከባቢ አርብቶ አደሮች ጋር ለመወያየት ቀጠሮ ተይዞ በነበረበት የኬንያ አርብቶ አደሮች ከትላንት በስቲያ ሁለት ኢትዮጵያዊያንን በትላንትናው ዕለት ደግሞ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላትን መግደላቸዉን ተከትሎ የዳሰነች አርብቶ አደሮች አስከሬን ለመዉሰድና ለአፀፋ ተኩስ ከፍተዉ እንደነበር የወረዳዉ መንግስት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቋል።
በዛሬዉ ዕለት በተለያዩ ተሽከርካሪዎች ታግዘዉ ከኬንያ በኩል በርከት ያሉ የታጠቁ ሃይሎች ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ እስከ ቀትር 9 ሰዓት ድረስ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ገብተዉ ሲታኮሱ መዋላቸዉን የገለፀው የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር የኬንያ ፓርላማ አባላት ወደ አከባቢው በመምጣት ተኩሱን ማስቆማቸዉንና ዜጎቻቸዉን ከኢትዮጵያ መሬት ማስወጣታቸውንና ከዳሰነች ወረዳና የዞን ፀጥታ መዋቅር ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን አስረድተዋል።
ግጭቱ የተከሰተበት ቦታ ከደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ ዋና ከተማ ኦሞ ራቴ 30 ኪሎሜትር ርቀት አከባቢ ሲሆን በተለይም በኬንያ ቱርካና ' ኮኮሮ '/ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢና በኢትዮጵያ ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሪኮ አከባቢ መሆኑም ተገልጿል።
የኬንያ አንዳንድ ሚዲያዎች ከ20 በላይ የሀገሪቱ አሳ አስጋሪዎች " በቱርካና ሀይቅ ላይ ከኢትዮጵያ በኩል ሜሪሌ አከባቢ በገቡ ታጣቂዎች ተገድለዋል " የሚል ዘገባ እየሰሩ ናቸው።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
⚫️ " በአከባቢዉ ዛሬ ከማለዳዉ 2 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ከፍተኛ ተኩስ ነበር ! "
በጎረቤት ሀገር ኬንያ ቱርካና እና ኢትዮጵያ ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች አከባቢ በአሳ ማጥመጃ ጀልባና መረብ ስርቆቶች እንደተነሳ በተገለጸ የአርብቶ አደሮች ግጭት ባለፉት ሶስት ቀናት 5 ኢትዮጵያዊያን መገደላቸውን የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ 28 ቀበሌዎች ከጎረቤት ሀገር ኬንያ ጋር ድንበር የሚጋሩ ሲሆን በአከባቢዉ በሁለቱ ሀገራት አዋሳኝ ላይ ከሚገኘው የቱርካና ሀይቅ አሳ በማስገር ስራ የአከባቢው አርብቶ አደሮች በጋራ ሲጠቀሙ የቆዩ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ በኢትዮጵያ በኩል የአሳ ምርት መበራከቱንና የኬንያ አርብቶ አደሮች ወደ ኢትዮጵያ ዘልቀዉ የመግባትና የአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባዎች (ዛተራ) የመስረቅ አዝማሚያዎች እየተበራከቱ መምጣታቸውን የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።
ይህን ተከትሎም ባሳለፍነዉ ሳምንት በኬንያ ቱርካና ግዛት የአከባቢው አስተዳዳሪዎች ጋር በመነጋገር መግባባት ላይ በመድረስና ከሁለቱም አከባቢ አርብቶ አደሮች ጋር ለመወያየት ቀጠሮ ተይዞ በነበረበት የኬንያ አርብቶ አደሮች ከትላንት በስቲያ ሁለት ኢትዮጵያዊያንን በትላንትናው ዕለት ደግሞ ሶስት የአንድ ቤተሰብ አባላትን መግደላቸዉን ተከትሎ የዳሰነች አርብቶ አደሮች አስከሬን ለመዉሰድና ለአፀፋ ተኩስ ከፍተዉ እንደነበር የወረዳዉ መንግስት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቋል።
በዛሬዉ ዕለት በተለያዩ ተሽከርካሪዎች ታግዘዉ ከኬንያ በኩል በርከት ያሉ የታጠቁ ሃይሎች ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ እስከ ቀትር 9 ሰዓት ድረስ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ገብተዉ ሲታኮሱ መዋላቸዉን የገለፀው የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር የኬንያ ፓርላማ አባላት ወደ አከባቢው በመምጣት ተኩሱን ማስቆማቸዉንና ዜጎቻቸዉን ከኢትዮጵያ መሬት ማስወጣታቸውንና ከዳሰነች ወረዳና የዞን ፀጥታ መዋቅር ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን አስረድተዋል።
ግጭቱ የተከሰተበት ቦታ ከደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ ዋና ከተማ ኦሞ ራቴ 30 ኪሎሜትር ርቀት አከባቢ ሲሆን በተለይም በኬንያ ቱርካና ' ኮኮሮ '/ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢና በኢትዮጵያ ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሪኮ አከባቢ መሆኑም ተገልጿል።
የኬንያ አንዳንድ ሚዲያዎች ከ20 በላይ የሀገሪቱ አሳ አስጋሪዎች " በቱርካና ሀይቅ ላይ ከኢትዮጵያ በኩል ሜሪሌ አከባቢ በገቡ ታጣቂዎች ተገድለዋል " የሚል ዘገባ እየሰሩ ናቸው።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶአደሮች ተፈናቅለዋል " - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር 🚨" አሁንም ከኬንያ ቱርካና ግዛት በኩል ዛቻዎች ስላሉ ስጋት ዉስጥ ነን ጥበቃና ከለላ ይደረግልን " - አርብቶአደሮች በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር ደቡብ ኦሞ ዳሰነች ወረዳና በኬንያ ቱርካና ግዛት አዋሳኝ አከባቢ ባለፉት ሁለት ቀናት በአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባ ስርቆቶች እንደተቀሰቀሰ በተነገረዉ ግጭት የበርካቶች…
" ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ነዉ ፤ የአስክሬን ፍለጋዉም ተጠናክሮ ቀጥሏል " - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ እና በሰሜን ኬንያ ቱርካና የድንበር አከባቢ ተከስቶ በነበረዉ ግጭት ምክንያት ስየስ ከተባለ የዳሰነች መንደር ተፈናቅለዉ የነበሩ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶአደሮች ወደ ቀያቸዉ መመለስ መጀመራቸዉን የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በቀጠናዉ በአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባ ስርቆቶች መነሻ እንደተቀሰቀሰ በተገለፀዉ ግጭት ከሁለቱም ሀገሮች ከ30 በላይ አርብቶአደሮች ሕይወት መጥፋቱን መዘገባችን አይዘነጋም።
ግጭቱን ተከትሎም ኬንያን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናት የቱርካና ሀይቅ ሰሜናዊ ጠረፍ ላለፉት አምስት ቀናት ከእንቅስቃሴ ዉጪ ሲሆን ከዳሰነች ወረዳ ስየስ መንደር በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች በአቅራቢያቸዉ ወደሚትገኘዉ ሌላ መንደር ተፈናቅለዉ ነበር።
በትናትዉ ዕለት የዳሰነችና የቱርካና አከባቢ አስተዳደሮች ባሉበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የተመራ ልዑክ ከኢትዮጵያ በኩል በኬንያ የቱርካና ካውንቲ የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነርና የአከባበው የፓርላማ ተወካይ የተመራ ልዑክ በሁለቱ ሀገራት የድንበር አከባቢ ተፈጠሮ የነበረዉን ግጭት በፍጥነት ለመፍታትና አከባቢውን ወደነበረበት ሰላም ለመመለስ መነጋገራቸዉን ተከትሎ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸዉ የመመለስ እየተሰራ እንደሆነ አቶ ታደለ ሀቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን በሀይቅ ዉስጥ የጠፉ አስከሬኖች የማፈላለጉ ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ያነሱት አቶ ታደለ በሁለቱም ወገን የተወሰዱ ንብረቶችን የማስመለስና በአከባቢዉ ጠንካራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ተጠናክረዉ በሚቀጥሉበት ዙሪያ ዉይይት ማድረጋቸዉን አስታዉቀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ እና በሰሜን ኬንያ ቱርካና የድንበር አከባቢ ተከስቶ በነበረዉ ግጭት ምክንያት ስየስ ከተባለ የዳሰነች መንደር ተፈናቅለዉ የነበሩ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶአደሮች ወደ ቀያቸዉ መመለስ መጀመራቸዉን የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በቀጠናዉ በአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባ ስርቆቶች መነሻ እንደተቀሰቀሰ በተገለፀዉ ግጭት ከሁለቱም ሀገሮች ከ30 በላይ አርብቶአደሮች ሕይወት መጥፋቱን መዘገባችን አይዘነጋም።
ግጭቱን ተከትሎም ኬንያን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናት የቱርካና ሀይቅ ሰሜናዊ ጠረፍ ላለፉት አምስት ቀናት ከእንቅስቃሴ ዉጪ ሲሆን ከዳሰነች ወረዳ ስየስ መንደር በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች በአቅራቢያቸዉ ወደሚትገኘዉ ሌላ መንደር ተፈናቅለዉ ነበር።
በትናትዉ ዕለት የዳሰነችና የቱርካና አከባቢ አስተዳደሮች ባሉበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የተመራ ልዑክ ከኢትዮጵያ በኩል በኬንያ የቱርካና ካውንቲ የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነርና የአከባበው የፓርላማ ተወካይ የተመራ ልዑክ በሁለቱ ሀገራት የድንበር አከባቢ ተፈጠሮ የነበረዉን ግጭት በፍጥነት ለመፍታትና አከባቢውን ወደነበረበት ሰላም ለመመለስ መነጋገራቸዉን ተከትሎ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸዉ የመመለስ እየተሰራ እንደሆነ አቶ ታደለ ሀቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን በሀይቅ ዉስጥ የጠፉ አስከሬኖች የማፈላለጉ ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ያነሱት አቶ ታደለ በሁለቱም ወገን የተወሰዱ ንብረቶችን የማስመለስና በአከባቢዉ ጠንካራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ተጠናክረዉ በሚቀጥሉበት ዙሪያ ዉይይት ማድረጋቸዉን አስታዉቀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
#ነዳጅ #ቤንዚን
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተባባሰ የመጣዉን የነዳጅ ምርቶች ሕገወጥ ግብይት ለመከላከልና በየከተማዉ የሚስተዋሉ ረጃጅም ሰልፎችን በማስቀረትና የተጠቃሚዎችን ቅሬታ ለመፍታት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ።
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አቡዱላሂ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በነዳጅ ምርቶች በተለይ በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ቅሬታዎች እንደሚነሱና ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ስለመኖራቸው ገልፀዋል።
" አንዱና መሠረታዊዉ ምክንያት ከዚህ ቀደም 80 በመቶ የሚሆነዉ የሀገራችንን የነዳጅ ፍጆታ ይሸፍን የነበረዉ በሱዳን ወደብ የሚገባዉ ቢሆንም አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ጅቡቲ ዞሯል " ብለዋል።
" ወደቡ ላይ ከፍተኛ መጨናነቆች ይስተዋላሉ የጅቡቲዉ ወደብ ከ20 ዓመታት በፊት የነበረን የሀገራችንን የነዳጅ ፍላጎትና አቅርቦትን ለማስተናገድ ታስቦ የተሰራ ስለነበር በቴርሚናሉ ላይ ያለዉ መጨናነቅ መንግስት በከፍተኛ ድጎማ የሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች በተለይም በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አሳድሯል " ሰሉ ገልፀዋል።
መንግስት አሁንም ድረስ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማ በማድረግ ወደ ሀገር ዉስጥ በሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች ላይ አንዳንድ አከባቢዎች ሰዉ ሰራሽ አቅርቦት እጥረት እንዲፈጠር በማድረግ የግል ጥቅማቸዉን ለማካበት የሚጥሩ አካላት መኖራቸዉን ማረጋገጣቸውን ወ/ሮ ሰሃረላ ተናግረዋል።
በቴክኖሎጂ የታገዘ ቁጥጥርና የአሠራር ስርዓት በመዘርጋት ሕገወጥ ግብይቱን የመከላከልና በህገወጦች ላይ እርምጃ የመዉሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
" ከአቅርቦቱ ባሻገር ወደ ሀገር ዉስጥ የገባዉን ቤንዚን በአግባቡ በማሰራጨቱ በኩል በየክልሉ የተለያዩ ክፍተቶች አሉ " ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሁሉም ማዕቀፎች ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል መወሰድ በመጀመሩ በርከት ያሉ የንግድና ገበያ ልማት ባለሙያዎች ማደያዎችን ጨምሮ በሕገወጥ ግብይቱ ሰንሰለቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት ላይ በየደረጃው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።
ለአብነትም በሲዳማ ክልል ብቻ የግብይት ስርዓቱ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ በመፍጠር ሰዉ ሰራሽ እጥረት እንዲስፋፋ ያደረጉ 9 ማደያዎች ላይ ነዳጅ እንዳያገኙ እገዳ እንደተላለፈባቸው ገልፀዋል።
በሌሎችም ክልልሎች በዚህ ረገድ እየተከናወኑ ያሉ የቁጥጥርና ክትትል ተግባራት በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀዉ አዲሱ የነዳጅ ምርቶች ቁጥጥር አዋጅ ጋር ተዳምረዉ በዘርፉ የሚስተዋለዉን ችግር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተባባሰ የመጣዉን የነዳጅ ምርቶች ሕገወጥ ግብይት ለመከላከልና በየከተማዉ የሚስተዋሉ ረጃጅም ሰልፎችን በማስቀረትና የተጠቃሚዎችን ቅሬታ ለመፍታት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ።
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አቡዱላሂ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በነዳጅ ምርቶች በተለይ በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ቅሬታዎች እንደሚነሱና ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ስለመኖራቸው ገልፀዋል።
" አንዱና መሠረታዊዉ ምክንያት ከዚህ ቀደም 80 በመቶ የሚሆነዉ የሀገራችንን የነዳጅ ፍጆታ ይሸፍን የነበረዉ በሱዳን ወደብ የሚገባዉ ቢሆንም አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ጅቡቲ ዞሯል " ብለዋል።
" ወደቡ ላይ ከፍተኛ መጨናነቆች ይስተዋላሉ የጅቡቲዉ ወደብ ከ20 ዓመታት በፊት የነበረን የሀገራችንን የነዳጅ ፍላጎትና አቅርቦትን ለማስተናገድ ታስቦ የተሰራ ስለነበር በቴርሚናሉ ላይ ያለዉ መጨናነቅ መንግስት በከፍተኛ ድጎማ የሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች በተለይም በቤንዚን አቅርቦትና ስርጭት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አሳድሯል " ሰሉ ገልፀዋል።
መንግስት አሁንም ድረስ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማ በማድረግ ወደ ሀገር ዉስጥ በሚያስገባቸዉ የነዳጅ ምርቶች ላይ አንዳንድ አከባቢዎች ሰዉ ሰራሽ አቅርቦት እጥረት እንዲፈጠር በማድረግ የግል ጥቅማቸዉን ለማካበት የሚጥሩ አካላት መኖራቸዉን ማረጋገጣቸውን ወ/ሮ ሰሃረላ ተናግረዋል።
በቴክኖሎጂ የታገዘ ቁጥጥርና የአሠራር ስርዓት በመዘርጋት ሕገወጥ ግብይቱን የመከላከልና በህገወጦች ላይ እርምጃ የመዉሰዱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
" ከአቅርቦቱ ባሻገር ወደ ሀገር ዉስጥ የገባዉን ቤንዚን በአግባቡ በማሰራጨቱ በኩል በየክልሉ የተለያዩ ክፍተቶች አሉ " ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሁሉም ማዕቀፎች ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል መወሰድ በመጀመሩ በርከት ያሉ የንግድና ገበያ ልማት ባለሙያዎች ማደያዎችን ጨምሮ በሕገወጥ ግብይቱ ሰንሰለቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት ላይ በየደረጃው እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አብራርተዋል።
ለአብነትም በሲዳማ ክልል ብቻ የግብይት ስርዓቱ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ በመፍጠር ሰዉ ሰራሽ እጥረት እንዲስፋፋ ያደረጉ 9 ማደያዎች ላይ ነዳጅ እንዳያገኙ እገዳ እንደተላለፈባቸው ገልፀዋል።
በሌሎችም ክልልሎች በዚህ ረገድ እየተከናወኑ ያሉ የቁጥጥርና ክትትል ተግባራት በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀዉ አዲሱ የነዳጅ ምርቶች ቁጥጥር አዋጅ ጋር ተዳምረዉ በዘርፉ የሚስተዋለዉን ችግር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንሰዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
" እሳቱ ከሰማይ እንደወረደ በማስመሰል የሚሰራጩት መረጃዎች የተሳሳቱ ናቸው " - ፖሊስ
በሀላባ እና ከንባታ አከባቢ " ሰማይ ላይ እሳት መሰል አካል ታየ " ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ትክክለኛ አይደለም ሲል የአከባቢው ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
ከዚህ ቀደም በደቡብ ኢትዮጵያ ማዕከላዊ ቦታዎች እና በኦሮሚያ ክልል ጉጂና ቦረና አከባቢዎች የታየዉ አይነት በራሪ እሳት መሰል ብርሃናማ አካል ትላንት ሌሊት 6 ሰዓት ገደማ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ እና ከንባታ አከባቢዎች ዳግም መታየቱን በመግለፅ በርካቶች በማህበራዊ የትስስር ገፃቸዉ መረጃዎችን ሲያጋሩ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን ለማጣራት የአከባቢውን የፀጥታ መዋቅሮች አነጋግሯቸዋል።
የከንባታ ዞን ዳንቦያ ወረዳ እና የሀላባ ዞን ወዠዌይራ ወረዳ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት ፤ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለዉ ይህ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ገልጸዋል።
" ጉዳዩ የተከሰተበት ሠዓት እኩለ ሌሊት መሆኑንና በተለይም ከሀላባ ከተማ በኩል ሲታይ በረጅም ተራራ አናት ላይ በድንገት የተከሰተውን እሳት በሌሊት የተነሱት ፎቶዎች ከወራት በፊት በሰማይ ከታየው ብርሃናማ አካል ጋር በማያያዝ ትክክለኛ ያለሆነ መረጃ በርካቶች እንዲቀባበሉ ሳያደርግ እንዳልቀረ " ተናግረዋል።
በሀላባ ዞን ዌይራ ወረዳና በከንባታ ዞን ዳንቦያ ወረዳ አዋሳኝ አከባቢ በሚገኝ ተራራማ ስፍራ በትላንትናው ዕለት ሌሊት 6 ሰዓት አከባቢ እስካሁን ትክክለኛ መንስኤው ያልታወቀ የእሳት አደጋ ተከስቶ ከ7 ሄክታር በላይ ደን ማዉደሙን ገልፀዋል።
እሳቱ የተቀሰቀሰበት ሠዓት እኩለ ሌሊት አከባቢ መሆንና የመልክአምድሩ አስቸጋሪነት ከወቅቱ በጋ መሆን ጋር ተዳምሮ እሳቱን የማጥፋት ሂደት አዳጋች አድርጎት እንደነበር የገለፁት የሁለቱም አጎራባች ወረዳዎች ፖሊስ አዛዦች የእሳት አደጋውን ትክክለኛ መነሻና መንስኤ አጣርተን ለሕዝቡ እናሳዉቃለን ሲሉ ቃል ገብተዋል።
ከዚህ በዘለለ እሳቱ ከሰማይ እንደወረደ በማስመሰል መረጃዎች እያሰራጩ ያሉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አሳስበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በሀላባ እና ከንባታ አከባቢ " ሰማይ ላይ እሳት መሰል አካል ታየ " ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ትክክለኛ አይደለም ሲል የአከባቢው ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
ከዚህ ቀደም በደቡብ ኢትዮጵያ ማዕከላዊ ቦታዎች እና በኦሮሚያ ክልል ጉጂና ቦረና አከባቢዎች የታየዉ አይነት በራሪ እሳት መሰል ብርሃናማ አካል ትላንት ሌሊት 6 ሰዓት ገደማ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ እና ከንባታ አከባቢዎች ዳግም መታየቱን በመግለፅ በርካቶች በማህበራዊ የትስስር ገፃቸዉ መረጃዎችን ሲያጋሩ ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን ለማጣራት የአከባቢውን የፀጥታ መዋቅሮች አነጋግሯቸዋል።
የከንባታ ዞን ዳንቦያ ወረዳ እና የሀላባ ዞን ወዠዌይራ ወረዳ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት ፤ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለዉ ይህ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ገልጸዋል።
" ጉዳዩ የተከሰተበት ሠዓት እኩለ ሌሊት መሆኑንና በተለይም ከሀላባ ከተማ በኩል ሲታይ በረጅም ተራራ አናት ላይ በድንገት የተከሰተውን እሳት በሌሊት የተነሱት ፎቶዎች ከወራት በፊት በሰማይ ከታየው ብርሃናማ አካል ጋር በማያያዝ ትክክለኛ ያለሆነ መረጃ በርካቶች እንዲቀባበሉ ሳያደርግ እንዳልቀረ " ተናግረዋል።
በሀላባ ዞን ዌይራ ወረዳና በከንባታ ዞን ዳንቦያ ወረዳ አዋሳኝ አከባቢ በሚገኝ ተራራማ ስፍራ በትላንትናው ዕለት ሌሊት 6 ሰዓት አከባቢ እስካሁን ትክክለኛ መንስኤው ያልታወቀ የእሳት አደጋ ተከስቶ ከ7 ሄክታር በላይ ደን ማዉደሙን ገልፀዋል።
እሳቱ የተቀሰቀሰበት ሠዓት እኩለ ሌሊት አከባቢ መሆንና የመልክአምድሩ አስቸጋሪነት ከወቅቱ በጋ መሆን ጋር ተዳምሮ እሳቱን የማጥፋት ሂደት አዳጋች አድርጎት እንደነበር የገለፁት የሁለቱም አጎራባች ወረዳዎች ፖሊስ አዛዦች የእሳት አደጋውን ትክክለኛ መነሻና መንስኤ አጣርተን ለሕዝቡ እናሳዉቃለን ሲሉ ቃል ገብተዋል።
ከዚህ በዘለለ እሳቱ ከሰማይ እንደወረደ በማስመሰል መረጃዎች እያሰራጩ ያሉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አሳስበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia