ኢትዮጵያ ከፍተኛ የወጣቶች ቁጥር ያለባት ሀገር ናት።
ካለው ከፍተኛ የወጣቶች ቁጥር አንጻር ያለው የስራ እድል አነስተኛ ነው። የስራ እድል ቢገኝ እንኳን የሚከፈለው ክፍያ ዝቅተኛ በሆኑ ህይወትን መቀየር እና ያሰቡትን ማሳካት ፈተና ነው።
በዚህ ምክንያት ብዙ ወጣቶች የተሻለ ኑሮና ገቢ ፍለጋ ከሀገር ለመውጣት ይፈልጋሉ።
ወጣቶቹ ያደጉ ሀገራት / በኢኮኖሚ የተሻሉ ሀገራት ሄደው ሰርተው ፣ ጥሩ ገቢ አግኝተው ለራሳቸው ተርፈው ፤ ዋጋ ለከፈለላቸውና ተቸግሮ ላሳደጋቸው ቤተሰባቸው እንዲሁም ለህብረተሰባቸው መድረስ እና ' አለሁላችሁ ' ማለት ይፈልጋሉ።
እድሜ ቆሞ አይጠብቅምና ፈጣሪ በሰጣቸው የወጣትነት ጊዜ ጉልበትና እውቀታቸውን ተጠቅመው ቢያንስ እነሱ ባይደላቸው ለልጆቻቸው የሚሆን ነገር ማስቀረት ትልቁ ምኞታቸው ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወጣቱ ዘንድ ከሀገር ወጥቶ ለመስራት የሚታየው ፍላጎት እጅግ በጣም መጨመሩን በተለያየ መንገድ ለመገንዘብ ችሏል።
በተለይ ወደ ካናዳ፣ ጣልያን፣ አሜሪካ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሳዑዲ፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ሮማኒያ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ... ሌሎችም የውጭ ሀገራት በትምህርት እና በስራ ለመሄድ ፕሮሰስ የሚያደርጉ በርካታ ወጣቶችን ማነጋገር ችለናል። ሀሳባቸውንም ተቀብለናል።
አንድ ካናዳ ለመሄድ በዝግጅት ላይ ያለ ወጣት ፥ " እኔ ከዩኒቨርሲቲ በትልቅ ውጤት ከተመረቅኩ አንስቶ ባለፉት 3 ዓመታት ያልሞከርኩት የስራ ሙከራ የለም ባለሁበት አካባቢ አጠቃላይ የቅጥር ሁኔታ ተስፋ አስቆራጭ ሆኖብኝ በግሌ ለመንቀሳቀስ ሞክሬ አይደለም ህይወቴን ላሻሻል ዳግም የቤተሰብ እጅ ጠባቂ ሆኛለሁ " ሲል ገልጿል።
" በዚህም ምክንያት ከሰዎች ብር አፈላልጌ ወደ ውጭ ሀገር በመሄድ ያለውን ነገር ሁሉ ለመስራት እየጣርኩኝ ነው " ብሏል።
ሌላኛዋ ወጣት በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ስትሆን " በተግባር የስራ እድል ማግኘት አስቸጋሪ እየሆነ ነው ፤ የሚሰራው በትውውቅ በብሄር እና በዝምድና ነው እንዴት ይሄንን ማለፍ እንዳለበኝ አላውቅም " ብላለች።
ለበርካታ ወራት እዚሁ ሀገር ውስጥ ሆኖ ሰርቶ ለመቀየር በሚል ብዙ ሙከራ ብታደርግም ስላልተሳካ የውጭ ሀገር እድል እየሞከረች እንደሆነ አመልክታለች።
ሌላኛው ቃሉን የሰጠ ክሩቤል የተባለ ወጣት ፥ ምንም እንኳን በስራ ላይ በሚገኝም በወር የሚያገኘው ገቢ አነስተኛ በመሆኑ በአጭር ጊዜ ትዳር ይዞ፣ የራሱን ሃሳብ አሳክቶ፣ ለቤተሰብ ፣ ለወገን ተርፎ መኖር የማይታሰብ ስለሆነበት ውጭ ሀገር ሰርቶ የመመለስ ፍላጎት እንዳለውና ይህን ለማድረግ እየሞከረ እንደሆነ ጠቁሟል።
ሌሎች ያናገርናቸው ወጣቶችም ባለው የኢኮኖሚ ሁኔታ ፣ ስራም ለማግኘት የሚያደርጉት ጥረት ተስፋ ስላስቆረጣቸው ውጭ ሀገር ለመሄድና ማንኛውም ስራ ለመስራት ሲሉ እድላቸውን እየሞከሩ እንደሆነ ተናግረዋል።
" ማንኛውም ሰው ሀገሩን ጥሎ የሚወጣው ሀገሩን ጠልቶ ሳይሆን የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ነው " የሚሉት ወጣቶቹ በዚህ እድሜ ካልሰራን መቼ ልንሰራ ነው ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ቃላቸውን የሰጡት ወጣቶች ፦
- በሀገር ውስጥ ያለው የስራ እድል እንዲሰፋ ፣
- በትውውቅ፣ በብሄር፣ በዝምድና የሚፈጸም ቅጥር እንዲቆም
- በገንዝብ የሚፈጸም ቅጥር እንዲቀር ካልተደረገ ወጣቱ እዚህ ሰርቶ የመለውጥ ተስፋው እንደሚሞት አስገንዝበዋል።
ሌላው " በሙስና የሚዘረፈው ብር ብዙ ነው እሱን ተከላክሎ ለወጣቶች አንዳች ነገር እንኳ ማድረግ ይቻላል ፤ ግን ዘራፊው የበለጠ ሃብቱን እያካበተ ወጣቱ የበለጠ ተስፋ እየቆረጠ ነው " ብለዋል።
አሁን ላይ በየመስኩ ሙስና መንሰራፋቱን ስራ ለመቀጠር፣ ጉዳይ ለመጨረስ እጅ መንሻ ካልተሰጠ እንደማይሆን በተግባር እንደተመለከቱ ጠቁመው ይሄ እያደር መዘዙ የከፋ ይሆናል ሲሉ አሳስበዋል።
" በሙስና በየአመቱ የሚዘረፈው የዚህች ሀገር ሃብት ለስንት ወጣቶች ህወይት መቀየሪያ ይበቃ ነበር ? " ሲሉም ጠይቀዋል።
ወጣቶች በሀገራቸው ላይ ሰርተው እንዲቀየሩ ምቹ ሁኔታ ከሌለ፣ እድሎችና ለስራ ለፈጠራ የሚሆን ሀቀኛ መደላደሎች ካልተፈጠሩ በሀገር ሰርቶ መቀየር አስቸጋሪ ስለሚሆን ሊታሰብበት ይገባል ብለዋል።
" ፖለቲከኞችም ሆኑ ለሀገር እናስባለን ተፅእኖ ፈጣሪ ነን የሚሉ ሰዎችም የወጣቶችን የኢኮኖሚ ጉዳይ አጀንዳ ሊያደርጉ ይገባል ዘውትር እነሱን የሚጠቅም ነገር ካልሆነ የመናገር እና ተፅእኖ የመፍጠር ፍላጎት የላቸውም " ሲሉ ተችተዋል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ አ/አ)
#ቲክቫህኢትዮጵያ #የወጣቶችድምጽ
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ዴሞክራሲ 👏 #ሶማሌላንድ
" የምርጫ ውጤቱን እንቀበላለን " - ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ
ባለፈው ሳምንት በራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ መደረጉ ይታወሳል።
በከፍተኛ ብልጫም የተቃዋሚው ዋደኒ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ " ኢሮ " ምርጫውን አሸንፈዋል።
በምርጫው የተሸነፉት ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ " የምርጫውን ውጤት እንቀበላለን " ብለዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንትንም " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።
" ባስመዘገቡት ድል እንኳን ደስ አልዎት " ያሉት ፕሬዜዳንት ቢሂ " ሰላማዊና የተረጋጋ የስልጣን ሽግግር እንዲደረግ ለማድረግ የተሟላ ድጋፌን አደጋለሁ " ሲሉ ቃል ገብተዋል።
" የአገልግሎት ዘመንዎ ሰላምን ፣ እድገትን እና ዘላቂ ስኬትን ለሀገራችን እንዲያመጣ እመኛለሁ " ብለዋል።
ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ቢሂ ለህዝቡ ባስተላለፉት መልዕክት " ፕሬዝዳንታችሁ ሆኜ እንዳገለግላችሁ ዕድሉን ስለሰጣችሁኝ አመሰግናለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
" የስልጣን ዘመኔ ማብቂያ ላይ ሆኜ የምለው ነገር ለሀገራችን እድገት ያለኝ ቁርጠኝነት ጸኑ መሆኑን ነው " ሲሉ አክለዋል።
" በአንድነት እና በጋራ ተነስተን ለሶማሌላንድ ብልፅግና እንስራ " ብለዋል።
6ኛው የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት አብዲራህማን ኢሮ " ማንም ተሸናፊ ማንም አሸናፊ የለም ያሸነፈው የሶማሌላንድ ህዝብ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ሶማሌላንድ እራሷን እንደ ሉዓላዊ ሀገር ምትቆጥር ናት። ከሶማሊያ መንግሥት ጋርም ግንኙነት የላትም። ላለፉት በርካታ ዓመታት ራሷን በራሷ እያስተዳደረች ነው።
እጅግ ሰለማዊ ፣ የተረጋጋ ፣ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማድረግ እና ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በማድረግ ትወደሳለች።
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
#Somaliland
@tikvahethiopia
" የምርጫ ውጤቱን እንቀበላለን " - ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ
ባለፈው ሳምንት በራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ መደረጉ ይታወሳል።
በከፍተኛ ብልጫም የተቃዋሚው ዋደኒ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ " ኢሮ " ምርጫውን አሸንፈዋል።
በምርጫው የተሸነፉት ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ " የምርጫውን ውጤት እንቀበላለን " ብለዋል።
ተመራጩ ፕሬዜዳንትንም " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።
" ባስመዘገቡት ድል እንኳን ደስ አልዎት " ያሉት ፕሬዜዳንት ቢሂ " ሰላማዊና የተረጋጋ የስልጣን ሽግግር እንዲደረግ ለማድረግ የተሟላ ድጋፌን አደጋለሁ " ሲሉ ቃል ገብተዋል።
" የአገልግሎት ዘመንዎ ሰላምን ፣ እድገትን እና ዘላቂ ስኬትን ለሀገራችን እንዲያመጣ እመኛለሁ " ብለዋል።
ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ቢሂ ለህዝቡ ባስተላለፉት መልዕክት " ፕሬዝዳንታችሁ ሆኜ እንዳገለግላችሁ ዕድሉን ስለሰጣችሁኝ አመሰግናለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
" የስልጣን ዘመኔ ማብቂያ ላይ ሆኜ የምለው ነገር ለሀገራችን እድገት ያለኝ ቁርጠኝነት ጸኑ መሆኑን ነው " ሲሉ አክለዋል።
" በአንድነት እና በጋራ ተነስተን ለሶማሌላንድ ብልፅግና እንስራ " ብለዋል።
6ኛው የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት አብዲራህማን ኢሮ " ማንም ተሸናፊ ማንም አሸናፊ የለም ያሸነፈው የሶማሌላንድ ህዝብ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
ሶማሌላንድ እራሷን እንደ ሉዓላዊ ሀገር ምትቆጥር ናት። ከሶማሊያ መንግሥት ጋርም ግንኙነት የላትም። ላለፉት በርካታ ዓመታት ራሷን በራሷ እያስተዳደረች ነው።
እጅግ ሰለማዊ ፣ የተረጋጋ ፣ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማድረግ እና ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በማድረግ ትወደሳለች።
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
#Somaliland
@tikvahethiopia
⚫️ #ኢትዮጵያ ⚫️
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ምን ያልተፈጸም ፤ ምንስ ያልተደረገ ግፍ አለ ?
እጅግ በጣም ሚያስደነግጠው እንዲሁም ፍጹም ከሰውነት ተራ እየተወጣ መሆኑን የሚያሳየው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ልክ ጀግንነት ፣ በጎ ተግባር፣ ፍቅርን ለትውልድ የሚያስተላልፉ ይመስል ግፍና ጭካኔያቸውን በቪድዮ ማስረጃ እራሳቸው ቀርጸው ለትውልድ እያስቀመጡ መሆናቸው ነው።
በእርግጥም እንዲህ እየቀረጹ ማስቀመጣቸው ህዝቡን ለሚፈልጉት ዓላማ ለማነሳሳትና እርስ በርስ ለማባላት፣ ህዝቡን ወደ ግጭት ለማስገባት ሊሆን ይችላል።
በጥላቻ የሚፈጽሙት የግፍ ተግባራቸው አላረካ ብሏቸው ፣ " እዩልን ምን ያህል አውሬ እንደሆንን " የሚለውን ለማሳየትም ይሆናል።
በሀገራችን ፦
🔴 ሰው ከነህይወቱ ሲቃጠል
🔴 በድንጋይ ተወግሮ ሲገደል
🔴 በጅምላ በጥይት ተደብድቦ ወደ ገደል ሲከተት
🔴 አስክሬን ሲጎተት
🔴 አስክሬን አደባባይ ላይ ሲጣል
🔴 ተዘቅዝቆ ሲሰቀል
🔴 በስለት ተቀልቶ ሲገደል
🔴 የጥይት በረዶ ሲዘንብበት ... ኧረ ብዙ ብዙ በቪድዮ ተቀርጾ አይተናል።
ይኸው ዛሬ የሰው ልጅ ልክ እንደ ዶሮ " በስመአብ " ተብሎ ሲታረድ በቁማችን አየን።
ይህ ጭካኔ በማስረጃ በቪድዮ ተቀርጾ የወጣ ነው ለመሆኑ ስንት በቪድዮ ያልተቀረጸ ፣ በየአካባቢው የተፈጸመ ግፍ ይኖር ይሆን ?
እነዚህ ግፍ ፈጻሚ ሰዎች ሰይጣናዊ ስራቸውን በቪድዮ ቀርጸው ማስቀረታቸው በቤተሰብ ፣ በህዝብ ላይ የማይረሳ ቂም፣ ቁርሾና ቁስል ለማኖር ይመስላል።
የትም ይሁን ማንኛውም የግፍ ድርጊት ሲፈጸም ግን የሚቀድመው ድርጊቱን ከልብ አዝኖ ማውገዝ ነው። ፍትህ ተጠያቂነት እንዲሰፍን መጠየቅ ፤ ለፍትህ መታገል ነው።
ልክ ሰው በሞተ ቁጥር ያለ አንዳች ሀዘን እና መከፋት ወደ ፖለቲካ ንትርክ መግባትና የሰው ደም ፈሶ እንዲቀር ለማድረግ መሯሯጥ የግፍ ግፍ ነው።
ከዚህ ቀደም ብዙ ታዝበናል።
ሰው በግፍ ይገደላል ከዛም ሰዎች በየማህበራዊ ሚዲያ ይመጡና " የኔ ወገን ሰው አይገድልም፤ ፍጹም ነው ፣ ፃድቅ ነው ፣ እንዲህ እንዲያደርግ ተፈጥሮው አይፈቅድለትም " እያሉ ድርጊቱ ያራክሱታል።
ሌላው ወገን ይመጣና በሞተው ንጹህ ሰው ደም ፖለቲካ ይሰራል። በጅምላ ጥላቻውን ይተፋል። በዚህ መንገድ የስንት ሰው ደም ፈሶ ቀረ ?
ላለፉት ዓመታት ሰው በግፍ ይገደላል ከዛ የቀናት የማህበራዊ ሚዲያ አጀንዳ ሆኖ ያልፋል፤ ይረሳል። ከዛ ሌላ ግፍ ሌላ ግድያ ይፈጸማል።
አንዳንዱ እውነት ከልቡ አዝኖ ፤ አንዳንዱ ደግሞ የይስሙላ ያዘነ ይመስል ሸፋፍኖ በማህበራዊ ሚዲያው ይጽፋል ፤ ይለፍፋል። ከሰዓታት በኃላ ሁሉም ረስቶት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ ህይወቱ ይመለሳል። ማህበራዊ ሚዲያ ሲገባ ትዝ ሲለው ለቀናት ስሜቱን ይፅፍ ይሆናል።
እስከ ህይወት ፍጻሜ ድረስ በሀዘን የሚቃጠሉትና ልጃቸውን የማይረሱት እናት አባት፣ ወንድም ፣ እህት ቤተሰብ፣ ዘመዶች ናቸው።
በተለይ እናት እና አባት ሲያለቅሱ ነው የሚኖሩት።
ይህ አዙሪት መቆም አለበት። ደመ በፈሰሰ ቁጥር ቁርሾ ቂም እየተወለደ እንጂ ፍቅር አንድነት አይመጣም።
ልጆቹን የተነጠቀ ቤተሰብና አካባቢ እንደሌላው የማህበራዊ ሚዲያ አርበኛ የአንድ ቀን ሀዘን አድርጎ አያልፈውም። የተፈጸመበትን ግፍና በደል መቼም አይረሳውም ! ቂም በውስጡ ያድራል። ይህ በሀገር ህዝብ ትስስር ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ ከባድ ነው።
ከምንም በላይ ለተጎዱ ወገኖች ፍትህ በማስፈን ፣ ሌላ የአንድ ሰው ደም እንዳይፈስ በማድረግ አዙሪቱን ማቆም ካልተቻለ የከፋ ነገር መምጣቱ አይቀርም።
እዚህች ምድር ላይ ነገ ሳይሆን ዛሬ የሰው ልጅ ደም መፍሰስ እንዲቆም ማድረግ ይገባል።
ፍትህ ሊሰፍን ፤ ተጠያቂነት ሊረጋገጥ ይገባል።
ታጣቂም ሆነ አልሆነ ፤ የአካባቢው ፣ የክልሉ የመንግሥት አካል ሆነ አልሆነ ሁሉም በየድርሻው በየደረጃው ሊጠየቅ ይገባል።
እጅግ በጣም አስገራሚው ነገር በምንም አይነት መንገድና ሁኔታ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ቀዳሚ ስራው ሊሆን የሚገባው እና ችግርም ሲፈጠር ለህዝብ የማሳወቅ ኃላፊነት ያለበት መንግሥት የሚፈጸሙ ድርጊቶችን ከማህበራዊ ሚዲያው ጩኸት በኃላ ለመናገር ሲወጣ መታየቱ ነው።
ለመሆኑ የሚፈጸመውን የሚሰማው ከህዝብ ጋር በሚዲያ ነው ? ነዋሪው በሚዲያ ባይጮህ ላያወግዝ ነው ?
ቆይ ልክ እንደማንኛውም ሌላ አካል " አወገዝኩ " ብቻ ነው የሚባለው ወይስ ስለተፈጸመ ግፍ በዝርዝር አጣርቶ ለህዝብ ወጥቶ መረጃ መስጠት ነው የሚገባው ? የመንግሥት ስራ ድርሻው ምንድነው ? ለስንቱ ፍትህ ለተነፈገ እያነባ ላለ ወገን ፍትህ ሰጠ ? ተጠያቂነትን አሰፈነ ? በደል የደረሰባቸውን ካሰ ? ዳግም ደም እንዳይፈስ ተከላከል ? እኚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልስ ይሻሉ።
ህዝብ በሀገሩ የሚሆነውን ሁሉ ያያል ፣ ይታዘባል፣ ይገመግማል ፣ ነጥብም ይይዛል።
በምንም አይነት ሁኔታ የሰው ደም አይፈስስ ፤ ደም ሲፈስ ቂምና ቁርሾ እንጂ ፍቅርና አንድነት አይወለድም።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#TikvahEthiopia
#ናውስ
@tikvahethiopia
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ምን ያልተፈጸም ፤ ምንስ ያልተደረገ ግፍ አለ ?
እጅግ በጣም ሚያስደነግጠው እንዲሁም ፍጹም ከሰውነት ተራ እየተወጣ መሆኑን የሚያሳየው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ልክ ጀግንነት ፣ በጎ ተግባር፣ ፍቅርን ለትውልድ የሚያስተላልፉ ይመስል ግፍና ጭካኔያቸውን በቪድዮ ማስረጃ እራሳቸው ቀርጸው ለትውልድ እያስቀመጡ መሆናቸው ነው።
በእርግጥም እንዲህ እየቀረጹ ማስቀመጣቸው ህዝቡን ለሚፈልጉት ዓላማ ለማነሳሳትና እርስ በርስ ለማባላት፣ ህዝቡን ወደ ግጭት ለማስገባት ሊሆን ይችላል።
በጥላቻ የሚፈጽሙት የግፍ ተግባራቸው አላረካ ብሏቸው ፣ " እዩልን ምን ያህል አውሬ እንደሆንን " የሚለውን ለማሳየትም ይሆናል።
በሀገራችን ፦
🔴 ሰው ከነህይወቱ ሲቃጠል
🔴 በድንጋይ ተወግሮ ሲገደል
🔴 በጅምላ በጥይት ተደብድቦ ወደ ገደል ሲከተት
🔴 አስክሬን ሲጎተት
🔴 አስክሬን አደባባይ ላይ ሲጣል
🔴 ተዘቅዝቆ ሲሰቀል
🔴 በስለት ተቀልቶ ሲገደል
🔴 የጥይት በረዶ ሲዘንብበት ... ኧረ ብዙ ብዙ በቪድዮ ተቀርጾ አይተናል።
ይኸው ዛሬ የሰው ልጅ ልክ እንደ ዶሮ " በስመአብ " ተብሎ ሲታረድ በቁማችን አየን።
ይህ ጭካኔ በማስረጃ በቪድዮ ተቀርጾ የወጣ ነው ለመሆኑ ስንት በቪድዮ ያልተቀረጸ ፣ በየአካባቢው የተፈጸመ ግፍ ይኖር ይሆን ?
እነዚህ ግፍ ፈጻሚ ሰዎች ሰይጣናዊ ስራቸውን በቪድዮ ቀርጸው ማስቀረታቸው በቤተሰብ ፣ በህዝብ ላይ የማይረሳ ቂም፣ ቁርሾና ቁስል ለማኖር ይመስላል።
የትም ይሁን ማንኛውም የግፍ ድርጊት ሲፈጸም ግን የሚቀድመው ድርጊቱን ከልብ አዝኖ ማውገዝ ነው። ፍትህ ተጠያቂነት እንዲሰፍን መጠየቅ ፤ ለፍትህ መታገል ነው።
ልክ ሰው በሞተ ቁጥር ያለ አንዳች ሀዘን እና መከፋት ወደ ፖለቲካ ንትርክ መግባትና የሰው ደም ፈሶ እንዲቀር ለማድረግ መሯሯጥ የግፍ ግፍ ነው።
ከዚህ ቀደም ብዙ ታዝበናል።
ሰው በግፍ ይገደላል ከዛም ሰዎች በየማህበራዊ ሚዲያ ይመጡና " የኔ ወገን ሰው አይገድልም፤ ፍጹም ነው ፣ ፃድቅ ነው ፣ እንዲህ እንዲያደርግ ተፈጥሮው አይፈቅድለትም " እያሉ ድርጊቱ ያራክሱታል።
ሌላው ወገን ይመጣና በሞተው ንጹህ ሰው ደም ፖለቲካ ይሰራል። በጅምላ ጥላቻውን ይተፋል። በዚህ መንገድ የስንት ሰው ደም ፈሶ ቀረ ?
ላለፉት ዓመታት ሰው በግፍ ይገደላል ከዛ የቀናት የማህበራዊ ሚዲያ አጀንዳ ሆኖ ያልፋል፤ ይረሳል። ከዛ ሌላ ግፍ ሌላ ግድያ ይፈጸማል።
አንዳንዱ እውነት ከልቡ አዝኖ ፤ አንዳንዱ ደግሞ የይስሙላ ያዘነ ይመስል ሸፋፍኖ በማህበራዊ ሚዲያው ይጽፋል ፤ ይለፍፋል። ከሰዓታት በኃላ ሁሉም ረስቶት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ ህይወቱ ይመለሳል። ማህበራዊ ሚዲያ ሲገባ ትዝ ሲለው ለቀናት ስሜቱን ይፅፍ ይሆናል።
እስከ ህይወት ፍጻሜ ድረስ በሀዘን የሚቃጠሉትና ልጃቸውን የማይረሱት እናት አባት፣ ወንድም ፣ እህት ቤተሰብ፣ ዘመዶች ናቸው።
በተለይ እናት እና አባት ሲያለቅሱ ነው የሚኖሩት።
ይህ አዙሪት መቆም አለበት። ደመ በፈሰሰ ቁጥር ቁርሾ ቂም እየተወለደ እንጂ ፍቅር አንድነት አይመጣም።
ልጆቹን የተነጠቀ ቤተሰብና አካባቢ እንደሌላው የማህበራዊ ሚዲያ አርበኛ የአንድ ቀን ሀዘን አድርጎ አያልፈውም። የተፈጸመበትን ግፍና በደል መቼም አይረሳውም ! ቂም በውስጡ ያድራል። ይህ በሀገር ህዝብ ትስስር ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ ከባድ ነው።
ከምንም በላይ ለተጎዱ ወገኖች ፍትህ በማስፈን ፣ ሌላ የአንድ ሰው ደም እንዳይፈስ በማድረግ አዙሪቱን ማቆም ካልተቻለ የከፋ ነገር መምጣቱ አይቀርም።
እዚህች ምድር ላይ ነገ ሳይሆን ዛሬ የሰው ልጅ ደም መፍሰስ እንዲቆም ማድረግ ይገባል።
ፍትህ ሊሰፍን ፤ ተጠያቂነት ሊረጋገጥ ይገባል።
ታጣቂም ሆነ አልሆነ ፤ የአካባቢው ፣ የክልሉ የመንግሥት አካል ሆነ አልሆነ ሁሉም በየድርሻው በየደረጃው ሊጠየቅ ይገባል።
እጅግ በጣም አስገራሚው ነገር በምንም አይነት መንገድና ሁኔታ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ቀዳሚ ስራው ሊሆን የሚገባው እና ችግርም ሲፈጠር ለህዝብ የማሳወቅ ኃላፊነት ያለበት መንግሥት የሚፈጸሙ ድርጊቶችን ከማህበራዊ ሚዲያው ጩኸት በኃላ ለመናገር ሲወጣ መታየቱ ነው።
ለመሆኑ የሚፈጸመውን የሚሰማው ከህዝብ ጋር በሚዲያ ነው ? ነዋሪው በሚዲያ ባይጮህ ላያወግዝ ነው ?
ቆይ ልክ እንደማንኛውም ሌላ አካል " አወገዝኩ " ብቻ ነው የሚባለው ወይስ ስለተፈጸመ ግፍ በዝርዝር አጣርቶ ለህዝብ ወጥቶ መረጃ መስጠት ነው የሚገባው ? የመንግሥት ስራ ድርሻው ምንድነው ? ለስንቱ ፍትህ ለተነፈገ እያነባ ላለ ወገን ፍትህ ሰጠ ? ተጠያቂነትን አሰፈነ ? በደል የደረሰባቸውን ካሰ ? ዳግም ደም እንዳይፈስ ተከላከል ? እኚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልስ ይሻሉ።
ህዝብ በሀገሩ የሚሆነውን ሁሉ ያያል ፣ ይታዘባል፣ ይገመግማል ፣ ነጥብም ይይዛል።
በምንም አይነት ሁኔታ የሰው ደም አይፈስስ ፤ ደም ሲፈስ ቂምና ቁርሾ እንጂ ፍቅርና አንድነት አይወለድም።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#TikvahEthiopia
#ናውስ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
⚫️ #ኢትዮጵያ ⚫️ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ምን ያልተፈጸም ፤ ምንስ ያልተደረገ ግፍ አለ ? እጅግ በጣም ሚያስደነግጠው እንዲሁም ፍጹም ከሰውነት ተራ እየተወጣ መሆኑን የሚያሳየው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ልክ ጀግንነት ፣ በጎ ተግባር፣ ፍቅርን ለትውልድ የሚያስተላልፉ ይመስል ግፍና ጭካኔያቸውን በቪድዮ ማስረጃ እራሳቸው ቀርጸው ለትውልድ እያስቀመጡ መሆናቸው ነው። በእርግጥም እንዲህ እየቀረጹ ማስቀመጣቸው…
የእውነት ያለቀስነው መቼ ነው ?
አሁን ላይ ጨምሮ ባለፉት ዓመታት ምን ያህል ግፍ ምን ያህል ጭካኔ ሀገራችን ውስጥ እንደተፈጸመ መናገር መቼም ለቀባሪው ማርዳት ነው።
ግን ግን እውነት አብረን ያለቀስንበት ቀን መቼ ነው ? ትዝ የሚለውስ አለ ?
አንዱ በሀዘን ተሰብሮ ሲያለቅስ አንዱ ይስቃል ይደሰታል ፤ አንዱ ሲደሰት አንዱ ያለቅሳል። ሁሉንም አንድ የሚያደርገው የሰብዓዊነት ስሜትም እየታየ ጠፍቷል ፤ ሞቶ አፈር ለብሷል።
ለማዘን ቅድሚያ ጥያቄው " ማነው ? የትኛው ወገን ነው ? " ብሎ መጠየቅ ተለማምደነዋል። " የኔ " የምንለው ሲሆን ማልቀስ " የሌላው ነው " ብለን ስናስብ ምንም እንዳልተፈጠረ ማለፍ ከዛም ከፍ ሲል ግፉን ኖርማል ለማድረግ መሮጥ ስራችን ሆኗል።
ሌላው ይቅር ግፍና መጥፎ ተግባር ማውገዝ እንኳን ሂሳብ ተሰልቶ ጥቅምና ጉዳቱ ታይቶ፣ ጩኸቱንና የህዝቡን ቁጣ ተመልክቶ ሆኗል።
ከምንም በላይ የሚስፈራው ጭካኔና ግፍ ለሚፈጽሙ ግለሰቦች ያውም ከነማስረስረጃቸው ለሚታዩ ሰዎች ጥብቅና መቆም ለነሱ መከራከር ልምድ እየሆነ መምጣቱ ነው።
" እባካችሁ ነገሩ በደንብ ይጣራ " ማለት አንድ ነገር ሆኖ ሳለ ሰው የግፍ ፈጻሚዎቹ ማንነት የኔ ወገን ነው ብሎ ካሰበ " በፍጹም እንዲህ አያደርጉም ፤ የተፈጠሩበት ተፈጥሮና ስነልቦና አይፈቅድም " ብሎ ድምዳሜ በመስጠት ሌላ ግፍ መፈጸም ተለምዷል።
በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በአማራ ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ... በሌሎችም ክልሎች በመንግሥት ታጣቂዎች፣ መንግሥትን እንፋለማለን ብለው በወጡ ታጣቂዎች ፣ ፓለቲከኞች በሚሰሩት ጥላቻ የተመረዙ ከማህበረሰቡ በወጡ ሰዎች ለማየት የሚከብድ ብዙ ግፍ ተሰርቶ ያውም በቪድዮ ተቀርጾ ታይቷል ዛሬም እዚሁ መንደር አለ።
ድርጊቶቹ ይፋ ሲወጡ አብሮ በጋራ ከማዘን ፍትህን ከመጠየቀ ይልቅ የፈጻሚዎቹ ደጋፊ ሆነው የሚቀርቡ ሰዎች በዘመቻ ነገሩን ለማራከስ እና እንዳልተፈጸመ ለማሳየት የሚሄዱበት ርቀት እውን ነገ ለወጥ ይመጣል ? የሚል ጥያቄ ያስነሳል።
በሌላኛው ጎራ በንጹህ ሰው ደም ጥቅም ያስገኝልኛል ያለውን ፖለቲካ ይጫወታል። ከበፊትም እጠላዋለሁ የሚለውን አካል መርጦ ሌላ እልቂት ይቀሰቅሳል።
በዚህም መሃል በርካቶች እንደወጡ ቀርተው ፍትህ አላገኙም።
ለማህበራዊ ሚዲያ ሰዎች እና ሰላም ያለበት ከተማ ለሚኖሩ ነገሩ የሁለት ቀን ግፋ ቢል የሶስት ቀን አጀንዳ ሆኖ ያልፋል። ከዛ ሌላ ግፍ ይፈጸማል።
እናት አምጣ የወለደችውን ፤ ለፍታ ያሳደገችውን ልጅ እያሰበች ዘላለም በለቅሶ ትኖራለች። ወዳጅ ዘመድ ግፉን እያሰበ አመለካከቱ ተቀይሮና በመጥፎ ስሜት ተሞልቶ ለሌላው እንዳያዝን ሆኖ ይኖራል።
የስንቱ ቤት በሀዘን ፣ የስንቱ ሰው ልብ በቂምና ቁርሾ ፤ ሳይወድ በግዱ በመጥፎ አመለካከት ተሞልቶ ይሆን ?
ይህ ነገር ማብቃት አለበት። ተስፋ የሚሰጥ ትንሽ ሰብዓዊነት ሊኖር ይገባል። ማንም ይሁን ማን ተጠያቂነት ሊፈጠር፣ ፍትህ ሊሰፍን ይገባል።
እናቶች የሞተው ልጆቻቸውን ባይመልስላቸውም ፍትህ ሲያገኙ ቢያንስ እንባቸው ይታበስ ተስፋቸው ይለመልም ይሆናል።
ፍትህ ሲገኝ ዜጎች በሀገራቸው ተስፋቸው ያብባል።
በምንም አይነት ሁኔታ በግጭት ፣ በጦርነት ሆነ በምንም መንገድ በምድሪቱ ደም አይፈሰስ ፣ ሰው አይበደል ፤ የሰው ደም በፈሰሰ ቁጥር ፤ በደል በተፈጸመ ቁጥር ቂም ጥላቻ፣ አለመተዛዘን እየተወለደ እየተስፋፋ ይመጣል።
ደስታውስ ይቅር እውነት አብረን መቼ ነው በጋራ ያለቀስነው ? ብለን እንጠይቅ። ከልብ እንኮንን፣ ሂሳብ አንስራ ፤ የሰው ደም ላይ ፖለቲካ አንቆምር ፤ ለፍትህ እንታገል ! ካልሆነ የሁላችን እጣ ፋንታ እንደወጡ መቅረት ፍትህ አለማግኘት ይሆናል።
#TikvahEthiopia
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#ናውስ
@tikvahethiopia
አሁን ላይ ጨምሮ ባለፉት ዓመታት ምን ያህል ግፍ ምን ያህል ጭካኔ ሀገራችን ውስጥ እንደተፈጸመ መናገር መቼም ለቀባሪው ማርዳት ነው።
ግን ግን እውነት አብረን ያለቀስንበት ቀን መቼ ነው ? ትዝ የሚለውስ አለ ?
አንዱ በሀዘን ተሰብሮ ሲያለቅስ አንዱ ይስቃል ይደሰታል ፤ አንዱ ሲደሰት አንዱ ያለቅሳል። ሁሉንም አንድ የሚያደርገው የሰብዓዊነት ስሜትም እየታየ ጠፍቷል ፤ ሞቶ አፈር ለብሷል።
ለማዘን ቅድሚያ ጥያቄው " ማነው ? የትኛው ወገን ነው ? " ብሎ መጠየቅ ተለማምደነዋል። " የኔ " የምንለው ሲሆን ማልቀስ " የሌላው ነው " ብለን ስናስብ ምንም እንዳልተፈጠረ ማለፍ ከዛም ከፍ ሲል ግፉን ኖርማል ለማድረግ መሮጥ ስራችን ሆኗል።
ሌላው ይቅር ግፍና መጥፎ ተግባር ማውገዝ እንኳን ሂሳብ ተሰልቶ ጥቅምና ጉዳቱ ታይቶ፣ ጩኸቱንና የህዝቡን ቁጣ ተመልክቶ ሆኗል።
ከምንም በላይ የሚስፈራው ጭካኔና ግፍ ለሚፈጽሙ ግለሰቦች ያውም ከነማስረስረጃቸው ለሚታዩ ሰዎች ጥብቅና መቆም ለነሱ መከራከር ልምድ እየሆነ መምጣቱ ነው።
" እባካችሁ ነገሩ በደንብ ይጣራ " ማለት አንድ ነገር ሆኖ ሳለ ሰው የግፍ ፈጻሚዎቹ ማንነት የኔ ወገን ነው ብሎ ካሰበ " በፍጹም እንዲህ አያደርጉም ፤ የተፈጠሩበት ተፈጥሮና ስነልቦና አይፈቅድም " ብሎ ድምዳሜ በመስጠት ሌላ ግፍ መፈጸም ተለምዷል።
በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በአማራ ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ... በሌሎችም ክልሎች በመንግሥት ታጣቂዎች፣ መንግሥትን እንፋለማለን ብለው በወጡ ታጣቂዎች ፣ ፓለቲከኞች በሚሰሩት ጥላቻ የተመረዙ ከማህበረሰቡ በወጡ ሰዎች ለማየት የሚከብድ ብዙ ግፍ ተሰርቶ ያውም በቪድዮ ተቀርጾ ታይቷል ዛሬም እዚሁ መንደር አለ።
ድርጊቶቹ ይፋ ሲወጡ አብሮ በጋራ ከማዘን ፍትህን ከመጠየቀ ይልቅ የፈጻሚዎቹ ደጋፊ ሆነው የሚቀርቡ ሰዎች በዘመቻ ነገሩን ለማራከስ እና እንዳልተፈጸመ ለማሳየት የሚሄዱበት ርቀት እውን ነገ ለወጥ ይመጣል ? የሚል ጥያቄ ያስነሳል።
በሌላኛው ጎራ በንጹህ ሰው ደም ጥቅም ያስገኝልኛል ያለውን ፖለቲካ ይጫወታል። ከበፊትም እጠላዋለሁ የሚለውን አካል መርጦ ሌላ እልቂት ይቀሰቅሳል።
በዚህም መሃል በርካቶች እንደወጡ ቀርተው ፍትህ አላገኙም።
ለማህበራዊ ሚዲያ ሰዎች እና ሰላም ያለበት ከተማ ለሚኖሩ ነገሩ የሁለት ቀን ግፋ ቢል የሶስት ቀን አጀንዳ ሆኖ ያልፋል። ከዛ ሌላ ግፍ ይፈጸማል።
እናት አምጣ የወለደችውን ፤ ለፍታ ያሳደገችውን ልጅ እያሰበች ዘላለም በለቅሶ ትኖራለች። ወዳጅ ዘመድ ግፉን እያሰበ አመለካከቱ ተቀይሮና በመጥፎ ስሜት ተሞልቶ ለሌላው እንዳያዝን ሆኖ ይኖራል።
የስንቱ ቤት በሀዘን ፣ የስንቱ ሰው ልብ በቂምና ቁርሾ ፤ ሳይወድ በግዱ በመጥፎ አመለካከት ተሞልቶ ይሆን ?
ይህ ነገር ማብቃት አለበት። ተስፋ የሚሰጥ ትንሽ ሰብዓዊነት ሊኖር ይገባል። ማንም ይሁን ማን ተጠያቂነት ሊፈጠር፣ ፍትህ ሊሰፍን ይገባል።
እናቶች የሞተው ልጆቻቸውን ባይመልስላቸውም ፍትህ ሲያገኙ ቢያንስ እንባቸው ይታበስ ተስፋቸው ይለመልም ይሆናል።
ፍትህ ሲገኝ ዜጎች በሀገራቸው ተስፋቸው ያብባል።
በምንም አይነት ሁኔታ በግጭት ፣ በጦርነት ሆነ በምንም መንገድ በምድሪቱ ደም አይፈሰስ ፣ ሰው አይበደል ፤ የሰው ደም በፈሰሰ ቁጥር ፤ በደል በተፈጸመ ቁጥር ቂም ጥላቻ፣ አለመተዛዘን እየተወለደ እየተስፋፋ ይመጣል።
ደስታውስ ይቅር እውነት አብረን መቼ ነው በጋራ ያለቀስነው ? ብለን እንጠይቅ። ከልብ እንኮንን፣ ሂሳብ አንስራ ፤ የሰው ደም ላይ ፖለቲካ አንቆምር ፤ ለፍትህ እንታገል ! ካልሆነ የሁላችን እጣ ፋንታ እንደወጡ መቅረት ፍትህ አለማግኘት ይሆናል።
#TikvahEthiopia
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#ናውስ
@tikvahethiopia
#Oromia
🕊 " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም ! " - ነዋሪዎች
🟢 " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
⚪ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው፤... ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ ይሰጣል " - ጃል ሰኚ
⚫ " ስምምነቱን ቀድሞውኑ ከተባረሩ ግለሰቦች ጋር ነው የተፈጸመው " - ከዚህ ቀደም ከመንግሥት ጋር ለድርድር ቁጭ ብሎ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት
ከሰሞኑን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የቀድሞው የማዕከላዊ ዞን አዛዥ ጃል ሰኚ ነጋሳ መካከል የሰላም ስምምነት ተፈርሟል።
የስምምነት ሰነዱ ምን እንደያዘ ፣ ምን ምን ጉዳዮች ላይ መግባባት ተደርሶ ስምምነት እንደተፈረመ ፣ በጃል ሰኚ ስር ምን ያህል ታጣቂ ወደ ሰላም እንደሚመለስ (በቁጥር) ፣ የነዚህ ታጣቂዎች ቀጣይ እጣ ፋንታ ምን እንደሆነ በይፋና በዝርዝር የተባለ ነገር የለም።
ነገር ግን የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ይህ የሰላም ስምምነት ለዜጎች እረፍትን የሚሰጥ ሰላም የሚያሰርጽ መሆኑን ገልጿል።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፤ " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " ብለዋል።
" የኦሮሞ ህዝብ በባህልና በወጉ መሰረት በሮቹን ጠምዶና ፈረሶችን ጭኖ በመውጣት ሰላም ይውረድ ባለው መሰረት ጥሪውን ተቀብላችሁ በመምጣታችሁ በራሴና በክልሉ መንግስት ስም አመሠግናለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህ ሂደት ትልቁን ስራ ለሰራው ሀገር መከላከያ ሠራዊት ምስጋና አቅርበዋል።
ጃል ሰኚ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የኦሮሞ ህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" በዓለም ላይ የሰው ልጅ የፖለቲካ ልዩነት አለው ፤ እኛም ያለንን የፖለቲካ ልዩነት በጠመንጃ ከመፍታት ይልቅ በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት ወስነን ነው ስምምነቱን የመረጥነው " ብለዋል።
ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም ከመንግሥት ጋር ውጭ ሀገር ለሰላም ድርድር ቁጭ ብሎ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ባወጣው መግለጫ " ስምምነቱ ህዝቡን ለማምታታ የተፈጸመ ነው " ሲል ተችቷል።
ስምምነቱን ቀድሞውኑ ከተባረሩ ግለሰቦች ጋር ነው የተፈጸመው ብሏል።
ያም ሆነ ይህ ስምምነቱን ተከትሎ በርካታ ታጣቂዎች የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ማዕከል እየገቡ እንደሆነ ተነግሯል።
ለመሆኑ ነዋሪዎች ምን ይላሉ ?
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች በርካታ ታጣቂዎች ወደተዘጋጀላቸው ማዕከላት እየገቡ እንደሆነ መመልከታቸውን ተናግረዋል።
በርካታ የታጣቂ አባላት የሰላም መንገድ መርጠው በተለይ በምዕራብ ሸዋ ዞን እና በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ባሉ ወረዳዎች እየተመለሱ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ምዕራብ ሸዋ ጮቢ፣ ኢልፈታ፣ ዳኖ እና ጅባት ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ አመያ እና ዳው በሚባሉ ወረዳዎች የቡድኑ አባላት ቅብላ እየተደተገላቸው ነው።
ጃለታ አበበ ፤ " ትላንት እና ዛሬ ብቻ 7 መኪና ነው የተሃድሶ ትምህርት ለመውሰድ ወደ ዞን ከተማ የገቡት። የሰላም ጥሪውን ከተቀበሉት ምንም የቀሩ አይመስለኝም ፤ ክላሽ መትረየስ እና ስናይፐር ይዘው ነው ያሉት " ብለዋል።
" ኢልፈታ፣ ግንደበረት ፣ ወዴሳና አምቦ አጠቃላይ ምእራብ ሸዋ ላይ ብዙ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አባል የሰላም ጥሪ ተቀብሎ እየገባ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በዚህ ልክ የሰላም ጥሪ ተቀብሎ የተመለሰ የታጣቂ ቡድን አባላትን አይተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ጀልዱ ወረዳ በተመሳሳይ ቅበላ እየተደረገላቸው እንደነበር ተሰምቷል።
አቶ ግርማ ሌሎ የጀልዱ ወረዳ ኪልቤ ቀበሌ አስታዳዳሪ ፥ " በትክክልም በሁሉም አቅጣጫ እየተመለሱ ናቸው። ዛሬ እና ትላንት ጀልዱ ወረዳ ጉጁ ከተማ ሲደረሱ ሰው ሁሉ ወጥቶ ሲመለከታቸው ነበር " ብለዋል።
" መጀመሪያ ሲመጡ በየቀበሌያቸው በየቦታው ይሰበሰባሉ ከዛ ወደ መንግሥት ኃይሎች ስልክ ደውለው ነው የቅበላ ሰርዓት የሚደረገው። በጀልዱ በተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ነው እየተበልን ያለነው " ሲሉ አክለዋል።
ዊቱሺኩቴ፣ ኢልኬ ፣ጎሮ ቀበሌዎች የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የመጡባቸው እንደሆኑ ጠቁመዋል።
አሁን ላይ በጃል ሰኚ የሚመሩት የሰላም አማራጭ ተከትለው እየተመለሱ ቢሆንም የሌሎች የቀሩትን እንደማያውቁ አቶ ግርማ ገልጸዋል።
" የህዝቡን ፍላጎት ተመልክተው ይመለሳሉ ብለን እናምናለን " ብለዋል።
ባለፈው ጥቅምት ወር በኪልቤ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና በመንግሥት የፀጥታ አካላት መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ የብዙ ሰው ህይወት አልፏል።
" አሁን ሰላም መውረዱ መሰል የሰው ህይወት ቀጥፈትን ይታደጋል " ሲሉ አቶ ግርማ ተናግረዋል።
እርስ በእርስ መተኳኮሱ ከቆመ በአካባቢው የተደናቀፈው ልማት ይቀጥላል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ፤ የህዝቡ ፍላጎትን ስለሚያስጠብቅ ሰላም መውረዱ አስደሳች እንደሚሆን አክለዋል።
የጮቢ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ጃለታ በቀለ ፤ " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም። አሁን ህዝቡ ለ5 ዓመታት በቀጠለው ጦርነት ተጎድቷል መንግሥት እና ግብረሰናይ ድርጅቶች የህዝቡ ህይወት የሚንሰራራበትን መላ ይዘው ቢመጡ መልካም ነው " ብለዋል።
[ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዋሪዎች ቃል ምንጭ ቪኦኤ አፋን ኦሮሞ ሬድዮ እንደሆነ ይገልጻል ]
ኦሮሚያ ባለፉት አመታት ?
ከ6 ዓመታት በፊት " ለውጥ መጥቷል " ከተባለና መንግሥት ኤርትራ አስመራ ላይ ከኦነግ ጋር ስምምነት ደርሷል ከተባለ በኃላ (ምንም እንኳን የስምምነት ሰነዱ ለህዝብ ይፋ ባይደረግም) ወደ ክልሉ በርካታ ታጣቂዎች ገብተዋል።
ከነዚህም ውስጥ ትጥቅ ሳይፈቱ የገቡ በርካቶች ነበሩ።
ወደ ሃገር ከገቡት ውስጥ " ከኦነግ ፓርቲ ጋር ተለያይተናል " ያሉ አባላት " መንግሥትን በትጥቅ ነው የምንታገለው " ብለው ወደ ጫካ ገብተዋል።
ይህን ተከትሎ በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች መካከል በሚደረግ የተኩስ ልውውጥ በርካቶች አልቀዋል።
እገታ፣ ዘረፋ ተስፋፍቷል።
ተማሪዎች ትምህርት መማር አልቻሉም ፡ ገበሬዎች ማረስ አልቻሉም። ንፁሃን ዛሬም ድረስ ፍዳቸውን እያዩ ነው።
ሰላም ወጥቶ መግባትም የማይታሰብ የሆነባቸው በርካታ ቦታዎች ተፈጥረዋል።
በተለያዩ ቦታዎች ትጥቅ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ትንንሽ ቡድኖችንም እንዲበዙ ሆኗል።
በክልሉ ያለውን የትጥቅ እንቅስቃሴ ሆነ ሰላም የራቃቸውን ቦታዎች ወደ ሰላም ለመመለስ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና መንግሥት መካከል የጠረጴዛ ድርድር ሁለት ጊዜ ከሀገር ውጭ ቢደረግም ጠብ ያለ ተስፋ ያለው ውጤት ሳይመጣ ቀርቶ የትጥቅ እንቅስቃሴ በክልሉ ቀጥሏል።
አሁን ተደርጓል የተባለው የሰላም ስምምነት በጃል ሰኚ ከሚመራው ቡድን ጋር ቢሆንም ሌሎችም የሚመሯቸው ታጣቂዎች በክልሉ ይንቀሳቀሳሉ።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#ኦሮሚያ
@tikvahethiopia
🕊 " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም ! " - ነዋሪዎች
🟢 " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
⚪ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው፤... ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ ይሰጣል " - ጃል ሰኚ
⚫ " ስምምነቱን ቀድሞውኑ ከተባረሩ ግለሰቦች ጋር ነው የተፈጸመው " - ከዚህ ቀደም ከመንግሥት ጋር ለድርድር ቁጭ ብሎ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት
ከሰሞኑን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የቀድሞው የማዕከላዊ ዞን አዛዥ ጃል ሰኚ ነጋሳ መካከል የሰላም ስምምነት ተፈርሟል።
የስምምነት ሰነዱ ምን እንደያዘ ፣ ምን ምን ጉዳዮች ላይ መግባባት ተደርሶ ስምምነት እንደተፈረመ ፣ በጃል ሰኚ ስር ምን ያህል ታጣቂ ወደ ሰላም እንደሚመለስ (በቁጥር) ፣ የነዚህ ታጣቂዎች ቀጣይ እጣ ፋንታ ምን እንደሆነ በይፋና በዝርዝር የተባለ ነገር የለም።
ነገር ግን የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ይህ የሰላም ስምምነት ለዜጎች እረፍትን የሚሰጥ ሰላም የሚያሰርጽ መሆኑን ገልጿል።
አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፤ " ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ " ብለዋል።
" የኦሮሞ ህዝብ በባህልና በወጉ መሰረት በሮቹን ጠምዶና ፈረሶችን ጭኖ በመውጣት ሰላም ይውረድ ባለው መሰረት ጥሪውን ተቀብላችሁ በመምጣታችሁ በራሴና በክልሉ መንግስት ስም አመሠግናለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህ ሂደት ትልቁን ስራ ለሰራው ሀገር መከላከያ ሠራዊት ምስጋና አቅርበዋል።
ጃል ሰኚ " የሰላም ስምምነቱን የተቀበልነው የኦሮሞ ህዝባችንን ስቃይ ከተመለከትን በኃላ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" በዓለም ላይ የሰው ልጅ የፖለቲካ ልዩነት አለው ፤ እኛም ያለንን የፖለቲካ ልዩነት በጠመንጃ ከመፍታት ይልቅ በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት ወስነን ነው ስምምነቱን የመረጥነው " ብለዋል።
ስምምነቱ ለኦሮሞ ህዝብ ትልቅ እፎይታ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም ከመንግሥት ጋር ውጭ ሀገር ለሰላም ድርድር ቁጭ ብሎ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ባወጣው መግለጫ " ስምምነቱ ህዝቡን ለማምታታ የተፈጸመ ነው " ሲል ተችቷል።
ስምምነቱን ቀድሞውኑ ከተባረሩ ግለሰቦች ጋር ነው የተፈጸመው ብሏል።
ያም ሆነ ይህ ስምምነቱን ተከትሎ በርካታ ታጣቂዎች የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ማዕከል እየገቡ እንደሆነ ተነግሯል።
ለመሆኑ ነዋሪዎች ምን ይላሉ ?
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች በርካታ ታጣቂዎች ወደተዘጋጀላቸው ማዕከላት እየገቡ እንደሆነ መመልከታቸውን ተናግረዋል።
በርካታ የታጣቂ አባላት የሰላም መንገድ መርጠው በተለይ በምዕራብ ሸዋ ዞን እና በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ባሉ ወረዳዎች እየተመለሱ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ምዕራብ ሸዋ ጮቢ፣ ኢልፈታ፣ ዳኖ እና ጅባት ፤ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ አመያ እና ዳው በሚባሉ ወረዳዎች የቡድኑ አባላት ቅብላ እየተደተገላቸው ነው።
ጃለታ አበበ ፤ " ትላንት እና ዛሬ ብቻ 7 መኪና ነው የተሃድሶ ትምህርት ለመውሰድ ወደ ዞን ከተማ የገቡት። የሰላም ጥሪውን ከተቀበሉት ምንም የቀሩ አይመስለኝም ፤ ክላሽ መትረየስ እና ስናይፐር ይዘው ነው ያሉት " ብለዋል።
" ኢልፈታ፣ ግንደበረት ፣ ወዴሳና አምቦ አጠቃላይ ምእራብ ሸዋ ላይ ብዙ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አባል የሰላም ጥሪ ተቀብሎ እየገባ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በዚህ ልክ የሰላም ጥሪ ተቀብሎ የተመለሰ የታጣቂ ቡድን አባላትን አይተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ጀልዱ ወረዳ በተመሳሳይ ቅበላ እየተደረገላቸው እንደነበር ተሰምቷል።
አቶ ግርማ ሌሎ የጀልዱ ወረዳ ኪልቤ ቀበሌ አስታዳዳሪ ፥ " በትክክልም በሁሉም አቅጣጫ እየተመለሱ ናቸው። ዛሬ እና ትላንት ጀልዱ ወረዳ ጉጁ ከተማ ሲደረሱ ሰው ሁሉ ወጥቶ ሲመለከታቸው ነበር " ብለዋል።
" መጀመሪያ ሲመጡ በየቀበሌያቸው በየቦታው ይሰበሰባሉ ከዛ ወደ መንግሥት ኃይሎች ስልክ ደውለው ነው የቅበላ ሰርዓት የሚደረገው። በጀልዱ በተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ነው እየተበልን ያለነው " ሲሉ አክለዋል።
ዊቱሺኩቴ፣ ኢልኬ ፣ጎሮ ቀበሌዎች የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የመጡባቸው እንደሆኑ ጠቁመዋል።
አሁን ላይ በጃል ሰኚ የሚመሩት የሰላም አማራጭ ተከትለው እየተመለሱ ቢሆንም የሌሎች የቀሩትን እንደማያውቁ አቶ ግርማ ገልጸዋል።
" የህዝቡን ፍላጎት ተመልክተው ይመለሳሉ ብለን እናምናለን " ብለዋል።
ባለፈው ጥቅምት ወር በኪልቤ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና በመንግሥት የፀጥታ አካላት መካከል በነበረ የተኩስ ልውውጥ የብዙ ሰው ህይወት አልፏል።
" አሁን ሰላም መውረዱ መሰል የሰው ህይወት ቀጥፈትን ይታደጋል " ሲሉ አቶ ግርማ ተናግረዋል።
እርስ በእርስ መተኳኮሱ ከቆመ በአካባቢው የተደናቀፈው ልማት ይቀጥላል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ፤ የህዝቡ ፍላጎትን ስለሚያስጠብቅ ሰላም መውረዱ አስደሳች እንደሚሆን አክለዋል።
የጮቢ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ጃለታ በቀለ ፤ " ሰው በየሄደበት ይገደል ነበር በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ያለፍነው አሁን ከሰላም በላይ ምን ጥቅም አለ ? ሰላምን የሚበልጥ ነገር የለም። አሁን ህዝቡ ለ5 ዓመታት በቀጠለው ጦርነት ተጎድቷል መንግሥት እና ግብረሰናይ ድርጅቶች የህዝቡ ህይወት የሚንሰራራበትን መላ ይዘው ቢመጡ መልካም ነው " ብለዋል።
[ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዋሪዎች ቃል ምንጭ ቪኦኤ አፋን ኦሮሞ ሬድዮ እንደሆነ ይገልጻል ]
ኦሮሚያ ባለፉት አመታት ?
ከ6 ዓመታት በፊት " ለውጥ መጥቷል " ከተባለና መንግሥት ኤርትራ አስመራ ላይ ከኦነግ ጋር ስምምነት ደርሷል ከተባለ በኃላ (ምንም እንኳን የስምምነት ሰነዱ ለህዝብ ይፋ ባይደረግም) ወደ ክልሉ በርካታ ታጣቂዎች ገብተዋል።
ከነዚህም ውስጥ ትጥቅ ሳይፈቱ የገቡ በርካቶች ነበሩ።
ወደ ሃገር ከገቡት ውስጥ " ከኦነግ ፓርቲ ጋር ተለያይተናል " ያሉ አባላት " መንግሥትን በትጥቅ ነው የምንታገለው " ብለው ወደ ጫካ ገብተዋል።
ይህን ተከትሎ በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች መካከል በሚደረግ የተኩስ ልውውጥ በርካቶች አልቀዋል።
እገታ፣ ዘረፋ ተስፋፍቷል።
ተማሪዎች ትምህርት መማር አልቻሉም ፡ ገበሬዎች ማረስ አልቻሉም። ንፁሃን ዛሬም ድረስ ፍዳቸውን እያዩ ነው።
ሰላም ወጥቶ መግባትም የማይታሰብ የሆነባቸው በርካታ ቦታዎች ተፈጥረዋል።
በተለያዩ ቦታዎች ትጥቅ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ትንንሽ ቡድኖችንም እንዲበዙ ሆኗል።
በክልሉ ያለውን የትጥቅ እንቅስቃሴ ሆነ ሰላም የራቃቸውን ቦታዎች ወደ ሰላም ለመመለስ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት እና መንግሥት መካከል የጠረጴዛ ድርድር ሁለት ጊዜ ከሀገር ውጭ ቢደረግም ጠብ ያለ ተስፋ ያለው ውጤት ሳይመጣ ቀርቶ የትጥቅ እንቅስቃሴ በክልሉ ቀጥሏል።
አሁን ተደርጓል የተባለው የሰላም ስምምነት በጃል ሰኚ ከሚመራው ቡድን ጋር ቢሆንም ሌሎችም የሚመሯቸው ታጣቂዎች በክልሉ ይንቀሳቀሳሉ።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#ኦሮሚያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
ሶሪያ በቀጣይ ወዴት ?
የ24 ዓመታት የበሽር አላሳድ አገዛዝ አክትሟል።
ቤተሰባቸውን ይዘውም ሩስያ ገብተዋል። ጥገኝነትም ተሰጥቷቸዋል።
አሁን ላይ የታጠቁ ተቃዋሚዎች መንበሩን ይዘዋል።
አላሳድን አንባገነን እንደሆኑ የሚገልጹ በርካቶች ክስተቱን ለሶሪያ ዘላቂ ሰላም እድል ያመጣል ይላሉ።
ከዚህ በተቃራኒ በሀገሪቱ ብዙ ታጣቂዎች ነፍጥ ስለያዙ ለስልጣን ሲባል ወደ 2ኛው ዙር የእርስ በእርስ እልቂት ሊገባ ይችላል የሚሉ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።
ሶሪያ ከፊቷ ተስፋ እና ስጋት ተደቅኗል።
ሶሪያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱት እነማን ናቸው ?
እ.ኤ.አ 2011 ነው የሶሪያ እርስ በርስ እልቂት የጀመረው።
የተሳታፊው ብዛት በርካታ ነው። እነዚህ የየራሳቸው ተሳትፎ፣ አመለካከት፣ ዓላማ ያነገቡ ናቸው።
ጉዳዩ ወስብስብ ያለ ነው።
👉 የአሳድ መንግሥት ኃይሎች
የሶሪያ አረብ ጦር (SAA) እና የብሔራዊ መከላከያ ኃይል (NDF) እኚህ የአላሳድ የጀርባ አጥንት ናቸው። SAA ኦፊሴላዊ የሆነው የሶሪያ መከላከያ ነው። NDF በመንግሥት የሚደገፍ ሚሊሻ ነው። SAA በኢራን እና ሩስያ ይደገፋል። በቀጣዩ መንግሥት ምስረታ ዕጣ ፋንታቸው ምን ይሆን ? የሚለው ምናልባትም በነ ሩስያ እና ኢራን ተፅእኖ ስር የወደቀ ሊሆን ይችላል።
👉 ነጻ የሶሪያ ጦር (FSA)
ቡድኑ መጀመሪያ የተቋቋመው ከሶሪያ ጦር ከድተው በወጡ አካላት ነው። ከዛም ወደ ተለያዩ አንጃዎች እና ጥምረት ተለውጣል። ብዙ ጊዜ ከምዕራባውያን እና ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ድጋፍ ያገኛል። በብዙ የሶሪያ ክፍሎች ይንቀሳቀሳል ነገር ግን በተለይ በሰሜን የአሳድን ጦር ሲዋጋ ነበር። በኃላም ISISን ሲዋጋ ነበር።
👉 ሀያት ታህሪር አል-ሻም (HTS)
ይህ በመጀመሪያ የሶሪያ የአልቃይዳ ክንፍ ነበር ፤ አልኑስራ በሚል ነበር ይንቀሳቀስ የነበረው። 2017 ላይ ግን በኢድሊብ እና ከፊል አሌፖ ፈርጠም ብሎ ወጥቷል። አላማው እስላማዊ መንግሥት መመስረት እንደሆነ ይነገርለታል። በቅርቡ አሳድን በመገርሰስ ጥቃት ላይ ቁልፍ ሚና ነበረው። በአዲሱ መንግሥት መመስረት ውስጥ የራሱን አላማ ለማስረጽ ግፊት ሊያደርግ ይችላል በዚህም ሴኩላር ከሚባሉት እና መሃከል ላይ ካሉት ጋር ሊጋጭ ይችላል። በኢድሊብ ከነበራቸው የመንግሥት አስተዳደር ጥብቅ የሸሪያ ህግ ለመተግበር ሊሰራ ይችላል።
👉 የሶሪያ ብሔራዊ ጦር (SNA)
እኚህ በቱርክ የሚደገፉ ናቸው። በዋነኝነት በሰሜናዊ ሶሪያ ነው የሚንቀሳቀሱት። የኩርዲሽ ኃይሎችን በመዋጋት የቱርክን ተፅእኖ ለማስረጽ ይንቀሳቀሳሉ ይባላሉ። በአዲሱ መንግሥት የቱርክን ፍላጎት የያዘ ሃሳብ ይዘው ሊቀርቡ ይችላሉ።
👉 የሶሪያ ዴሞክራቲክ ኃይል (SDF)
እኚህ በኩርዲሽ ዋይፒጂ ነው የሚመሩት። በአሜሪካ ድጋፍ ISISን በማሸነፉ ረገድ ትልቁን ሚና ተጫውተዋል። እኚህ ቡድኖች ሰሜናዊ ምስራቅ ሶሪያን ተቆጣጥረው የያዙ ናቸው። ራዕያቸው የፌዴራል፣ ያልተማከለ ሶሪያ እንድትኖር ነው። በማንኛውም አዲስ መንግስት ውስጥ፣ የኩርድ የራስ ገዝ አስተዳደር ወይም ፌደራሊዝም እንዲሰፍን ግፊት ሊያደርጉ ይችላሉ። ይህ ደግሞ እንደ SNA ካሉ ሌሎች ቡድኖች ጋር ሊያጋጫቸው ይችላል።
እንግዴ እኚህ ሁሉ አላማቸው የሚለያይ ነፍጥ ያነገቡ ቡድኖች ናቸው ሶሪያ ውስጥ ያሉት።
ከአሳድ አገዛዝ ወደ አዲስ መንግሥት ለሚደረገው ሽግግር ምናልባትም እጅግ ወሳኝና ጥልቅ ድርድር አልያም የእርስ በእርስ ግጭት በቡድኖቹ መካከል ሊፈጠር ይችላል።
🚨 SAA እና የአሳድ ደጋፊ ሚሊሻዎች ለውጡ ለነሱ ወይም አጋሮቻቸው ምቹ ሁኔታ ካልፈጠረ ሊቃወሙ ይችላሉ።
🚨 HTS ይበልጥ ሃይማኖታዊ የመንግሥት አስታዳደር ለመመስረት ሊንቀሳቀሱ ይችላሉ።
🚨 FSA እና ተመሳሳይ አቋም ያላቸው ቡድኖች ዴሞክራሲያዊ ሂደትን ይደግፋሉ ነገር ግን ጉልህ ተፅእኖ እንዲኖራቸው በአንድ የፖለቲካ ጥላ ስር መጠቃለል አለባቸው።
🚨 SDF ፌዴራሊዝም (ክልላዊ ራስን በራስ የማስተዳደር) እንዲተገበር ግፊት ሊያደርግ ይችላል። ይህን ሞዴል ሌሎች ከተቃወሙት ግጭት መቀጠሉ አይቀሬ ነው።
🚨 ቱርክ በSNA በኩል በምታደርገው ተፅእኖ ጠንካራ ፣ የተማከለ የኩርድ አካል እንዳይፈጠር ለመከላከል በመሆኑ ይህ ወደ ቀጣይ ውጥረት ሊያመራ ይችላል።
በአዲሱ የሶሪያ መንግሥት መስረታ የኃይል መመጣጠን ፣ በቡድኖቹ መካከል ያለው የአስተሳሰብ ልዩነት እና የውጭ ኃይሎች ተፅእኖ ትልቅ ፈታና ይሆናል። የእያንዳንዱ ቡድን ወታደራዊ ጥንካሬ በውጭ ኃይሎች ድጋፍ እና በውስጥ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የተቀረጸ በመሆኑ ሰላማዊ ሽግግር ይኖር ይሆን ? የሚለው አሳሳቢ ነው።
አንዳንዶች ለውጡን በአግባቡ መያዝ ካልተቻለ ሀገሪቱ የመበታተን አደጋ እና ከበፊቱም የባሰ ሰቆቃ ውስጥ ልትገባ የምትችልበት ዕድል ሰፊ እንደሆነ እየገለጹ ነው።
እኚህ ሁሉ ነፍጥ ያነገቡ ቡድኖች ወደ አንድነት መጥተው ጠንካራ ሶሪያን ይመሰርቱ ይሆን ? ወይስ ሁለተኛው ዙር የሶሪያ እርስ በርስ እልቂት ይቀጥላል ? ሁሉንም ጊዜ ይፈታዋል !
🛑 ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን ፅሁፍ ለማዘጋጀት በመሰል ጉዳዮች ላይ የሚተነትኑትን ቻክ ፈረን ጨምሮ የተለያዩ ድረገጾችን ተጠቅሟል።
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
የ24 ዓመታት የበሽር አላሳድ አገዛዝ አክትሟል።
ቤተሰባቸውን ይዘውም ሩስያ ገብተዋል። ጥገኝነትም ተሰጥቷቸዋል።
አሁን ላይ የታጠቁ ተቃዋሚዎች መንበሩን ይዘዋል።
አላሳድን አንባገነን እንደሆኑ የሚገልጹ በርካቶች ክስተቱን ለሶሪያ ዘላቂ ሰላም እድል ያመጣል ይላሉ።
ከዚህ በተቃራኒ በሀገሪቱ ብዙ ታጣቂዎች ነፍጥ ስለያዙ ለስልጣን ሲባል ወደ 2ኛው ዙር የእርስ በእርስ እልቂት ሊገባ ይችላል የሚሉ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም።
ሶሪያ ከፊቷ ተስፋ እና ስጋት ተደቅኗል።
ሶሪያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱት እነማን ናቸው ?
እ.ኤ.አ 2011 ነው የሶሪያ እርስ በርስ እልቂት የጀመረው።
የተሳታፊው ብዛት በርካታ ነው። እነዚህ የየራሳቸው ተሳትፎ፣ አመለካከት፣ ዓላማ ያነገቡ ናቸው።
ጉዳዩ ወስብስብ ያለ ነው።
👉 የአሳድ መንግሥት ኃይሎች
የሶሪያ አረብ ጦር (SAA) እና የብሔራዊ መከላከያ ኃይል (NDF) እኚህ የአላሳድ የጀርባ አጥንት ናቸው። SAA ኦፊሴላዊ የሆነው የሶሪያ መከላከያ ነው። NDF በመንግሥት የሚደገፍ ሚሊሻ ነው። SAA በኢራን እና ሩስያ ይደገፋል። በቀጣዩ መንግሥት ምስረታ ዕጣ ፋንታቸው ምን ይሆን ? የሚለው ምናልባትም በነ ሩስያ እና ኢራን ተፅእኖ ስር የወደቀ ሊሆን ይችላል።
👉 ነጻ የሶሪያ ጦር (FSA)
ቡድኑ መጀመሪያ የተቋቋመው ከሶሪያ ጦር ከድተው በወጡ አካላት ነው። ከዛም ወደ ተለያዩ አንጃዎች እና ጥምረት ተለውጣል። ብዙ ጊዜ ከምዕራባውያን እና ከባህረ ሰላጤው ሀገራት ድጋፍ ያገኛል። በብዙ የሶሪያ ክፍሎች ይንቀሳቀሳል ነገር ግን በተለይ በሰሜን የአሳድን ጦር ሲዋጋ ነበር። በኃላም ISISን ሲዋጋ ነበር።
👉 ሀያት ታህሪር አል-ሻም (HTS)
ይህ በመጀመሪያ የሶሪያ የአልቃይዳ ክንፍ ነበር ፤ አልኑስራ በሚል ነበር ይንቀሳቀስ የነበረው። 2017 ላይ ግን በኢድሊብ እና ከፊል አሌፖ ፈርጠም ብሎ ወጥቷል። አላማው እስላማዊ መንግሥት መመስረት እንደሆነ ይነገርለታል። በቅርቡ አሳድን በመገርሰስ ጥቃት ላይ ቁልፍ ሚና ነበረው። በአዲሱ መንግሥት መመስረት ውስጥ የራሱን አላማ ለማስረጽ ግፊት ሊያደርግ ይችላል በዚህም ሴኩላር ከሚባሉት እና መሃከል ላይ ካሉት ጋር ሊጋጭ ይችላል። በኢድሊብ ከነበራቸው የመንግሥት አስተዳደር ጥብቅ የሸሪያ ህግ ለመተግበር ሊሰራ ይችላል።
👉 የሶሪያ ብሔራዊ ጦር (SNA)
እኚህ በቱርክ የሚደገፉ ናቸው። በዋነኝነት በሰሜናዊ ሶሪያ ነው የሚንቀሳቀሱት። የኩርዲሽ ኃይሎችን በመዋጋት የቱርክን ተፅእኖ ለማስረጽ ይንቀሳቀሳሉ ይባላሉ። በአዲሱ መንግሥት የቱርክን ፍላጎት የያዘ ሃሳብ ይዘው ሊቀርቡ ይችላሉ።
👉 የሶሪያ ዴሞክራቲክ ኃይል (SDF)
እኚህ በኩርዲሽ ዋይፒጂ ነው የሚመሩት። በአሜሪካ ድጋፍ ISISን በማሸነፉ ረገድ ትልቁን ሚና ተጫውተዋል። እኚህ ቡድኖች ሰሜናዊ ምስራቅ ሶሪያን ተቆጣጥረው የያዙ ናቸው። ራዕያቸው የፌዴራል፣ ያልተማከለ ሶሪያ እንድትኖር ነው። በማንኛውም አዲስ መንግስት ውስጥ፣ የኩርድ የራስ ገዝ አስተዳደር ወይም ፌደራሊዝም እንዲሰፍን ግፊት ሊያደርጉ ይችላሉ። ይህ ደግሞ እንደ SNA ካሉ ሌሎች ቡድኖች ጋር ሊያጋጫቸው ይችላል።
እንግዴ እኚህ ሁሉ አላማቸው የሚለያይ ነፍጥ ያነገቡ ቡድኖች ናቸው ሶሪያ ውስጥ ያሉት።
ከአሳድ አገዛዝ ወደ አዲስ መንግሥት ለሚደረገው ሽግግር ምናልባትም እጅግ ወሳኝና ጥልቅ ድርድር አልያም የእርስ በእርስ ግጭት በቡድኖቹ መካከል ሊፈጠር ይችላል።
🚨 SAA እና የአሳድ ደጋፊ ሚሊሻዎች ለውጡ ለነሱ ወይም አጋሮቻቸው ምቹ ሁኔታ ካልፈጠረ ሊቃወሙ ይችላሉ።
🚨 HTS ይበልጥ ሃይማኖታዊ የመንግሥት አስታዳደር ለመመስረት ሊንቀሳቀሱ ይችላሉ።
🚨 FSA እና ተመሳሳይ አቋም ያላቸው ቡድኖች ዴሞክራሲያዊ ሂደትን ይደግፋሉ ነገር ግን ጉልህ ተፅእኖ እንዲኖራቸው በአንድ የፖለቲካ ጥላ ስር መጠቃለል አለባቸው።
🚨 SDF ፌዴራሊዝም (ክልላዊ ራስን በራስ የማስተዳደር) እንዲተገበር ግፊት ሊያደርግ ይችላል። ይህን ሞዴል ሌሎች ከተቃወሙት ግጭት መቀጠሉ አይቀሬ ነው።
🚨 ቱርክ በSNA በኩል በምታደርገው ተፅእኖ ጠንካራ ፣ የተማከለ የኩርድ አካል እንዳይፈጠር ለመከላከል በመሆኑ ይህ ወደ ቀጣይ ውጥረት ሊያመራ ይችላል።
በአዲሱ የሶሪያ መንግሥት መስረታ የኃይል መመጣጠን ፣ በቡድኖቹ መካከል ያለው የአስተሳሰብ ልዩነት እና የውጭ ኃይሎች ተፅእኖ ትልቅ ፈታና ይሆናል። የእያንዳንዱ ቡድን ወታደራዊ ጥንካሬ በውጭ ኃይሎች ድጋፍ እና በውስጥ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የተቀረጸ በመሆኑ ሰላማዊ ሽግግር ይኖር ይሆን ? የሚለው አሳሳቢ ነው።
አንዳንዶች ለውጡን በአግባቡ መያዝ ካልተቻለ ሀገሪቱ የመበታተን አደጋ እና ከበፊቱም የባሰ ሰቆቃ ውስጥ ልትገባ የምትችልበት ዕድል ሰፊ እንደሆነ እየገለጹ ነው።
እኚህ ሁሉ ነፍጥ ያነገቡ ቡድኖች ወደ አንድነት መጥተው ጠንካራ ሶሪያን ይመሰርቱ ይሆን ? ወይስ ሁለተኛው ዙር የሶሪያ እርስ በርስ እልቂት ይቀጥላል ? ሁሉንም ጊዜ ይፈታዋል !
🛑 ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን ፅሁፍ ለማዘጋጀት በመሰል ጉዳዮች ላይ የሚተነትኑትን ቻክ ፈረን ጨምሮ የተለያዩ ድረገጾችን ተጠቅሟል።
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የመሬት መንቀጥቀጡ የቦታ ለውጥ አድርጓል ?
" በአንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም " - ፕ/ር አታላይ አየለ
በትላንትናው ዕለት በቀን፣ በምሽትና በለሊቱ ክፍለ ጊዜ ተደጋጋሚ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጦች መከሰታቸው ዓለም አቀፍ ጁኦሎጂካል ተቋማት ዘግበዋል።
ትላንት ምሽት 2:10 የተከሰተው እና ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ ከተሰማው በሬክተር ስኬል 5.0 ሆኖ ከተመዘገበው መንቀጥቀጥ በተጨማሪ ለሊት 7:20 ላይ 5.1 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አስታውቋል።
የመሬት መንቀጥቀጡ በተጠቀሰው መጠን መከሰቱን እና ዛሬ ጠዋት 2:11 ላይም ሌላ መንቀጥቀጥ በመታየቱ የመተንተን ስራ እየተሰራ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ህዋ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም፤ የሴስሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕ/ር አታላይ አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ትላንት ለሊት 7:20 ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ከደብረ ሲና 52 ኪሜ ርቀት ላይ ምሽት ላይ የተከሰተው ደግሞ ከአዋሽ 14 ኪሜ ርቀት ላይ የተከሰተ ነው መባሉ ከዚህ ቀደም ይከሰት ከነበረበት የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የቦታ ለውጥ አለ ማለት አለመሆኑን አስረድተዋል።
ተመራማሪው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
" ትላንትና ከሰዓት ጀምሮ በጣም የተደጋጋመ ከፍተኛ መጠን ያለው ከ4.6 ጀምሮ እስከ 5.0 የተመዘገበ መንቀጥቀጥ ተከስቷል ፤ ነገር ግን ደብረ ሲና ሲል ከፈንታሌ በወፍ በረር ሲለካ ነው ከተለያየ አቅጣጫ በማየት ነው እንጂ መነሻው ስለተቀየረ አይደለም።
አንድ አካባቢ ላይ መሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት በአቅራቢያው ያለው ከተማ የትኛው ነው ? የሚለው ይታያል ከዛ የተለያዩ ከተሞችን እንደ ሪፈረንስ ይጠቅስና ከዛ ከተማ ምን ያህል ነው የሚርቀው የሚለውን ሪፈር ያደርጋል፤ እንደዛ ሲሆን ሌላ ሰው መንቀጥቀጡ ለዛ ከተማ ቀርቧል ማለት ነው የሚል ስጋት ሊያድርበት ይችላል ነገር ግን እስካሁን የተቀየረ ነገር የለም፤ ፈንታሌ ዙሪያ ነው እንቅስቃሴው እየተታየ ያለው።
የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ እና የጀርመኑ የጂኦ ሳይንስ ተቋማት የሚጠቀሙት ዳታ አውቶማቲክ ነው ሲስተሙ ቶሎ አናላይዝ አድርጎ የተከሰተበትን መጠን እና አካባቢ ከርቀት ጋር ይናገራል ነገር ግን ይህ አይነቱን አዘጋገብ የሚከተሉት ለማህበረሰቡ በምን ያህል ርቀት ላይ ነው የተከሰተው የሚለውን ለማስረዳት ነው።
ለምሳሌ፦ አንድ ብቻ አይደለም የተለያዩ ቦታዎች ይጠቅሳሉ ከመተሃራ፣ከደብረሲና ፣ከደብረ ብርሃን እና ከአዲስ አበባስ ምን ያህል ርቀት ላይ ይገኛል ሊል ይችላል በአንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም።
አዲስ ነገር አይደለም ስንመዘግብ የኖርነው ነገር ነው ነገር ግን መሃንዲስም፣ ኢንቨስተርም ሆነ የሚመለከተው አካል ጆሮ ሰጥቶ ጥንቃቄ አድርጎ አያውቅም አሁን የሚከሰተውንም መአት እንደተከሰተ አድርጎ የሚያወራ አለ እንደዛ አይደለም በተለያየ ጊዜ ይመዘገባል።
በ1997 በአፋር ታይቶ የማይታወቅ የቅልጥ አለት እንቅስቃሴ ነበር ብዙ አለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ሁሉ መጥተው አብረን የሰራናቸው ስራዎች አሉ፣ ፈንታሌም በፈረንጂዎቹ 1981 እንደ አሁኑ 3 እና 4 ወር የቆየ የቅልጥ አለት እንቅስቃሴ ነበር።
የመረጃ ውንዥብር እየተፈጠረ ነው ሳይንቲስት የምንለው ማነው ? ታማኝነቱስ ምን ያህል ነው ?የሚለው አስቸጋሪ ሆኗል ያልሆነውን ሆኗል እያሉ የሚያወናብደውም ብዝቷል ተማረ የምንለውም መሬት ላይ ያለውም ህብረተሰብ።
መሬት በራሷ ጉዞ እየሄደች የምታስተነፍሰው ሃይል ነው ምንም የሚያስደንቅ ነገር አይደለም ቦታውም፣ በምን ያህል ርቀት ላይ እንደሆነ ይታወቃል በተለይ አዲስ አበባ ያለ ሰው ምንም ሊደነግጥ አይገባም።
ከትላንት እኩለ ቀን ጀምሮ ጎላ ጎላ ያሉት መንቀጥቀጦች የመደጋገም ፍጥነታቸው ጨምሯል ቀጣይነትም ያለው ሊሆን ይችላል እየተከታተልን እየመዘገብን እንገኛለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AAU
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
" በአንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም " - ፕ/ር አታላይ አየለ
በትላንትናው ዕለት በቀን፣ በምሽትና በለሊቱ ክፍለ ጊዜ ተደጋጋሚ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጦች መከሰታቸው ዓለም አቀፍ ጁኦሎጂካል ተቋማት ዘግበዋል።
ትላንት ምሽት 2:10 የተከሰተው እና ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ ከተሰማው በሬክተር ስኬል 5.0 ሆኖ ከተመዘገበው መንቀጥቀጥ በተጨማሪ ለሊት 7:20 ላይ 5.1 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አስታውቋል።
የመሬት መንቀጥቀጡ በተጠቀሰው መጠን መከሰቱን እና ዛሬ ጠዋት 2:11 ላይም ሌላ መንቀጥቀጥ በመታየቱ የመተንተን ስራ እየተሰራ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ህዋ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም፤ የሴስሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕ/ር አታላይ አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ትላንት ለሊት 7:20 ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ከደብረ ሲና 52 ኪሜ ርቀት ላይ ምሽት ላይ የተከሰተው ደግሞ ከአዋሽ 14 ኪሜ ርቀት ላይ የተከሰተ ነው መባሉ ከዚህ ቀደም ይከሰት ከነበረበት የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የቦታ ለውጥ አለ ማለት አለመሆኑን አስረድተዋል።
ተመራማሪው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?
" ትላንትና ከሰዓት ጀምሮ በጣም የተደጋጋመ ከፍተኛ መጠን ያለው ከ4.6 ጀምሮ እስከ 5.0 የተመዘገበ መንቀጥቀጥ ተከስቷል ፤ ነገር ግን ደብረ ሲና ሲል ከፈንታሌ በወፍ በረር ሲለካ ነው ከተለያየ አቅጣጫ በማየት ነው እንጂ መነሻው ስለተቀየረ አይደለም።
አንድ አካባቢ ላይ መሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት በአቅራቢያው ያለው ከተማ የትኛው ነው ? የሚለው ይታያል ከዛ የተለያዩ ከተሞችን እንደ ሪፈረንስ ይጠቅስና ከዛ ከተማ ምን ያህል ነው የሚርቀው የሚለውን ሪፈር ያደርጋል፤ እንደዛ ሲሆን ሌላ ሰው መንቀጥቀጡ ለዛ ከተማ ቀርቧል ማለት ነው የሚል ስጋት ሊያድርበት ይችላል ነገር ግን እስካሁን የተቀየረ ነገር የለም፤ ፈንታሌ ዙሪያ ነው እንቅስቃሴው እየተታየ ያለው።
የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ እና የጀርመኑ የጂኦ ሳይንስ ተቋማት የሚጠቀሙት ዳታ አውቶማቲክ ነው ሲስተሙ ቶሎ አናላይዝ አድርጎ የተከሰተበትን መጠን እና አካባቢ ከርቀት ጋር ይናገራል ነገር ግን ይህ አይነቱን አዘጋገብ የሚከተሉት ለማህበረሰቡ በምን ያህል ርቀት ላይ ነው የተከሰተው የሚለውን ለማስረዳት ነው።
ለምሳሌ፦ አንድ ብቻ አይደለም የተለያዩ ቦታዎች ይጠቅሳሉ ከመተሃራ፣ከደብረሲና ፣ከደብረ ብርሃን እና ከአዲስ አበባስ ምን ያህል ርቀት ላይ ይገኛል ሊል ይችላል በአንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም።
አዲስ ነገር አይደለም ስንመዘግብ የኖርነው ነገር ነው ነገር ግን መሃንዲስም፣ ኢንቨስተርም ሆነ የሚመለከተው አካል ጆሮ ሰጥቶ ጥንቃቄ አድርጎ አያውቅም አሁን የሚከሰተውንም መአት እንደተከሰተ አድርጎ የሚያወራ አለ እንደዛ አይደለም በተለያየ ጊዜ ይመዘገባል።
በ1997 በአፋር ታይቶ የማይታወቅ የቅልጥ አለት እንቅስቃሴ ነበር ብዙ አለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ሁሉ መጥተው አብረን የሰራናቸው ስራዎች አሉ፣ ፈንታሌም በፈረንጂዎቹ 1981 እንደ አሁኑ 3 እና 4 ወር የቆየ የቅልጥ አለት እንቅስቃሴ ነበር።
የመረጃ ውንዥብር እየተፈጠረ ነው ሳይንቲስት የምንለው ማነው ? ታማኝነቱስ ምን ያህል ነው ?የሚለው አስቸጋሪ ሆኗል ያልሆነውን ሆኗል እያሉ የሚያወናብደውም ብዝቷል ተማረ የምንለውም መሬት ላይ ያለውም ህብረተሰብ።
መሬት በራሷ ጉዞ እየሄደች የምታስተነፍሰው ሃይል ነው ምንም የሚያስደንቅ ነገር አይደለም ቦታውም፣ በምን ያህል ርቀት ላይ እንደሆነ ይታወቃል በተለይ አዲስ አበባ ያለ ሰው ምንም ሊደነግጥ አይገባም።
ከትላንት እኩለ ቀን ጀምሮ ጎላ ጎላ ያሉት መንቀጥቀጦች የመደጋገም ፍጥነታቸው ጨምሯል ቀጣይነትም ያለው ሊሆን ይችላል እየተከታተልን እየመዘገብን እንገኛለን " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AAU
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia