TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
“ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶታል” - ጤና ሳይንስ ኮሌጁ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥበበ ግዮን ግቢ ስፔሻላንስድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ዳኘ በተተኮሰባቸው ጥይት መገዳላቸውን ዩኒቨርሲቲውና ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ለደህንነታቸው…
' በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን ! '

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት በፊት ሥራ ቦታ ላይ አንድ የኮሌጁ ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” - የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር

የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር (ባሕር ዳር) “በጥይት ተገደሉ” በተባሉት በዶክተር አንዷለም ዳኘ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፤ “ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ማኀበሩ ይህን ያለው በኮሌጁ አካላትም ሆነ በኢንተርን ሀኪሞች የግድያና የዘረፋ ሙከራዎች እየተደረጉባቸው መሆናቸውን በመግለጽ ጭምር ነው።

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት  በፊት ሥራ ስራ ቦታ ላይ የነበረ አንድ የህክምና ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” ሲልም አስታውሷል።

ማኀበሩ ስለዶክተር አንዷለም ግድያና ስለስጋቱ ምን አሉ?

“ የዶክተር አንዷለም ዳኘ የቀብር ሥነ ስርዓት በድባንቄ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

ዶክተር አንዷለም ትሁት ሀኪም ነበር። ስለሞተ ሳይሆን እውነታው ይሄው ስለሆነ ነው ይህን የምንለው። ስለሞተ ለመሞጋገስ አይደለም። ከሰውም ሰው ስለነበር እንጂ።

አሟሟቱም ልብ ሰባሪ ነው። ሙያው ሰብ ስፔሻሊስት ነው። አንቱ በሚባልበትና ህዝብን የሚያገለግልበት እድሜ ላይ ነው ያጣነው። እንደ ህክምና ተማሪዎች የእውቀት አባታችንን፤ ወንድማችንን ነው ያጣነው።

ይህን የመሰለ ሰብ ስፔሻሊቲ ሀኪም ማጣት እንደ ሀገርም እንደ ህዝብም በጣም ያማል። መራር ሀዘን ገጥሞናል።

በነገራችን ላይ ተደጋጋሚ ችግሮች አሉ። የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ስልክ ተቀምቶ፣ በሽጉጥ ማንገራገር ገጥሞት ነበር፤ በኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ይደረጋል።

በዚሁ የተነሳ ሰብ ስፔሻሊስቶች አገር እየለቀቁ፤ እየሸሹ ነው። ይሄ ባለበት ሁኔታ ጥበቃ፣ ከለላ አለመደረጉ በጣም ያሳዝናል። በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን። የሆስፒታሉ ኃላፊ፣ ኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ተደርጎባቸል።

የኮሌጁ ኃላፊዎችም ከአቅማቸው በላይ የሆነባቸው ይመስለናል። ምንም ከለላ የለም። ግቢ ያሉ ጥበቃዎችም የተጠናከረ አይደለም። ውጪ ላይ ይቅርና ግቢ ውስጥ ራሱ ከፍተኛ ስጋት አለ። አቤት የምንልበት አጥተን ነው እንጂ ” ብሏል።

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች መጪውን ጊዜ ለማስተካከል እንዲተጉ፣ ስለመብታቸው ዘብ እንዲቆሙ፣ አንድነት በመፍጠር የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ ማኀበሩ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ

ስለ ብርሃን ዕቁብ ሰምተዋል ?

በባንካችን ለሚከፈቱ ዕቁቦች ሁሉ የተሻለ ወለድ እና ለአባላት የሚሆኑ የብድር አማራጮችን የሚያስገኝ ህልምዎን የሚያሳኩበት መልካም እድል በብርሃን ዕቁብ ቀርቦሎታል፡፡ ደንበኞች ለዚህ አገልግሎት ማሞላት ያለባቸው መስፈርቶች;
-ሒሳቡን በጣምራ የሚከፍቱት አባላት ከመሀበሩ የውክልና ህጋዊ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል
-የታደሰ መታወቂያ/ፋይዳ መታወቂያ
-የሁሉም እቁብ አባላት ስም ዝርዝር
-ሁሉም የእቁብ አባላት የብርሀን ባንክ የግል ሂሳብ ሊኖራቸው ይገባል
በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ ቅርንጫፍ ጎራ ብለው ወይም በ 8292 የደንበኞች አገልግሎት ቁጥር ደውለው ዝርዝር መረጃ ማግኘት ይችላሉ።
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ሥራችን!
#SafaricomEthiopia

🏆የኮከቦቹ ውድድር ተጠናቀቀ! 🤩

በአይነቱ የመጀመሪያው የሆነው እና ላለፉት ወራት ስናካሂደው የነበረው የ#1Wedefit ዲጂታል የሙዚቃ ውድድር በደመቀ መልኩ ፍጻሜውን አግኝቷል!

ሙሉውን የመጨረሻውን ክፍል YouTube ላይ ታገኙታላችሁ! 👉🏾 https://youtu.be/zBMhIHTMJAc

#1Wedefit
#FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴" በ104.4 የመቐለ ኤፍኤም ያጋጠመው ችግር በመግባባት እንዲፈታ አድርጊያለሁ  ስልጣን መረከብ የሚፈልግ አካል እና ግለሰብ ህግ እና ስርዓት ያክብር  " - የመቐለ ከተማ ፓሊስ  " ሬድዮ ጣቢያችን ለሁለት የተሰነጠቁ ቡድኖች መጫወቻ እንዲሆን አንፈቅድም " - የመቐለ FM አመራር ጥሪ 21 / 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት 5 ታጣቂዎች አስከትሎ የመቐለ ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያን…
#Update

" ህጋዊ ስራ አስኪያጅ እኔ ነኝ ወደ ስራ ቦታየ እንዳልገባ ፓሊስ ከልክሎኛል " - የ104.4 ኤፍ ኤም መቐለ ሹመኛ መሆናቸውን የሚናገሩት ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ

" ሹመኛ ነኝ " ያሉት በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በመቐለ ከተሾመው ከንቲባ በኋላ ህዳር 2017 ዓ.ም የኤፍ ኤም ሬድዮው ስራ አስኪያጅ ሆኖው መመደባቸው የገለጹት ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ የከተማዋ ፓሊስ ወደ ስራ ቦታቸው እንዳይገቡ መከልከሉ " አግባብ " አይደለም ብለዋል።

ለኤፍኤም ሬድዮ ጣብያው የከተማዋን ምክር ቤት እና አሰራር በጣሰ መልኩ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ወዲህ ሦስት ስራ አስኪያጆች መመደባቸው የገለፁት ዘመንፈስቅዱስ ፍስሃ ይህ አካሄድ እንዲታረምና ወደ ስራቸው እንዲገቡ ጠይቀዋል።

ከተመደቡበት ወርሃ ህዳር 2017 ዓ.ም ሦስቴ ወደ ስራ ገበታቸው ለመግባት ያደረጉት ጥረት በኤፍ ኤም ሬድዮው በሚገኙ አመራሮች መስተጓጉሉም አምርረው የነቀፉት ዘመንፈስቅዱስ ከጥር 22/2017 ዓ.ም በኋላ ወደ ስራ ገበታቸው ለመግባት ያደረጉት ጥረት ከዛ በፊት አይተዋቸው የማያውቁ ታጣቂዎች ተመድበው  እንደተደናቀፋባቸው በምሬት ተናግረዋል። 

104.4 የመቐለ ኤፍኤም ከተማዋ ባቋቋመው ቦርድ የሚመራ እንደሆነ የጠቀሱም ሱሆን " ቦርዱ እኔ ህጋዊ ስራ አስኪያጅ አድርጎ ሹመኛል ስለሆነም ስራዬን እንድሰራ በጣብያው ያሉ ህገ-ወጦች ስርዓት መያዝ አለባቸው " ብለዋል።

ጥር 22/2017 ዓ.ም በ104.4 ኤፍ ኤም መቐለ ቅጥር ግቢ " እኔን ነኝ ህጋዊ ሹመኛ ... እንተ አይደለህም " በሚል በተፈጠረ ግርግር ፓሊስ ደርሶ በውይይት መፍታቱ መዘገባችን ይታወሳል።

የወዝግቡ መነሻ ለሁለት ከተከፈሉት የህወሓት አመራሮች የሚያያዝ ሆኖ በጣብያው የሚገኙ አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ቅቡልነት ያላቸው ፤ አዲሱ ተሿሚ ደግሞ በድብረፅዮኑ ህወሓት ድጋፍ ያላቸው ናቸው።

በ2001 ዓ.ም የተቋቋመው 104.4 የመቐለ ኤፍ ኤም በአገሪቱዋ የሚድያ ህግ የተቋቋመ እና በየአመቱ ተገቢ ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት መሆኑ ይታወቃል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
" ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል ! " - የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር 

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ለትግራይ ህዝብ በተለይ ደግሞ ለልሂቃን መልእክት እና ምክር አስተላልፈዋል። 

ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥር 26/2017 ዓ.ም በፅሁፍ ባስተላለፉት ጠንካራ መልእክት እና ምክር ትግራይን እና ህዝብዋን " የጥንታዊ እና ገናና ታሪክ ባለቤት የኢትዮጵያ ዋልታና መከታ " ሲሉ ገልፀዋቸዋል።

" የትግራይ ህዝብ ታሪክ የማያረጅ እና የማይደበዝዝ በደማቅ ቀለም የተፃፈ ነው " ያሉ ሲሆን " ክልሉ ለህዝባቸው እና አገራቸው የሚጠቅሙ በርካታ ሊቃውንት ፣ የሃይማኖት መሪዎች ፣ ፓለቲከኞች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ያፈራ ነው " ሲሉ ፅፈዋል።

የትግራይ ህዝብ የዘመናት ተጋድሎዎች ያወሱ እና ያወደሱት ጠቅላይ ሚንስትሩ " የአገር ፍቅር ስሜት የትግራይ ህዝብ መለያ እና መገለጫ ነው " ብለዋል።

" ቢሆንም መጥፎ አጋጣሚ ሆኖ በተለይ ባለፉት አንድ መቶ ዓመታት ከማእከላይ መንግስቱ ለተደጋጋሚ ጊዜዎች ግጭት ውስጥ በመግባት ትግራይ የጦርነት አውድማ ፤ ህዝቡም ደግሞ የሁሉም ዓይነት ችግሮች ተጋላጭ እና ተጠቂ መሆኑን " ጠቅላይ ሚንስትሩ አውስተው " የሚያጋጥሙ እና የሚፈጠሩ ችግሮች ከውግያ በመለስ የሚፈቱበት አማራጭ አልነበረም ወይ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

" ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል ፤ ይህንን ዓይነት አደጋ የሚፈጥር ችግር እንዴት መፍታት እና ማስወገድ እንደሚቻል በግልፅ መነጋገር እንደሚያስፈልግ ለአስተዋይ የሚሰወር አይደለም " ብለዋል።

" ስለሆነም በፓለቲካ ፣ በንግድ ፣ ፀጥታ ፣ አካዳሚ እና ሚድያ እና በሌሎች የስራ ዘርፎች የተሰማራችሁ የትግራይ ልሂቃን ወገኖች የትግራይ ህዝብ እስከ ዛሬ የተሰቃየው የከፈለው ዋጋ ይብቃው ፤ ልዩነትን በመነጋገር እና በውይይት የመፍታት ባህልንና ልምድ ታጠቁ " ሲሉ መክረዋል።

ልሂቃኑ ከፌደራል መንግስት እና ሌሎች ሃይሎች ያላቸው ልዩነት በአገሪቱ ህገ-መንግስት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመግባባት ለመፍታት ዝግጁ እንዲሆኑ ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።

" የፌደራል መንግስት በሁሉም አጀንዳዎች ለመነጋገር ፤ የሃሳብ ልዩነት ደግሞ እንደልዩነት በማክበር ፣ በሚያግባቡ አገራዊ ርእሰ ጉዳዮች በመስማማት ለመስራት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩ የትግራይ ህዝብ እና ልሂቃኑ መገንዘብ አለባችሁ " ብለዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልእክታቸው ማሳረግያ " ሰላም እና ብሩህ መፃኢ ለትግራይ ህዝብ ፣ ግጭት እና ጦርነት ይብቃ ! " የሚል መልካም ምኞታቸው አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopia            
#እናትፓርቲ

እናት ፓርቲ የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ያደረገው የጣሪያ ግድግዳ/ ንብረት ግብር መመርያ እንዲቆም የመሠረተው ክስ በፍርድ ቤት ተቀባይነት አግኝቶ መመሪያው "ተፈጻሚ ሊሆን አይገባም" ሲል ፍርድ ቤት ጥር 9 ቀን ብይን መስጡቱን ፓርቲው አስታውቋቃ።

ፓርቲው የወጣው መመርያ " ሕግን ባልተከተለ መንገድ እና የከተማ አስተዳደሩ ባልተሰጠው ሥልጣን የወጣ በመሆኑ " መመሪያው እንዲሻሻል ሲል በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አስተዳደር ችሎት ክስ መስሮቶ መቆየቱን ገልጿል።

ፍ/ቤቱ የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ያቀረባቸውን ሦስት መቃወምያዎች ውድቅ አድርጎ ወደ ፍሬ ነገር ክርክር ከገባ በኋላ ጉዳዩን መርምሮ መመሪያው " ተፈጻሚነት ሊኖረው አይገባም " የሚል ውሳኔ መስጠቱን፤ የውሳኔውን አፈጻጸም እንደሚከታተልም ፓርቲው አስታውቋል።

(ፓርቲው የላከው መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
Some wait for opportunities. Others create them. Which one are you? The Jasiri Talent Investor Program invites bold, innovative thinkers ready to take action. Don’t miss out on our 8th Cohort. Click the link to start your application, https://bit.ly/4aGlAm8.

#Jasiri4Africa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የአፖሎ አካውንት በመክፈት ወይም የአፖሎን መተግበርያ ለሌሎች በማጋራት አንዲሁም ገንዘብ ተቀማጭ በማድረግ የተለያዩ ሽልማቶችን ያሸንፉ።

የመርሃ ግብሩን ዝርዝር መረጃ ከዚህ በታች ያግኙ፡፡
https://yangx.top/BoAEth/1525


አፖሎን በማውረድ ተሳታፊ ይሁኑ፡
ለአንድሮይድ ስልኮች: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US
ለአፕል ስልኮች: https://apps.apple.com/eg/app/apollo-digital/id1601224628
ለህዋዌ ስልኮች ፡https://appgallery.huawei.com/app/C108966741

#መጣሁልሽ #አምሮኛል_መጣሁልሽ #ApolloWinBig #DepositAndWin #JoinApolloGetRewarded
#Ethiotelecom

የካቲት 07 ይጠናቀቃል፤ ፈጥነው የኢትዮ ቴሌኮም የአክሲዮን ባለቤት ይሁኑ!!

💁‍♂️ የአክሲዮን ሽያጩ በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ይከናወናል፤ የመሸጫው ጊዜ ገደብ ከመጠናቀቁ በፊት የኢትዮ ቴሌኮም የቀጥታ ድርሻ ባለቤት ይሁኑ!!

🗓 እስከ የካቲት 07/2017 ዓ.ም ብቻ!

📖 የደንበኛ ሳቢ መግለጫውን https://teleshares.ethiotelecom.et/ ያንብቡ፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ወደ 128 ይደውሉ !

#telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቄዶንያ❤️ 🔵 “ የጎዳና ኑሮ ከባድ ነው፣ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ” - የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ 🔴 “ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል ” - ቀሲስ ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ከመቄዶንያ በጎ…
#መቄዶንያ

“ ህንፃው ለማጠናቀቅ ገንዘብ ተቸግረናል። ለማጠናቀቅ ወደ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልገናል ” - መቄዶንያ

መቄዶንያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በሚያስገነባው ሆስፒታል ጭምር ያለው ህንፃ ለማጠናቀቅ የገንዘብ እጥረት ስለገጠመው እርዳታ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ።

ከየካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ “ በሰይፉ ኢቢኤስ የዩቱብ ቻነል ” ድጋፍ ማድረጊያ መርሀ ግብር ስለሚጀመር ደጋጎች ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርጉ በአንጽንኦት ተጠይቋል።

ይህ የተባለው ዛሬ በመቄዶኒያ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

የመቄዶንያ መስራች የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ደግሞ፣ “ ይህን ህንፃ ጀምረነዋል። ለማጠቀቅ ገንዘብ ተቸግረናል። 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልገናል ” ብለዋል።

ህንፃው ምን የማጠቃለያ ስራዎች ቀርተውት ነው ድጋፍ ያስፈለገው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበላቸው ጥያቄ፣ “ ሴራሚክ የባኞ ቤት እቃዎች፣ 7 ሊፍቶች፣ የኤሌክትሪክ ፊኒሽንግ እቃዎች ገና ናቸው ” ሲሉ መልሰዋል።

በመቄዶንያ ምን ያክል የአእምሮ ህሙማን አሉ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ ደግሞ፣ “ ወደ 2,500 የአእምሮ ሆሙማን፤ ከ2,000 በላይ ዳይፐር ተጠቃሚዎች፣ ከዚያ ውጪ ያሉት አረጋዊያን ናቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ፣ “ በ44 ቅርንጫፍ ከ8,000 በላይ ሰዎች አሉ። በየጊዜው ሰው እየጨመረ ነው የሚሄደው። ህክምና የሚፈልጉ ሰዎች ጭምር ናቸው ያሉት ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

መቄዶንያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ከ8,000 በላይ ወገኖችን ከጎዳና በማንሳት በ44 ቅርንጫፎች በቀን ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት ሰብዓዊ ድጋፍ የሚረዳ ማዕከል ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia