🪪 የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ ይመዝገቡ!!
የካርድ ኅትመት አገልግሎት በአዲስ አበባ፣ በሐዋሳ፣ አዳማ፣ ወላይታ ሶዶ እና ነቀምቴ ከተሞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ‘’NID (Fayda) Printing’’ መተግበሪያ ተጠቅመው የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
የካርድ ኅትመት አገልግሎት በአዲስ አበባ፣ በሐዋሳ፣ አዳማ፣ ወላይታ ሶዶ እና ነቀምቴ ከተሞች እየተሰጠ ይገኛል፡፡
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ‘’NID (Fayda) Printing’’ መተግበሪያ ተጠቅመው የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
" ተመዝግበንና ክፍያም ከፍለናቸው ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ ባለንበት ዩኒቨርሲቲዉ አላስተምራችሁም ብሎናል " - የሪሚዲያል ተማሪዎች
➡️ " ዉሳኔዉ የትምህርት ሚንስቴ እንጂ የዩኒቨርሲቲው አይደለም " - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
" የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ወራት ፊት በሣምንቱ የዕረፍት ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት የምዝገባ እና የመማሪያ ክፍያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ እያለን ዩኒቨርሲቲው ሌሎች አማራጮችን መጠቀሚያ ጊዜ ባለፈብን በዚህ ወቅት አላስተምራችሁም ብሎናል " ሲሉ ተማሪዎሽ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።
ቅሬታቸዉን ካደረሱን ተማሪዎች መካከል በመደበኛው የትምህርት ሚንስቴር ምደባ ጅግጅጋ ፣ሰላሌ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተመደብዉ እያለ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) በእረፍት ቀናት በክፍያ ለማስተማር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ከቤተሰብ ላለመራቅና በአንዳንድ አከባቢዎች ካለዉ የፀጥታ ችግር የተነሳ ከፍለዉ ለመማር በመወሰን የምዝገባና የትምህርት ክፍያ አጠናቀው የትምህርት መጀመርን ሲጠባበቁ እንደነበር ገልፀዉ ዩኒቨርሲቲዉ " ኃላፊነት በጎደለው መልኩ 'ትምህርት ሚንስቴር በግል ከፍሎ መማርን ስላልፈቀደ ማስተማር የማንችል በመሆኑ ክፍያችሁን መዉሰድ ትችላላችሁ ' ብሎ የለጠፈዉ ማስታወቂያ እጅግ አሳዝኖናል " ብለዋል።
በተመደብንባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች መሄድ በማንችልበትና ሌሎችም በግል ኮሌጆች ከፍለን የመማሪያ ጊዜዉ ካለፈብን በኋላ የተወሰነዉ ይህ ዉሳኔ ከጊዜ እና ገንዘብ ጉልበት ብክነት ባሻገር በስነልቦናም ጉዳት አድርሶብናል ብለዋል።
ተማሪዎቹ ቅሬታቸዉን ለዩኒቨርሲቲዉና በግልባጭ ለትምህርት ሚንስቴርም ማቅረባቸውን ገልፀዉ የሚመለከተዉ አካል አስፈላጊውን መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌን አግኝቶ በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግሯል።
ዶክተር ቅሬታዉ እንደደረሳቸዉና ዩኒቨርሲቲዉ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገዉ ሁሉ " በሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለመስጠት ማስታወቂያ ማዉጣቱንና 400 የሚሆኑ ተማሪዎች ተመዝግበው ክፍያ ላጠናቀቁ ተማሪዎች ትምህርት የመጀመር ሂደት ላይ እያለን ትምህርት ሚንስቴር በሰጠዉ ትዕዛዝ መሰረት ማስተማር ስለማንችል ማስታወቂያ ለጥፈናል " ሲሉ ተናግረዋል።
ዩኒቨርቲዉ ለማስተማር ካለዉ ፍላጎት የተነሳ ተማሪዎችን መዝግቦ ወደ መማር ማስተማር ሂደት በመግባት ሂደት ላይ እንደነበር ያስታወሱት ፕሬዘረዳንቱ የተማሪዎችንና የወላጆችን ቅሬታ ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ትምህርት ሚንስቴር በማቅረብ ሂደት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።
" በሚንስትር መስሪያ ቤቱ ምላሽ ላይ ተመስርተን ' አስተምሩ ' የሚባል ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች የሚገኙ ከሆነ ለተማሪዎቹ ጥሪ እናቀርባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
ጉዳዩን ተከታትለን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
➡️ " ዉሳኔዉ የትምህርት ሚንስቴ እንጂ የዩኒቨርሲቲው አይደለም " - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
" የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ወራት ፊት በሣምንቱ የዕረፍት ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት የምዝገባ እና የመማሪያ ክፍያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ እያለን ዩኒቨርሲቲው ሌሎች አማራጮችን መጠቀሚያ ጊዜ ባለፈብን በዚህ ወቅት አላስተምራችሁም ብሎናል " ሲሉ ተማሪዎሽ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።
ቅሬታቸዉን ካደረሱን ተማሪዎች መካከል በመደበኛው የትምህርት ሚንስቴር ምደባ ጅግጅጋ ፣ሰላሌ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተመደብዉ እያለ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) በእረፍት ቀናት በክፍያ ለማስተማር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ከቤተሰብ ላለመራቅና በአንዳንድ አከባቢዎች ካለዉ የፀጥታ ችግር የተነሳ ከፍለዉ ለመማር በመወሰን የምዝገባና የትምህርት ክፍያ አጠናቀው የትምህርት መጀመርን ሲጠባበቁ እንደነበር ገልፀዉ ዩኒቨርሲቲዉ " ኃላፊነት በጎደለው መልኩ 'ትምህርት ሚንስቴር በግል ከፍሎ መማርን ስላልፈቀደ ማስተማር የማንችል በመሆኑ ክፍያችሁን መዉሰድ ትችላላችሁ ' ብሎ የለጠፈዉ ማስታወቂያ እጅግ አሳዝኖናል " ብለዋል።
በተመደብንባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች መሄድ በማንችልበትና ሌሎችም በግል ኮሌጆች ከፍለን የመማሪያ ጊዜዉ ካለፈብን በኋላ የተወሰነዉ ይህ ዉሳኔ ከጊዜ እና ገንዘብ ጉልበት ብክነት ባሻገር በስነልቦናም ጉዳት አድርሶብናል ብለዋል።
ተማሪዎቹ ቅሬታቸዉን ለዩኒቨርሲቲዉና በግልባጭ ለትምህርት ሚንስቴርም ማቅረባቸውን ገልፀዉ የሚመለከተዉ አካል አስፈላጊውን መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌን አግኝቶ በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግሯል።
ዶክተር ቅሬታዉ እንደደረሳቸዉና ዩኒቨርሲቲዉ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገዉ ሁሉ " በሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለመስጠት ማስታወቂያ ማዉጣቱንና 400 የሚሆኑ ተማሪዎች ተመዝግበው ክፍያ ላጠናቀቁ ተማሪዎች ትምህርት የመጀመር ሂደት ላይ እያለን ትምህርት ሚንስቴር በሰጠዉ ትዕዛዝ መሰረት ማስተማር ስለማንችል ማስታወቂያ ለጥፈናል " ሲሉ ተናግረዋል።
ዩኒቨርቲዉ ለማስተማር ካለዉ ፍላጎት የተነሳ ተማሪዎችን መዝግቦ ወደ መማር ማስተማር ሂደት በመግባት ሂደት ላይ እንደነበር ያስታወሱት ፕሬዘረዳንቱ የተማሪዎችንና የወላጆችን ቅሬታ ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ትምህርት ሚንስቴር በማቅረብ ሂደት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።
" በሚንስትር መስሪያ ቤቱ ምላሽ ላይ ተመስርተን ' አስተምሩ ' የሚባል ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች የሚገኙ ከሆነ ለተማሪዎቹ ጥሪ እናቀርባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
ጉዳዩን ተከታትለን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከውጭ የሚመጣ ተሟጋች አያስፈልገንም !! " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በሂጃብ ጉዳይ ምን አሉ ? " ከውጭ የሚመጣ ተሟጋች አያስፈልገንም። ጉዳዩ በራሳችን ነው የምንጨርሰው። ያለን አንድነት እና መፈቃቀር ሊነካ አይገባም። የአክሱም ህዝብም በዚህች ጉዳይ ላይ ተመሳሳይ አቋም እንዳለው ነው የማውቀው። አንዳንድ በክፋት የተሰማራ ካልሆነ፥ እያያችሁት…
" ታስረው ይቅረቡ " - ፍርድ ቤት
ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የቀረበውን ክስ ፍርድ ቤት ቀርበው መልስ እንዲሰጡ የተፃፈላቸውን ትእዛዝ " አንቀበልም " ያሉ አካላት ታስረው እንዲቀርቡ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት አዘዘ።
ፍርድ ቤቱ ጥር 19/2017 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ ፤ ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 4 ርእሰ መምህራን የአክሱም ከተማ ፓሊስ አስሮ እንዲያቀርባቸው ፍርድ ቤቱ አዟል።
ፍርድ ቤቱ ታስረው እንዲቀርቡ ትእዛዝ ያወጣባቸው የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ የአብርሃ ወ አፅብሃ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ የወርዒ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ የክንደያ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ርእሳነ መምህራን የካቲት 7/2017 ዓ.ም በአክሱም ከተማ ፓሊስ ተይዘው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ይህ በእንዲህ እያለ ከሂጃብ ክልከላ ተያይዞ በአክሱም በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተነሳው ውዝግብ ቀጥሏል።
አንዳንድ መረጃዎች አሁንም 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከሂጃብ ክልከላ ጋር በተያያዘ ከሚድ ፈተና ውጪ እንዲሆኑ መደረጋቸውን እያመላከቱ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ከፈተና መቅረት ልክ መሆኑ እና አለመሆኑ ለማጣራት ወደ ትምህርት ቤቶቹ ደውሎ ባገኘው መረጃ መሰረት " የቆየው የተማሪዎች የትምህርት ቤት የአለባበስ ደንብ በሚመለከተው አካል እስካልተቀየረ ድረስ ሂጃብ ለብሰው መግባት አይችሉም " ብለዋል።
@tikvahethiopia
ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ የቀረበውን ክስ ፍርድ ቤት ቀርበው መልስ እንዲሰጡ የተፃፈላቸውን ትእዛዝ " አንቀበልም " ያሉ አካላት ታስረው እንዲቀርቡ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት አዘዘ።
ፍርድ ቤቱ ጥር 19/2017 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ ፤ ከሂጃብ ክልከላ ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 4 ርእሰ መምህራን የአክሱም ከተማ ፓሊስ አስሮ እንዲያቀርባቸው ፍርድ ቤቱ አዟል።
ፍርድ ቤቱ ታስረው እንዲቀርቡ ትእዛዝ ያወጣባቸው የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ የአብርሃ ወ አፅብሃ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ የወርዒ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ የክንደያ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ርእሳነ መምህራን የካቲት 7/2017 ዓ.ም በአክሱም ከተማ ፓሊስ ተይዘው ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ይህ በእንዲህ እያለ ከሂጃብ ክልከላ ተያይዞ በአክሱም በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተነሳው ውዝግብ ቀጥሏል።
አንዳንድ መረጃዎች አሁንም 159 ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከሂጃብ ክልከላ ጋር በተያያዘ ከሚድ ፈተና ውጪ እንዲሆኑ መደረጋቸውን እያመላከቱ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ከፈተና መቅረት ልክ መሆኑ እና አለመሆኑ ለማጣራት ወደ ትምህርት ቤቶቹ ደውሎ ባገኘው መረጃ መሰረት " የቆየው የተማሪዎች የትምህርት ቤት የአለባበስ ደንብ በሚመለከተው አካል እስካልተቀየረ ድረስ ሂጃብ ለብሰው መግባት አይችሉም " ብለዋል።
@tikvahethiopia
" ' ብር (ጉቦ) ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ " - ቅሬታ አቅራቢዎች
በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ሳይት 3 የብሎክ 734 እና 735 ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገቡት የቆጣሪ እዳ ውዝግብ ምክንያት ሃይል ከተቋረጠባቸው 1 ወር ከ 5 ቀን መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጠቀሱት ብሎኮች ሃይል ያቋረጠው " በሦስት ቆጣሪዎች ያልተከፈለኝ ከ160 ሺ ብር በላይ እዳ አለ " በማለቱ ምክንያት ነው።
ቆጣሪዎቹ የተተከሉት ሳይቶቹ በግንባታ ላይ በነበሩበት ወቅት የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገባው ውል ሲሆን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት ደግሞ ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ውል በገባው እና ግንባታዎቹን ባከናወነው የስራ ተቋራጭ (ኮንትራክተር) ስም ነው።
" ይህ በሆነበት ሁኔታ ቆጣሪዎቹን ባልተረከብንበት እና ከእነዚህም ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለን ባልተጠቀምንበት ሁኔታ እዳውን ክፈሉ ተብለናል " ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተዋል።
" የመኖሪያ መንደሩ በግንባታ ላይ በነበረበት ወቅት የስራ ተቋራጩ (ኮንትራክተሩ) የተጠቀማቸው እና ግንባታቸው ተጠናቆ ከገባን በኋላም እንዲነሱ ባልተደረጉ ቆጣሪዎች ምክንያት የቆጣሪዎቹን የተጠራቀመ የክፍያ እዳ ክፈሉ ተብለናል ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆናችንም ምክንያት ላለፈው አንድ ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ ሃይል ታቋርጦብናል" ነው ያሉት።
በሁለቱ ብሎኮች ከ60 በላይ ነዋሪዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛኛዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ በሚገኙ የልማት ሥራዎች ምክንያት የተነሱ እና ከሁለት ዓመት እስከ ሁለት ወር ለሚሆን ጊዜ ገብተው መኖር የጀመሩ ናቸው።
ነዋሪዎቹ ቅሬታቸውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ያሳወቁ ሲሆን ጽ/ቤቶቹም ሃይል እንዲመለስላቸው የሚጠይቅ ደብዳቤ በተናጠል ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው እና በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ኢ/ር በላይ ሞቱማ ተፈርሞ በ07/05/17 ዓም የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ብሎኮቹን የገነባው ኮንትራክተር ቆጣሪዎቹን ከኮርፖሬሽኑ መረከቡን ከግንባታው በኋላም እነዚህን ቆጣሪዎች ከኮንትራክተሩ በመረከብ ለነዋሪዎች አለመተላለፉን እና አሁንም በኮንትራክተሩ የተመዘገበ መሆኑን ይገልጻል።
በዚህም ምክንያት ከቆጣሪው ጋር ተያይዞ የሚመጣ እዳ ሁሉ ኮንትራክተሩን እንጂ ነዋሪዎችን እንደማይመለከት በማስረዳት አስፈላጊውን ህጋዊ ድጋፍ ይደረግላቸው ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጠይቋል።
የለሚኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በበኩሉ በ 09/05/17 ዓም በጻፈው ደብዳቤ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የጻፈውን ደብዳቤ በመጥቀስ ለነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ እንዲደርግ እንገልጻለን ብሏል።
ሁለቱም ጽ/ቤቶች በተናጠል በጻፉት ደብዳቤ ሃይል የተቋረጠባቸው ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ቢጠይቁም አገልግሎቱ ሃይሉን ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ላለፉት አንድ ወር በላይ በጨለማ ለመቀመጥ መገደዳቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ነዋሪዎች በዝርዝር ባቀረቡት ቅሬታ ምን አሉ ?
" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጠራቀመውን እዳ ኮንትራክተሩን ፈልጋቹ አስከፍሉ ወይም የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እዳውን እንዲከፍል አድርጉ እያለን ነው እነሱ በተዋዋሉት እኛ የምንጠየቀው ለምንድነው ?
መንገድ ላይ ያሉ ቆጣሪዎች እንዲነሱ ማህበረሰቡ ከአመት በፊት ጀምሮ አቤቱታ እያቀረበ ነው ያለው አልተሰማንም ቆጣሪዎቹ ሃይል አልተቋረጠባቸውም፣ አላነሳቸውም እኛ ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል አልቀጠልንም።
በዚህም ምክንያት ተዋውለን ለብሎካችን ያስገባነውን ስሪ ፌዝ ቆጣሪ ሃይል አቋረጡብን ለምን ? ስንል የዛኛውን ቆጣሪ እዳ ካልከፈላቹ ተባልን ባልገባነው ውል ባልተጠቀምንበት ሃይል ክፈሉ ተብለን ለምን እንገደዳለን ? እዳው የተመዘገበው በኮንትራክተሩ ነው እኛ ለምንድነው የምንከፍለው።
ምግብ ለማብሰል እንጨት እና ከሰል ነው እየተጠቀምን ያለነው ተማሪዎች አሉ የሚመገቡትን ትተን ፈተና የሚፈተኑበት ጊዜ እንደመሆኑ ያጥኑ እንኳን ቢባል በምን ? ለተጨማሪ እና አላስፈላጊ ለሆነ ወጪ ነው የተዳረግነው።
ፊዩዝ በተደጋጋሚ እያመጡ እየነቀሉ እያዋጣን መክፈል ሥራ ሆነብን ሲበዛብን ከወር በፊት ሊነቅል የመጣውን ሰራተኛ ለማስቆም ሞከርን ለምን ታስቆሙታላቹ በሚል አጠፉብን በዚህ ምክንያት እየተበቀሉን ነው እስካሁን መብራት የለንም።
እያዋጣን ጉቦ መክፈል ሰልችቶናል ' ብር ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ ይሄንን እና ሌሎች ነገሮች ስላሳወቅንባቸው ሌሎች ተመሳሳይ የሆኑ ቆጣሪ ያለባቸው ሳይቶች ላይ እንደዚህ አይነት እርምጃ ሳይወሰድ እኛ ላይ የተደረገው ለብቀላ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፣የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እና የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በጉዳዩ ላይ የሰጡት ምላሽ በቀጣይ ይቀርባል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ በለሚኩራ ክፍለ ከተማ በቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ሳይት 3 የብሎክ 734 እና 735 ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገቡት የቆጣሪ እዳ ውዝግብ ምክንያት ሃይል ከተቋረጠባቸው 1 ወር ከ 5 ቀን መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጠቀሱት ብሎኮች ሃይል ያቋረጠው " በሦስት ቆጣሪዎች ያልተከፈለኝ ከ160 ሺ ብር በላይ እዳ አለ " በማለቱ ምክንያት ነው።
ቆጣሪዎቹ የተተከሉት ሳይቶቹ በግንባታ ላይ በነበሩበት ወቅት የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በገባው ውል ሲሆን ቆጣሪዎቹ የተመዘገቡት ደግሞ ከቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር ውል በገባው እና ግንባታዎቹን ባከናወነው የስራ ተቋራጭ (ኮንትራክተር) ስም ነው።
" ይህ በሆነበት ሁኔታ ቆጣሪዎቹን ባልተረከብንበት እና ከእነዚህም ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለን ባልተጠቀምንበት ሁኔታ እዳውን ክፈሉ ተብለናል " ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተዋል።
" የመኖሪያ መንደሩ በግንባታ ላይ በነበረበት ወቅት የስራ ተቋራጩ (ኮንትራክተሩ) የተጠቀማቸው እና ግንባታቸው ተጠናቆ ከገባን በኋላም እንዲነሱ ባልተደረጉ ቆጣሪዎች ምክንያት የቆጣሪዎቹን የተጠራቀመ የክፍያ እዳ ክፈሉ ተብለናል ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆናችንም ምክንያት ላለፈው አንድ ወር በላይ ለሚሆን ጊዜ ሃይል ታቋርጦብናል" ነው ያሉት።
በሁለቱ ብሎኮች ከ60 በላይ ነዋሪዎች የሚገኙ ሲሆን አብዛኛዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ በሚገኙ የልማት ሥራዎች ምክንያት የተነሱ እና ከሁለት ዓመት እስከ ሁለት ወር ለሚሆን ጊዜ ገብተው መኖር የጀመሩ ናቸው።
ነዋሪዎቹ ቅሬታቸውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ያሳወቁ ሲሆን ጽ/ቤቶቹም ሃይል እንዲመለስላቸው የሚጠይቅ ደብዳቤ በተናጠል ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው እና በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ ኢ/ር በላይ ሞቱማ ተፈርሞ በ07/05/17 ዓም የወጣው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ብሎኮቹን የገነባው ኮንትራክተር ቆጣሪዎቹን ከኮርፖሬሽኑ መረከቡን ከግንባታው በኋላም እነዚህን ቆጣሪዎች ከኮንትራክተሩ በመረከብ ለነዋሪዎች አለመተላለፉን እና አሁንም በኮንትራክተሩ የተመዘገበ መሆኑን ይገልጻል።
በዚህም ምክንያት ከቆጣሪው ጋር ተያይዞ የሚመጣ እዳ ሁሉ ኮንትራክተሩን እንጂ ነዋሪዎችን እንደማይመለከት በማስረዳት አስፈላጊውን ህጋዊ ድጋፍ ይደረግላቸው ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጠይቋል።
የለሚኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በበኩሉ በ 09/05/17 ዓም በጻፈው ደብዳቤ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የጻፈውን ደብዳቤ በመጥቀስ ለነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ እንዲደርግ እንገልጻለን ብሏል።
ሁለቱም ጽ/ቤቶች በተናጠል በጻፉት ደብዳቤ ሃይል የተቋረጠባቸው ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ቢጠይቁም አገልግሎቱ ሃይሉን ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ላለፉት አንድ ወር በላይ በጨለማ ለመቀመጥ መገደዳቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ነዋሪዎች በዝርዝር ባቀረቡት ቅሬታ ምን አሉ ?
" የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጠራቀመውን እዳ ኮንትራክተሩን ፈልጋቹ አስከፍሉ ወይም የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እዳውን እንዲከፍል አድርጉ እያለን ነው እነሱ በተዋዋሉት እኛ የምንጠየቀው ለምንድነው ?
መንገድ ላይ ያሉ ቆጣሪዎች እንዲነሱ ማህበረሰቡ ከአመት በፊት ጀምሮ አቤቱታ እያቀረበ ነው ያለው አልተሰማንም ቆጣሪዎቹ ሃይል አልተቋረጠባቸውም፣ አላነሳቸውም እኛ ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል አልቀጠልንም።
በዚህም ምክንያት ተዋውለን ለብሎካችን ያስገባነውን ስሪ ፌዝ ቆጣሪ ሃይል አቋረጡብን ለምን ? ስንል የዛኛውን ቆጣሪ እዳ ካልከፈላቹ ተባልን ባልገባነው ውል ባልተጠቀምንበት ሃይል ክፈሉ ተብለን ለምን እንገደዳለን ? እዳው የተመዘገበው በኮንትራክተሩ ነው እኛ ለምንድነው የምንከፍለው።
ምግብ ለማብሰል እንጨት እና ከሰል ነው እየተጠቀምን ያለነው ተማሪዎች አሉ የሚመገቡትን ትተን ፈተና የሚፈተኑበት ጊዜ እንደመሆኑ ያጥኑ እንኳን ቢባል በምን ? ለተጨማሪ እና አላስፈላጊ ለሆነ ወጪ ነው የተዳረግነው።
ፊዩዝ በተደጋጋሚ እያመጡ እየነቀሉ እያዋጣን መክፈል ሥራ ሆነብን ሲበዛብን ከወር በፊት ሊነቅል የመጣውን ሰራተኛ ለማስቆም ሞከርን ለምን ታስቆሙታላቹ በሚል አጠፉብን በዚህ ምክንያት እየተበቀሉን ነው እስካሁን መብራት የለንም።
እያዋጣን ጉቦ መክፈል ሰልችቶናል ' ብር ክፈሉና እንቀጥልላቹ ' ያለን የቴክኒክ ክፍል ሰራተኛ አለ ይሄንን እና ሌሎች ነገሮች ስላሳወቅንባቸው ሌሎች ተመሳሳይ የሆኑ ቆጣሪ ያለባቸው ሳይቶች ላይ እንደዚህ አይነት እርምጃ ሳይወሰድ እኛ ላይ የተደረገው ለብቀላ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፣የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን እና የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በጉዳዩ ላይ የሰጡት ምላሽ በቀጣይ ይቀርባል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ብልህ ለራሱ ያውቃል ... በአቢሲንያ ሞባይል ባንኪንግ ህይወትን ቀለል አድርጎ ይመራል።#Banking #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
“ 763 ሠራተኞች ከ2013 ዓ/ም እስካሁን ደመወዝ አልተከፈላቸውም። ሌላ ቦታ እንዳይቀጠሩም የስንብት ደብዳቤ የለም ” - ጽሕፈቱ ቤቱ ስለቀድሞ ሰሜን ዕዝ ሲቪል ሰርቫንቶች
ከ760 በላይ የቀድሞ ሰሜን ዕዝ ሠራተኞች ከ4 ዓመት በላይ ደመወዝ ስላልተከፈላቸው ከነቤተሰቦቻቸው በከፋ ችግር መሆናቸውን በኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የምን ያህል ጊዜ ደመወዝ ነው ያልተፈጸመላቸው? ስንል የጠየቅናቸው የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ፀሐዬ እምባዬ፣ “763 ሠራተኞች ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ እስካሁን ደመወዝ አልተከፈላቸውም። ሌላ ቦታ እንዳይቀጠሩም የስንብት ደብዳቤ የለም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“በሌላ መስሪያ ለመቀጠርምኮ የአገልግሎት ድጋፍ ያስጋል። ይህን የፃፈላቸው አካልም የለም። ዝም ብለው በባዶ እናንተ ‘ስላላመለከታችሁ ተሰናብታችኋል’ የሚል ነው” ነው ያሉት።
“ ይህ እንደ ዜጋ አግባብነት የለውም። ከ20 ዓመት በላይ የሰሩ ናቸው የመከላከያ ሰሜን ዕዝ ሲቪል ሰርቫንት ሆነው ” በማለት ሁነቱን አስረድተዋል።
“ ከሠራተኞቹ ወጣት የሚበል የለም ማለት ይቻላል” ብለው፣ “ ከነቤተሰቦቻቸው ችግር ላይ ናቸው የሚመለከተው አካል መፍትሄ ይስጥ ” ሲሉም አሳስበዋል።
ኃላፊው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
“ ከጦርነቱ በኋላ ሰሜን ዕዝ ከፈረሰ በኋላ ሰሜን ዕዝ ሲቪል ሰርቫንት በሥራ ላይ አልነበሩም እንደማንኛውም ሲቪል ሰርቫንት ሰራተኛ። ከፕሪቶራያው በኋላም ስምምነት ማንም ሰው ሊመለከታቸው አልቻለም።
ወደ ዋና መስሪያም ቤት ደብዳቤ ልከናል። መከላከያ ሚኒስቴርም ተጠይቋል። እነርሱ ግን ‘ነገሩ ከተስተካከለ በኋላ ተመለሱና ረፖርት አድርጉ ብለን አሳውቀናል’ይላሉ።
ግን በዚህ ጉዳይ የተፃፈ ደብዳቤም፣ የደረሳቸው ነገርም የለም። 2016 ዓ/ም እንደደረሳቸው ወዲያውኑ መጥተው ወደኛ አመለከቱ። ግን ሪፓርት ያደረጉትን ተቀብለናቸዋል፤ ያላደረጉ እንደሰናበቱ ይቆጠራል’ ብለው ነው የፃፉላቸው።
የሚከታተል ሰው ካለ መጥቶ ያለና የሌለ፣ የሚገባውና የማይገባውን መለየት እንጂ የዓመታት ደመወዝ የሌላቸውን ሠራተኞች ‘ወደ አዲስ አበባ ተጉዛችሁ ሪፓርት አድርጉ’ ማለት አግባብ አይደለም።
ሊሄዱ የፈጉም ነበሩ ግን የሦስትና አራት ዓመታት የቤት ኪራይ እዳ አለባቸው። እዳቸውን ሳይከፍሉ የሚለቃቸው የለም። ይህን ለማድረግ ንብረታቸውን ለአከራይ ማስረከብ አለባቸው።
እንዳይሄዱ መሳፈሪያ ገንዘብ የላቸውም። መካላከያም ‘ካልመጣችሁ አይሆንም ነው ያለውያና መንግስት እያሰራቸው በነበረው ቦታ ሰው ልኮ ቁጥጥር አድርጎ የሚገባውና የማይገባው ማጣራት አለበት ” ብለዋል።
“ ሲቪል ሰርቫንቱ መፍትሄ እየጠበቀ ነው ያለው። መፍትሄ ሊልጣቸው ይገባል። በወረቀት መወራወር ከሆነ ግን ጥሩ አይደለም ለቀጣይም ዜጋ ” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
(የሚመለከታቸው አካላት ለዚህ ቅሬታ ምላሽ እንደሰጡ የምናቀርብ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከ760 በላይ የቀድሞ ሰሜን ዕዝ ሠራተኞች ከ4 ዓመት በላይ ደመወዝ ስላልተከፈላቸው ከነቤተሰቦቻቸው በከፋ ችግር መሆናቸውን በኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የምን ያህል ጊዜ ደመወዝ ነው ያልተፈጸመላቸው? ስንል የጠየቅናቸው የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ፀሐዬ እምባዬ፣ “763 ሠራተኞች ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ እስካሁን ደመወዝ አልተከፈላቸውም። ሌላ ቦታ እንዳይቀጠሩም የስንብት ደብዳቤ የለም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“በሌላ መስሪያ ለመቀጠርምኮ የአገልግሎት ድጋፍ ያስጋል። ይህን የፃፈላቸው አካልም የለም። ዝም ብለው በባዶ እናንተ ‘ስላላመለከታችሁ ተሰናብታችኋል’ የሚል ነው” ነው ያሉት።
“ ይህ እንደ ዜጋ አግባብነት የለውም። ከ20 ዓመት በላይ የሰሩ ናቸው የመከላከያ ሰሜን ዕዝ ሲቪል ሰርቫንት ሆነው ” በማለት ሁነቱን አስረድተዋል።
“ ከሠራተኞቹ ወጣት የሚበል የለም ማለት ይቻላል” ብለው፣ “ ከነቤተሰቦቻቸው ችግር ላይ ናቸው የሚመለከተው አካል መፍትሄ ይስጥ ” ሲሉም አሳስበዋል።
ኃላፊው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
“ ከጦርነቱ በኋላ ሰሜን ዕዝ ከፈረሰ በኋላ ሰሜን ዕዝ ሲቪል ሰርቫንት በሥራ ላይ አልነበሩም እንደማንኛውም ሲቪል ሰርቫንት ሰራተኛ። ከፕሪቶራያው በኋላም ስምምነት ማንም ሰው ሊመለከታቸው አልቻለም።
ወደ ዋና መስሪያም ቤት ደብዳቤ ልከናል። መከላከያ ሚኒስቴርም ተጠይቋል። እነርሱ ግን ‘ነገሩ ከተስተካከለ በኋላ ተመለሱና ረፖርት አድርጉ ብለን አሳውቀናል’ይላሉ።
ግን በዚህ ጉዳይ የተፃፈ ደብዳቤም፣ የደረሳቸው ነገርም የለም። 2016 ዓ/ም እንደደረሳቸው ወዲያውኑ መጥተው ወደኛ አመለከቱ። ግን ሪፓርት ያደረጉትን ተቀብለናቸዋል፤ ያላደረጉ እንደሰናበቱ ይቆጠራል’ ብለው ነው የፃፉላቸው።
የሚከታተል ሰው ካለ መጥቶ ያለና የሌለ፣ የሚገባውና የማይገባውን መለየት እንጂ የዓመታት ደመወዝ የሌላቸውን ሠራተኞች ‘ወደ አዲስ አበባ ተጉዛችሁ ሪፓርት አድርጉ’ ማለት አግባብ አይደለም።
ሊሄዱ የፈጉም ነበሩ ግን የሦስትና አራት ዓመታት የቤት ኪራይ እዳ አለባቸው። እዳቸውን ሳይከፍሉ የሚለቃቸው የለም። ይህን ለማድረግ ንብረታቸውን ለአከራይ ማስረከብ አለባቸው።
እንዳይሄዱ መሳፈሪያ ገንዘብ የላቸውም። መካላከያም ‘ካልመጣችሁ አይሆንም ነው ያለውያና መንግስት እያሰራቸው በነበረው ቦታ ሰው ልኮ ቁጥጥር አድርጎ የሚገባውና የማይገባው ማጣራት አለበት ” ብለዋል።
“ ሲቪል ሰርቫንቱ መፍትሄ እየጠበቀ ነው ያለው። መፍትሄ ሊልጣቸው ይገባል። በወረቀት መወራወር ከሆነ ግን ጥሩ አይደለም ለቀጣይም ዜጋ ” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
(የሚመለከታቸው አካላት ለዚህ ቅሬታ ምላሽ እንደሰጡ የምናቀርብ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ካናዳ ለውጭ ዜጎች ስትሰጠው በነበረው የትምህርት እድል ፍቃድ ላይ ገደብ ጥላለች።
ውሳኔው ከተለያዩ የውጭ ሀገራት ወደ ካናዳ የሚገቡ ዜጎች ቁጥር እጅግ መጨመሩን ተከትሎ የተፈጠሩ ክፍተቶችን ለማስተካከል ያለመ ነው ሲል የካናዳ የስደተኞች፣ ዜግነት ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በካናዳ የውጭ ሀገር ዜጎች ቁጥር መጨመር በሀገሪቱ የመኖሪያ ቤት እጥረት እንድያጋጥም እና የጤና አጠባበቅ ስርዓቱ ተመጣጣኝ እንዳይሆን አድርጎታል።
በ2025 በካናዳ የትምህርት እድል የሚያገኙ የውጭ ዜጎች ባለፈው አመት እድሉን ካገኙት ጋር ሲነጻጸር 10 በመቶ ያነሰ ነው ተብሏል፡፡ #legit
Via @ThiqahEth
ውሳኔው ከተለያዩ የውጭ ሀገራት ወደ ካናዳ የሚገቡ ዜጎች ቁጥር እጅግ መጨመሩን ተከትሎ የተፈጠሩ ክፍተቶችን ለማስተካከል ያለመ ነው ሲል የካናዳ የስደተኞች፣ ዜግነት ጉዳዮች ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በካናዳ የውጭ ሀገር ዜጎች ቁጥር መጨመር በሀገሪቱ የመኖሪያ ቤት እጥረት እንድያጋጥም እና የጤና አጠባበቅ ስርዓቱ ተመጣጣኝ እንዳይሆን አድርጎታል።
በ2025 በካናዳ የትምህርት እድል የሚያገኙ የውጭ ዜጎች ባለፈው አመት እድሉን ካገኙት ጋር ሲነጻጸር 10 በመቶ ያነሰ ነው ተብሏል፡፡ #legit
Via @ThiqahEth
#ለጥንቃቄ
(በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀረበ)
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ምንድነው ?
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ስልካችን ላይ ከማህበራዊ ትስስር ድረ-ገፆች በምንጭናቸው መተግበሪያዎች አማካኝነት ወደ ስልካችን ሰርጎ የሚገባ ሲሆን እንደ ቴሌግራም፣ ዋትስአፕ፣ የመሳሰሉ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በስፋት እየተሰራጨ ጥቃትን የሚሰነዝር #መተግበሪያ ነው፡፡
ጉዳቱ ምንድነው ?
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመረጃ ሥርዓት ደህንነት ክፍል ፋርማ ፕላስ (Pharma+) የተሰኘውን መተግበሪያ ጉዳት አምጪ እንደሆነ ገልጿል።
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ከማህበራዊ ትስስር ገጾች አውርደን በምንጭናቸው ሌሎች መተግበሪያዎች ጋር በመለጠፍ ወደ ስልካችን ሰርጎ በመግባት ፦
- የስልካችንን ስክሪን ማየት፤
- አጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን ማንበብ፣
- ሀሰተኛ የመግቢያ ገጾቸን በማዘጋጀት
- የይለፍ ቃሎችን መመንተፍ እና የመሳሰሉ የግል መረጃዎችን የሚሰርቅ መተግበሪያ ነው፡፡
የፋይናንሻል ግብይቶችን ከተጠቂው እውቅና ውጪ መፈፅሙ እና ስልካችን ላይ ተጭነው ካሉት መተግበሪያዎች ውስጥ መደበቁ ማየት ስለማንችል ለመከላከል በጣም አዳጋች ነው።
እንዴት ራሳችንን ከፋርማ ፕላስ (Pharma+) እንጠብቅ ?
➡️ ካልታመኑ ምጮቾች ማንኛውንም መተግበሪያ ስልኮት ላይ አይጫኑ፤
➡️ በማህበራው ገጽ አማካኝነት የሚላክሎትን ማንኛውንም ማስፈንጠሪያ ወይም መተግበሪያ ምንነቱን ሳያረጋግጡ አይክፈቱ፤
➡️ ብቅ ባይ (Pop up) ማስታወቂያዎችን ወይም አጠራጣሪ ገጾችን በፍጹም አይክፈቱ፤
➡️ እንደ ጎግል ፕሌይ፣ አማዞን፣ አፕስቶር ወይም ሳምሰንግጋላክሲ ስቶር ጥብቅ የደህንነት ፍተሻዎችን የሚያደርጉ ይፋዊ የመተግበሪያ ማከማቻዎችን ብቻ ይጠቀሙ።
ትክክለኛ የስልክ መተግበሪያዎችን በመጠቀም እራስዎትን ይጠብቁ።
(የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
@tikvahethiopia
(በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቀረበ)
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ምንድነው ?
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ስልካችን ላይ ከማህበራዊ ትስስር ድረ-ገፆች በምንጭናቸው መተግበሪያዎች አማካኝነት ወደ ስልካችን ሰርጎ የሚገባ ሲሆን እንደ ቴሌግራም፣ ዋትስአፕ፣ የመሳሰሉ ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በስፋት እየተሰራጨ ጥቃትን የሚሰነዝር #መተግበሪያ ነው፡፡
ጉዳቱ ምንድነው ?
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመረጃ ሥርዓት ደህንነት ክፍል ፋርማ ፕላስ (Pharma+) የተሰኘውን መተግበሪያ ጉዳት አምጪ እንደሆነ ገልጿል።
ፋርማ ፕላስ (Pharma+) ከማህበራዊ ትስስር ገጾች አውርደን በምንጭናቸው ሌሎች መተግበሪያዎች ጋር በመለጠፍ ወደ ስልካችን ሰርጎ በመግባት ፦
- የስልካችንን ስክሪን ማየት፤
- አጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን ማንበብ፣
- ሀሰተኛ የመግቢያ ገጾቸን በማዘጋጀት
- የይለፍ ቃሎችን መመንተፍ እና የመሳሰሉ የግል መረጃዎችን የሚሰርቅ መተግበሪያ ነው፡፡
የፋይናንሻል ግብይቶችን ከተጠቂው እውቅና ውጪ መፈፅሙ እና ስልካችን ላይ ተጭነው ካሉት መተግበሪያዎች ውስጥ መደበቁ ማየት ስለማንችል ለመከላከል በጣም አዳጋች ነው።
እንዴት ራሳችንን ከፋርማ ፕላስ (Pharma+) እንጠብቅ ?
➡️ ካልታመኑ ምጮቾች ማንኛውንም መተግበሪያ ስልኮት ላይ አይጫኑ፤
➡️ በማህበራው ገጽ አማካኝነት የሚላክሎትን ማንኛውንም ማስፈንጠሪያ ወይም መተግበሪያ ምንነቱን ሳያረጋግጡ አይክፈቱ፤
➡️ ብቅ ባይ (Pop up) ማስታወቂያዎችን ወይም አጠራጣሪ ገጾችን በፍጹም አይክፈቱ፤
➡️ እንደ ጎግል ፕሌይ፣ አማዞን፣ አፕስቶር ወይም ሳምሰንግጋላክሲ ስቶር ጥብቅ የደህንነት ፍተሻዎችን የሚያደርጉ ይፋዊ የመተግበሪያ ማከማቻዎችን ብቻ ይጠቀሙ።
ትክክለኛ የስልክ መተግበሪያዎችን በመጠቀም እራስዎትን ይጠብቁ።
(የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
🪄 ዳታው በርክቷል! ወርሃዊ የዳታ ጥቅሎችን እየገዛን እስከ 25% የበለጠ ዳታ አግኝተን በየሄድንበት በፈጣኑ ኢንተርኔት ፈታ እንበል! 🥳
M-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው!
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በአስተማማኙ ኔትወርክ ዳታ እንንበሽበሽ!
#MPESASafaricom
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
🪄 ዳታው በርክቷል! ወርሃዊ የዳታ ጥቅሎችን እየገዛን እስከ 25% የበለጠ ዳታ አግኝተን በየሄድንበት በፈጣኑ ኢንተርኔት ፈታ እንበል! 🥳
M-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው!
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በአስተማማኙ ኔትወርክ ዳታ እንንበሽበሽ!
#MPESASafaricom
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
ዋሪት !
እስከ ጥር 23 ቀን 2017 የሚቆየው የዋሪት ፈርኒቸር ቅናሽ ሊጠናቀቅ 3ቀናት ብቻ ቀርተውታል።
እንዳያመልጥዎ ! አሁኑኑ ይጎብኙን!
*ወሎ ሰፈር- ከጋራ ሙለታ ህንጻ ጎን
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
* ፒያሳ- ፍርዱ ኮሜርሻል
ለተጨማሪ መረጃ: ☎️ 0911210706 / 07
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ !
እስከ ጥር 23 ቀን 2017 የሚቆየው የዋሪት ፈርኒቸር ቅናሽ ሊጠናቀቅ 3ቀናት ብቻ ቀርተውታል።
እንዳያመልጥዎ ! አሁኑኑ ይጎብኙን!
*ወሎ ሰፈር- ከጋራ ሙለታ ህንጻ ጎን
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
* ፒያሳ- ፍርዱ ኮሜርሻል
ለተጨማሪ መረጃ: ☎️ 0911210706 / 07
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ !
#ለጥንቃቄ
" የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው ወንጀሎችን የሚፈፅሙ ስላሉ ተጠንቀቁ " - ፖሊስ
በተለያዩ ቦታዎች በመንቀሳቀስና የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው በተለምዶው " ሿሿ " የተባለውን ወንጀል ፈፅመዋል የተባሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ተጠርጣሪዎቹ ብዛታቸው 4 ሲሆን የወንጀል ድርጊቱን ፈፅመዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አካባቢ ነው።
የግል ተበዳይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቄራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ሄደው የጤና ምርመራ ለማድረግ ዘነበወርቅ አደባባይ ትራንስፖርት እየጠበቁ ነበር።
ግለሰቦቹም በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 B-13788 አ.አ በሆነ የቤት መኪና የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለውና የግል ተበዳይን ተሽከርካሪው ውስጥ ያገቧቸዋል።
በኃላም " ቄራ ድረስ ከምትሄጂ እዚሁ ቅርብ ቦታ የጤና ምርመራ ማድረግ ትችያለሽ እናሳይሻለን " በማለት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ታቦት ማደሪያ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሲደርሱ ቅያስ ውስጥ ይገባሉ።
እዛም በማስገባት በእጅ ቦርሳ ውስጥ የነበረ 7,900 ጥሬ ገንዘብ ይዘው ለመሰወር ሙከራ ሲያደርጉ በአየር ጤና አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ግለሰቦቹ ወንጀሉን ፈፅመው በተሽከርካሪ ለማምለጥ በሚሞክሩበት ሰዓትም አንድ ግለሰብ ላይ አደጋ ማድረሳቸው ተጠቁሟል።
ከተያዙት 4 ተጠርጣሪዎች ውስጥ አንዷ ሴት ስትሆን አስፈላጊው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
ግለሰቦቹ ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ ወንጀል በጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ፓስተር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደነበርና ደጋጋሚ ወንጀል ፈፃሚዎች መሆናቸውን ጅምር የምርመራ መዝገቡ ያመለክታል ተብሏል።
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለውና የተለያዩ ማታለያ ዘዴዎችን በመጠቀም ወንጀሎችን የሚፈፅሙ ግለሰቦችን በህግ ለማስቀጣት ህብረተሰቡ የራሱን ጥንቃቄ እንዲያደርግና ጥቆማ በመስጠት የተለመደውን ትብብር እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
" የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው ወንጀሎችን የሚፈፅሙ ስላሉ ተጠንቀቁ " - ፖሊስ
በተለያዩ ቦታዎች በመንቀሳቀስና የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለው በተለምዶው " ሿሿ " የተባለውን ወንጀል ፈፅመዋል የተባሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ተጠርጣሪዎቹ ብዛታቸው 4 ሲሆን የወንጀል ድርጊቱን ፈፅመዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አካባቢ ነው።
የግል ተበዳይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቄራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ሄደው የጤና ምርመራ ለማድረግ ዘነበወርቅ አደባባይ ትራንስፖርት እየጠበቁ ነበር።
ግለሰቦቹም በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 B-13788 አ.አ በሆነ የቤት መኪና የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለውና የግል ተበዳይን ተሽከርካሪው ውስጥ ያገቧቸዋል።
በኃላም " ቄራ ድረስ ከምትሄጂ እዚሁ ቅርብ ቦታ የጤና ምርመራ ማድረግ ትችያለሽ እናሳይሻለን " በማለት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ታቦት ማደሪያ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሲደርሱ ቅያስ ውስጥ ይገባሉ።
እዛም በማስገባት በእጅ ቦርሳ ውስጥ የነበረ 7,900 ጥሬ ገንዘብ ይዘው ለመሰወር ሙከራ ሲያደርጉ በአየር ጤና አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ግለሰቦቹ ወንጀሉን ፈፅመው በተሽከርካሪ ለማምለጥ በሚሞክሩበት ሰዓትም አንድ ግለሰብ ላይ አደጋ ማድረሳቸው ተጠቁሟል።
ከተያዙት 4 ተጠርጣሪዎች ውስጥ አንዷ ሴት ስትሆን አስፈላጊው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
ግለሰቦቹ ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ ወንጀል በጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ፓስተር አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደነበርና ደጋጋሚ ወንጀል ፈፃሚዎች መሆናቸውን ጅምር የምርመራ መዝገቡ ያመለክታል ተብሏል።
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ መስለውና የተለያዩ ማታለያ ዘዴዎችን በመጠቀም ወንጀሎችን የሚፈፅሙ ግለሰቦችን በህግ ለማስቀጣት ህብረተሰቡ የራሱን ጥንቃቄ እንዲያደርግና ጥቆማ በመስጠት የተለመደውን ትብብር እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia