TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#Telegram የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፈረንሳይ ውስጥ ታሰረ። በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ የዱሮቭን ሁኔታ በቅርብ እየተከታተለ ነው። ዱሮቭ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል። ብሎገሮች በፈረንሳይ ኤምባሲዎች የተቃውሞ ሰልፍ እየጠሩ ናቸው። የቴሌግራም መተግበሪያ መስራቹና ዋና ስራ አስኪያጁ ፓቨል ዱሮቭ ትላንት ቅዳሜ ምሽት ፈረንሳይ ፣ በፈረንሳይ ከፓሪስ ወጣ ብሎ…
#Telegram : የቴሌግራም መስራች እና ዋናው ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፍርድ ቤት ቀርቧል።

ፍርድ ቤት በ5 ሚሊዮን ዩሮ ወይም 5.56 ሚሊዮን ዶላር ዋስ ተለቆ ጉዳዩን እንዲከታተል ወስኖለታል።

ከፈረንሳይ እንዳይወጣ ግን ታግዷል።

እገዳው ተጨማሪ ምርመራ ስለሚደረግ ነው የተጣለው።

በሳምንት ሁለት ጊዜ ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት ተገልጿል።

ዱሮቭ ከቀናት በፊት ፓሪስ አቅራቢያ ኤርፖት ተይዞ ከታሰረ በኃላ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ቆይቶ ነበር። ከዚህ በላይ በህጉ ማቆየት ስለማይቻል ከማቆያ ወጥቶ በፍርድ ቤት ጉዳዩ ታይቷል።

ፍርድ ቤቱም ከፈረንሳይ እንዳይወጣ በማገድ የ5 ሚሊዮን ዩሮ ዋስትና ፈቅዶለታል።

የፈረንሳይ መንግስት ዱሮቭ ላይ ምርመራ የከፈተው በቴሌግራም ፦
- ሞደሬት የማድረግ / ቁጥጥር የማድረግ ክፍተት አለ፣
- ለባለስልጣናት አስፈላጊ መረጃ አይሰጥም
- የወንጀል ድርጊቶች ይፈጸምበታል፣
- የአደገኛ እፅ ዝውውር ይከናወንበታል
- ሽብር፣ መኒ ላውንደሪንግ ይሰራበታል በሚል ነው።

ቴሌግራም ወደ 1 ቢሊዮን ተጠቃሚዎች ያሉት ሲሆን በነጻነቱና ደህንነቱ በተጠበቀ የመልዕክት እና መረጃ ልውውጥ በብዙዎች ዘንድ እጅግ ተመራጭ ነው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Telegram : የቴሌግራም መስራች እና ዋናው ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፍርድ ቤት ቀርቧል። ፍርድ ቤት በ5 ሚሊዮን ዩሮ ወይም 5.56 ሚሊዮን ዶላር ዋስ ተለቆ ጉዳዩን እንዲከታተል ወስኖለታል። ከፈረንሳይ እንዳይወጣ ግን ታግዷል። እገዳው ተጨማሪ ምርመራ ስለሚደረግ ነው የተጣለው። በሳምንት ሁለት ጊዜ ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ እንዳለበት ተገልጿል። ዱሮቭ ከቀናት በፊት ፓሪስ አቅራቢያ ኤርፖት ተይዞ…
#Telegram

የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ፓቨል ድሮቭ ፓሪስ ውስጥ ታስሮ በዋስ ከተለቀቀ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ አስተያየት ሰጥቷል።

ዱሮቭ ምን አለ ?

አብረውት ለነበሩትና ለደገፉትና ፍቅራቸውን ላሳዩት ሁሉ ምስጋና አቅርቧል።

ባለፈው ወር ፓሪስ በደረሰ ወቅት 4 ጊዜ በፖሊስ ኢንተርቪው ተደርጎ እንደነበር ገልጿል።

በዚህ ወቅት የፈረንሳይ ባለስልጣናት ከቴሌግራም ምላሾችን ስላላገኙ ምናልባትም ለሌሎች ሰዎች ህገወጥ የቴሌግራም አጠቃቀም በግል ዱሮቭ ተጠያቂ እንደሚሆን እንደተነገረው አመልክቷል።

ይህ ግን በብዙ ምክንያቶች አስገራሚ እንደነበር አስረድቷል።

- ቴሌግራም የአውሮፓ ህብረት ጥያቄዎችን የሚቀበል እና የሚመልስ በአውሮፓ ህብረት ውስጥ ኦፊሴላዊ ተወካይ አለው። ይፋዊ ኢሜልም አለው።

- የፈረንሳይ ባለስልጣናት እርዳታ ለመጠየቅ ዱሮቭን ለማግኘት ብዙ መንገዶች ነበሯቸው። እንደ አንድ የፈረንሳይ ዜጋ በዱባይ በሚገኘው የፈረንሳይ ቆንስላ ተደጋጋሚ እንግዳም ነበር። ከጥቂት ጊዜ በፊት ደግሞ በግሉ በፈረንሳይ ያለውን የሽብርተኝነት ስጋት ለማስወገድ ከቴሌግራም ጋር የስልክ መስመር እንዲፈጥሩ ረድቷቸዋል።

- አንድ ሀገር በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ደስተኛ ካልሆነ በራሱ በአገልግሎቱ ላይ ህጋዊ እርምጃ መጀመር ነው። ከቅድመ ስማርት ስልክ በፊት የነበረ ህግ አምጥቶ በመተግበሪያው ላይ በሶስተኛ ወገኖች ለሚሰራ ወንጀል የድርጅት ስራ አስፈጻሚን ተጠያቂ ማደረግ ትክክለኛ አካሄድ አይደለም። ቴክኖሎጂን መገንባት በራሱ ከባድ ነገር ነው። ማንም ኢኖቬተር ሌሎች አላግባብ ለሚጠቀሙት አጠቃቀም እሱ በግሉ እንደሚጠየቅ ካወቀ አዲስ ነገር አይፈጥርም።

በግላዊ መረጃ እና በደህንነት መካከል ትክክለኛውን ሚዛን መፍጠር እንዲሁ ቀላል እንዳልሆነ ዱሮቭ ገልጿል።

አንዳንድ ጊዜ ይህን ሚዛን በመጠበቅ ጉዳይ ከሀገራት ተቆጣጣሪዎች ጋር መግባባት ሳይፈጠር ሲቀር ቴሌግራም ሀገራቱን ለቆ እንደሚወጣ አመልክቷል። ይህንን ብዙ ጊዜ እንዳደረገ ገልጿል።

ለአብነት ፦ ሩስያ ለስለላ " የኢንክሪፕሽን ቁልፎችን " መጠየቋን ተከክሎ ቴሌግራም አልሰጥም በማለቱ ሩስያ ውስጥ ቴሌግራም ታግዷል።

ኢራን የሰላማዊ ሰልፎችን ቻናሎች ብሎክ እንዲደረግላት ጠይቃ ቴሌግራም " አላደርገውም አይቻልም " በማለቱ ኢራን ውስጥ ታግዷል።

ዱሮቭ ምስራዎች የሚሰሩት ለገንዘብ ባለመሆነ ከቴሌግራም መርህ ጋር የማይሄድን ገበያ ለቆ ለመውጣት ሁሌም ዝግጁ እንደሆነ ገልጿል።

ይህ ሁሉ ማለት ግን ቴሌግራም ፍጹም ነው ማለት እንዳልሆነ ዱሮቭ አመልክቷል።

የመንግሥት አካላት / ባለስልጣናት ጥያቄያቸውን የት መላክ እንዳለባቸው ግራ ይግባሉ ይህንን ማስተካከል አለብን ብሏል።

ነገር ግን በአንዳንድ ሚዲያዎች ቴሌግራም የስርዓት አልበኞች መፈንጫ ተደርጎ የሚቀርበው ፍጹም ሀሰተኛ ነው ሲል ገልጿል።

" በየቀኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ጎጂ ፖስቶችን እና ቻናሎችን እናስወግዳለን " ያለው ዱሮቭ በየዕለቱ ግልጽነት መፍጠሪያ ሪፖርቶችም እንልካለን ብሏል።

መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች (NGOs) ጋር አስቸኳይ የሞደሬሽን ጥያቄዎችን በፍጥነት ለማስተናገድም የቀጥታ ስልክ መስመሮችም አሉን ሲል አክሏል።

" ሆኖም ግን ይህ በቂ አይደለም የሚሉ ድምፆችን እንሰማለን " ያለው ዱሮቭ " የተጠቃሚዎች ብዛት ወደ 950 ሚሊዮን መድረስ ወንጀለኞች የእኛን መድረክ አላግባብ ለመጠቀም ቀላል አድርጎላቸዋል። በዚህ ረገድ ያሉ ነገሮችን በከፍተኛ ሁኔታ ማሻሻል የግል ግቤ አድርጊያለሁ " ብሏል።

ይህ ሂደት በውስጥ በኩል መጀመሩን ጠቁሞ በቀጣይ ስላለው ሁኔታ ተጨማሪ ዝርዝር ጉዳዮች በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ አሳውቋል።

ያለፈው ወር ክስተት ቴሌግራም እና የማህበራዊ አውታረመረብ ኢንዱስትሪን በጠቅላላ ደህንነቱ የተጠበቀና ጠንካራ እንደሚያደርገው ተስፋ እንዳለው ዱሮቭ ገልጿል።

#TikvahEthiopia
#Telegram

@tikvahethiopia
#Telegram

" አዲሱ ደንብ መተግበሪያውን ለወንጀል የሚጠቀሙት ሰዎችን ቅስም የሚሰብር ይሆናል " - ዱሮቭ

ቴሌግራም አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ የደንበኞቹን መረጃዎች ለሕግ አካላት አሳልፎ ሊሰጥ ነው።

በዚህም የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ፦
➡️ ስልክ ቁጥሮች፣
➡️ የኢንተርኔት አድራሻ
➡️ ሌሎችንም መረጃዎች በፖሊስ፣ በፍርድ ቤት በመሳሰሉ የሕግ ተርጓሚዎች በሚፈለግበት ጊዜ ሊሰጥ እንደሚችል ቴሌግራም አሳውቋል።

የቴሌግራም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፔቨል ዱሮቭ ይህ አዲስ ደንብ እንደሆነው አመልክተዋል።

ይህ አዲስ ደንብ " መተግበሪያውን ለወንጀል የሚጠቀሙት ሰዎችን ቅስም የሚሰብር ይሆናል " ብለዋል።

" 99.999% የቴሌግራም ተጠቃሚዎች ከወንጀል ጋር የሚያያይዛቸው አንዳችም ነገር የለም። 0.001% የሚሆኑት ግን ለድብቅ ወንጀል እየተጠቀሙበት የቴሌግራምን ዝና እና ክብርን እያጎደፉት ይገኛሉ። ይህ ደግሞ ቢሊዮን የሚጠጉ ጨዋ ተጠቃሚዎቻችን የሚጎዳ ነው " ብለዋል።

ዱሮቭ ባለፈው ወር በፈረንሳይ ፣ ፓሪስ ኤርፖርት በቁጥጥር ሥር ውለው እንደነበር አይዘነጋም።

በፖሊስ ከተያዙ በኋላ የቀረበባቸው ክስ " መተግበሪያው ለወንጀለኞች መፈንጫ እንዲሆን ፈቅደዋል " የሚል ነበር።

" ሕገ ወጥ የሕጻናት ምስሎች ዝውውርና የአደገኛ እጽ አዘዋዋሪዎችን በሚያበረታታ መልኩ መተግበሪያው ለወንጀል ተግባር እንዲውል ፈቅደዋል " በሚል የተከሰሱት ዱሮቭ ከሕግ አካላት ጋር ባለመተባበርም ተወንጅለው ነበር።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው በበኩላቸው ሌሎች ለፈጸሙት ወንጀል እሳቸው ተከሳሽ መሆናቸው " አስደናቂ እና ግራ የሚያጋባ " ነገር ነው ሲሉ የፈረንሳይ ባለሥልጣናትን ወርፈው ነበር።

በኃላ ፍ/ቤት ዱሮቭ በዋስ ወጥተው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ማዘዙ ይታወሳል።

#Telegram #BBC

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
ቅዳሜ ጥር 10 ከረፋዱ 4:30 ቀጣይ ዙር የጥያቄ እና መልስ ውድድር በቴሌግራም ቻናላችን ላይ ይደረጋል። በየሳምንቱ አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀልና ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ 👇
https://yangx.top/BoAEth

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#Telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ