TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
" 50,000 ብር ተቀጥተዋል " - የአ/አ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ፤ በከተማው በተሰራው የኮሪደር ልማት ለተሽከርካሪ ባልተፈቀደ የእግረኛ መንገድ ላይ " ሆን ብለው በቸልተኝነት " የደንብ መተላለፍ ፈጽመዋል ያለውን ግለሰብ በ50,000 ብር መቀጮ መቅጣቱን አሳውቋል።

ቅጣቱ የተላለፈባቸው በሠሌዳ ቁጥር ኮድ 2 C 03643 አ.አ የተመዘገበ የቤት መኪና ሲያሽከረክሩ የነበሩ ግለሰብ ናቸው።

" ግለሰቡ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ቀደም ሲል የቀይ ሽብር ሠማዕታት ወይም ሠላም ፓርክ በተሠራ የልማት ኮርደር ላይ ለተሽከርካሪ ባልተፈቀደ የእግረኞች መንገድ  ሆን ብለው በቸልተኝነት በማጥፋት አምልጠው ተሰውረው ነበር " ብሏል ባለልስጣኑ።

ለግዜው ቢሠወሩም ግን በአዲስ አበባ  ትራፊክ ፖሊስ አባላት ክትትል ከነ ተሽከርካሪያቸው በዛሬው ዕለት መያዛቸውን ፤ ባጠፉት ጥፋት መሰረት 50,000/ሃምሳ ሺህ ብር/ ብር መቀጣታቸውን አሳውቋል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
🔈#የተማሪዎችድምጽ

° “ ሳንመረቅ አመታት ተቆጠሩ፡፡ ዩኒቨርሲቲው መቼ እንደሚጠራን ያሳውቀን ” - ተመራቂ ተማሪዎች

° “ መስከረም 2017 ዓ/ም መጀመሪያ አካባቢ ይጠራሉ ” - መቐለ ዩኒቨርሲቲ


ትግራይ ውስጥ በነበረው ጦርነት ሳቢያ ጭምር የመመረቂያ ጊዜያቸው የተራዘመባቸው የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለመመረቅና ድግሪ ለመያዝ አመታትን እንደጠበቁ ፣ አሁንም ዩኒቨርሲቲው እንዳልጠራቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

ተማሪዎቹ ምን አሉ ?

- ከዚህ ቀደም ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተን ስለጉዳዩ ዩኒቨርሲቲውን ጠይቀን ነበር። የመውጫ ፈተና እንደምንፈተን እና ነሐሴ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ላይ እንደምንመረቅ ነበር ስኬጁል የወጣው።

- የመውጫ ፈተናውን ብንወስድም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናን ተከትሎ ዩኒቨርሲቲውን ለቀን ወጥተናል። ከዚያ ነሐሴ 2016 ዓ/ም ትጠራላችሁ ተባልን፡፡ አሁን የክረምት ተማሪዎችም ተጠርተዋል፡፡ እስካሁን የኛ ግን ምንም ነገር የለም። ዝም ጭጭ ብለዋል።

- የፌደራል መንግስትም በጦርነነቱ ጊዜ የነበሩ ተማሪዎች በዓመት 3 ሴሚስተር ማካካሻ ጊዜ ፈቅዶልን ነበር፡፡ ያኔ የተፈቀደልንን ማካካሻ በአግባቡ ያስተናግዱን።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥ የጠየቀው መቐለ ዩኒቨርሲቲ ፤ “ ተማሪዎቹ እያነሱት ያለው ቅሬታ ትክክል ነው ” ብሏል።

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዚደንት ተከስተ ብርሃን (ዶ/ር) ምን አሉ ?

በተለያዩ ምክንያቶች በተለይ ትግራይ ክልል ውስጥ በነበረው ጦርነት ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ ትምህርት ያቋረጡ ተማሪዎች አሉን።

ክረምቱን እንዲማሩ ነበር በዩኒቨርሲቲው ማኔጀመንት የወሰነው። ነገር ግን በአገር ደረጃ በተሰጠው ዳይሬክሽን መሠረት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች እንዲፈተኑ መደበኛ ተማሪዎቹ ማስወጣት የግድ ነበር።

በኮረና እና በነበረውም ጦርነት ትምህርታቸውን ያቋረጡ የክረምት ተማሪዎች ነበሩ። እነርሱንም ተቀበልን፡፡ ለመምህራን የሚሰጥ ስልጠና አለ፡፡ እነርሱንም ተቀብለን እያሰለጠንን ነው።

በእነዚህ ምክንያቶች መደበኛ ተማሪዎቻችንን መጥራት አልቻልንም።

አሁን እንደ አቅጣጫ የያዝነው መስከረም 2017 ዓ/ም መጀመሪያ አካባቢ ጠርተን ማካካሽ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ባለፉት ዓመታት ሊመረቁ ለነበሩ ተማሪዎች ብቻ ካላንደር አዘጋጅተን በአጭር ጊዜ ውስጥ ትምህርታቸውን አጠናቀው እንዲመረቁ ነው።

መስከረም ስንት ቀን ይጠራሉ ? ቁርጥ ያለውስ ቀን መቼ ነው ? ለሚለው ጥያቄ ተከሰተ (ዶ/ር)፣ " የክረምት ተማሪዎቹ ነሐሴ 30 ቀን 2016 ዓ/ም እንዲያጠናቅቁ ብለናል፡፡ ስለዚህ ካላንደሩ ገና አልጸደቀም መስከረም መጀመሪያ አካባቢ ይጠራሉ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

#TIkvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
ዓለም ወደለየለት ቀውስ ውስጥ ትገባ ይሆን ? የፍልስጤም እና እስራኤል ጦርነት መቆሚያ ማጣቱን ተከትሎ በየጊዜው አዳዲስ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ ፤ መካከለኛው ምስራቅ እየታመሰ ነው። ምንም ሰላማዊ መፍትሄ በመጥፋቱ አሁንም በጦርነቱ ሰዎች እያለቁ ነው። " ፍልስጤምን አትንኳት " የሚሉና ሃማስን የሚደግፉ ኃይሎችም እስራኤልን በሮኬት / ሚሳኤል መደብደብ አላቋረጡም። ከሰሞኑን ግን በኢራን ቴህራን ውስጥ…
" ኢራን ዛሬ ምሽት ጥቃት እንደምትሰነዝር ሰምቻለሁ " - ትራምፕ

ዶናልድ ትራምፕ  ፥ " ኢራን ዛሬ ምሽት በእስራኤል ላይ ጥቃት እንደምታደርስ ሰምቻለሁ " ብለዋል።

" ዛሬ ምሽት ኢራን በእስራኤል ላይ ጥቃት ልትሰነዝር እንደምትችል ሰምቻለሁ፤ ጥቃት ይደርስባቸዋል [እስራኤል] ይህን እነግራችኋለሁ " ሲሉ አዲን ሮስ ከተሰኘ ዩትዩበር ጋር በነበራቸው ቆይታ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ትራምፕ " እኔኮ ፕሬዝዳንት ብሆን ኖሮ ማንም ስለዚያ ቃል (ጥቃት) እንኳን አይነገርም ነበር ፣ ምክንያቱም ይህ 100% አይከሰትም ነበር " ብለዋል።

በመካከለኛ ምስራቅ ያለው ውጥረቱ እጅግ የተባባሰ ሲሆን ምንም እንኳን ሰዓቱና ቀኑ ባይነገረም የኢራን ጥቃት አይቀርም ተብሏል።

የተለያዩ ሀገራት ኢራንን " እባክሽ ሁኔታውን አረጋጊው " ብለው ቢማጸኗትም " እስራኤልን ሳልቀጣት አርፌ አልቀመጥም " ብላለች።

በእስራኤል እና በአሜሪካ በኩልም ፥ የኢራን ጥቃት ትፈጽማለች ተብሎ ዝግጅት ማድረጋቸው ተነግሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia🇪🇹 የፓሪስ ኦሎምፒክ የ5,000 ሜትር የሴቶች ፍጻሜ ውድድር ተጀምሯል። ሀገራችን ኢትዮጵያ ፦ 🇪🇹 በአትሌት ጉዳፍ ፀጋይ 🇪🇹 በአትሌት መዲና ኢሳ 🇪🇹 በአትሌት እጅጋየሁ ተወክላለች። መልካም ዕድል ለሀገራችን ኢትዮጵያ ! More - @tikvahethsport
ኬንያዎቹ ወርቁንም ብሩንም ጠራርገው ወስደውታል።

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው ሲፋን ሀሰን 3ኛ ሆና በመውጣት ነሃስ ወስዳለች።

የሀገራችን ልጆች እጅጋየሁ ታዬ 6ኛ ፣ መዲና ኢሳ 7ኛ ፣ ጉዳፍ ፀጋይ 9ኛ ሆነው አጠናቀዋል።

ኢትዮጵያ በዚህ ስሟ በገነነበት ርቀት ከሜዳሊያ ውጭ ሆናለች።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

በፓሪስ ኦሎምፒክ የሴቶች 800 ሜትር ፍጻሜ ውድድር ጀምሯል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ ፦
🇪🇹 በአትሌት ወርቅነሽ መሰለ 
🇪🇹 በአትሌት ፅጌ ድጉማ ተወክላለች።

በዚህ እንኳን አስደስቱን ፤ ተስፋን ስጡን !

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ኬንያዎቹ ወርቁንም ብሩንም ጠራርገው ወስደውታል። ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው ሲፋን ሀሰን 3ኛ ሆና በመውጣት ነሃስ ወስዳለች። የሀገራችን ልጆች እጅጋየሁ ታዬ 6ኛ ፣ መዲና ኢሳ 7ኛ ፣ ጉዳፍ ፀጋይ 9ኛ ሆነው አጠናቀዋል። ኢትዮጵያ በዚህ ስሟ በገነነበት ርቀት ከሜዳሊያ ውጭ ሆናለች። @tikvahethiopia
ፌዝ ኪፕዬጎን ውጤቷ ተሰረዘ ፤ ሲፋን ሃሰን ሁለተኛ ሆነች።

ከደቂቃዎች በፊት በ5000ሜትር ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው ፌዝ ኪፕዬጎን ውጤቷ መሰረዙ ተገልፆል።

ኪፕዬጎን በውድድሩ ከጉዳፍ ፀጋይ ጋር በነበራቸው አካላዊ ንክኪ (መደነቃቀፍ) ምክንያት ውጤቷ ሊሰረዝ ችሏል።

ይህንንም ተከትሎ ሲፋን ሀሰን ሁለተኛ ፤ ጣልያናዊቷ ባቶሶሌቲ ሶስተኛ ሆነዋል።

Via @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
ብር ለኢትዮጵያ የ800ሜትር ሴቶች ውድድር ፍፃሜውን ሲያገኝ አትሌት ፅጌ ድጉማ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ለሀገራችን ሁለተኛውን የብር ሜዳሊያ አስገኝታለች። @tikvahethiopia
#TsigeDuguma

ፈረንሳይ ፓሪስ ላይ በ800 ሜትር የሴቶች ፍጻሜ ለሀገሯ ኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ያስገኘችው ፅጌ ዱጉማ ከውድድሩ በኃላ " JESUS IS LORD ! " የሚል ጽሁፍ አሳይታለች።

ፅጌ ስሟ ተጽፎ ደረቷ ላይ ከተለጠፈበት ወረቀት የጀርባ ክፍል ላይ ነው ይህን መልዕክት ፅፋ ገብታ ያስተላለፈችው።

የዘንድሮ የፓሪስ ኦሎምፒክ የመክፈቻ ስነስርዓት በክርስቲያኖች ዘንድ ቁጣ ቀስቅሶ እንደነበር ይታወሳል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
ፌዝ ኪፕዬጎን ውጤቷ ተሰረዘ ፤ ሲፋን ሃሰን ሁለተኛ ሆነች። ከደቂቃዎች በፊት በ5000ሜትር ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ያጠናቀቀችው ፌዝ ኪፕዬጎን ውጤቷ መሰረዙ ተገልፆል። ኪፕዬጎን በውድድሩ ከጉዳፍ ፀጋይ ጋር በነበራቸው አካላዊ ንክኪ (መደነቃቀፍ) ምክንያት ውጤቷ ሊሰረዝ ችሏል። ይህንንም ተከትሎ ሲፋን ሀሰን ሁለተኛ ፤ ጣልያናዊቷ ባቶሶሌቲ ሶስተኛ ሆነዋል። Via @tikvahethsport
ኬንያ የብር ሜዳሊያዋን አስመለሰች።

ከጉዳፍ ፀጋይ ጋር በነበረው መገፋፋት (መደነቃቀፍ) የፌዝ ኪፒዬጎን ውጤት መሰረዙን ተከትሎ የኬንያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ይግባኝ በማቅረብ ይግባኙ ተቀባይነት አግኝቷል።

ይህን ተከትሎ የኪፕዬጎን 2ኛ ደረጃ መፅደቁን የሀገሪቱ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አሳውቋል።

በዚህም ኬንያ በ5000ሜትር ውድድር የወርቅ እና ብር ሜዳልያ አሸናፊ መሆን ችላለች።

ኔዘርላንዳዊቷ አትሌት ሲፋን ሀሰን ወደ ሶስተኛ ደረጃዋ ተመልሳለች።

ድራማዊ ነው !

@tikvahethiopia
We are Hiring !

Ethio telecom is seeking to hire young, energetic, and customer-focused professionals with zero years of experience for the position of Contact Center Advisor proficient in:

👉🏼 Amharic
👉🏼 Afaan Oromoo
👉🏼 Af-Somali and
👉🏼 Tigrigna

Qualified individuals who meet the requirements are encouraged to apply through the Ethio telecom website before August 11, 2024. 

Click here to apply: https://bit.ly/3AchAM4
Watch how to apply for the vacancy: youtu.be/6h-78lnmft8
" እባካችሁ የመኖሪያ ፍቃዴን አፋልጉኝ !

እኔ ወንድማችሁ ከጀርመን ሀገር ነው የመጣሁት።

ከላይ የምትመለከቱት የጀርመን ሀገር የመኖሪያ ፍቃድ ጠፍቶብኛል።

ፍቃዱ የጠፋብኝን ትክክለኛ ቦታ ማወቅ ባልችልም በዕለቱ ከለቡ ወደ አዳማ መስመር በመኪና ተጎዤ ነበር።

የኤምባሲው ፕሮሰስ ረጅም ጊዜ የሚወስድ ነው። ረጅም ዓመታት በጀርመን ሀገር የሰራሁበት ፍቃድ ነው።

ለትብብራችሁ በፈጣሪ ስም እያመሰገንኩ ፤ ወረታውንም እከፍላለሁ

0911251959 የስልክ ቁጥሬ ነው "

@tikvahethmagazine
“ የልጅነት ልጄን አድኑልኝ። ሁለት የልብ ክፍተት ህመም አለበት ፤ ለህክምና 665 ሺህ ብር ተጠይቄአለሁ ” - የመቐለ ዩኒቨርሲቲ መምህር

የ2 ዓመት ከ5 ወር ልጃቸው የታመመባቸው አቶ ገ/መድህን መብርሃቱ የተባሉ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ መምህር፣ ለህክምና የተጠየቁት ገንዘብ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ እርዳታ እንዲደረግላቸው ተማጸኑ።

ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡት የህፃኑ አባት፣ “ ህፃኑ ሁለት የልብ ክፍተት አለበት። ጥቁር አንበሳ የህፃናት ልብ ህሙማን መርጃ ማዕከል ሂጄ ነበር ‘ወረፋው ብዙ ነው’ አሉኝ ” ብለዋል።

“ የግል ህክምና ሂጄ ደግሞ ‘ልጄህ በአስቸኳይ ካልታከመ አደጋ ላይ ነው’ አሉኝ። ለህክምናው 665 ሺህ ብር ተጠይቄአለሁ። ይህ ገንዘብ በጣም ከአቅሜ በላይ ነው ” ሲሉ አክለዋል።

“ መምህር ነኝ። የማስተምረው መቐለ ዩኒቨርሲቲ ነው። ይሄ የልጅነት ልጄ ነው። ገና 29 ዓመቴ ነው " ያሉት መምህሩ፣ " የኢትዮጵያ ህዝብ ያቅሙን በማዋጣት የልጅነት ልጄን በማትረፍ ይተባበረኝ ” ሲሉ ተማጽነዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ሀኪም ቤት ደብዳቤ ለህክምና የተጠየቀው ገንዘብ 665 ሺህ ብር መሆኑን፣ ሌላኛው የህክምና ውጤት ደግሞ፣ ህፃኑ ሁለት የልብ ክፍተት እንዳለበት ያስረዳል።

መርዳት ለምትሹ፣ የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000543793508 (ገብረመድህን መብራህቱ ኣብርሃ)፣ ለመደወል 0914178980 (አባት)፣ 0946482480 ተ/ወይኒ ፍሰሃ (እናት) መጠቀም ይቻላል።
 
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ዕለታዊ : ንግድ ባንክ ምዛሬውን በትላንትናው ተመን ሲያስቀጥል በግል ባንኮችም ዛሬ ያን ያህል ለውጥ የለም።

በንግድ ባንክ ዛሬ ዶላር እንደትላንቱ መግዣው 95.6931 ሲሆን መሸጫው 101.4347 ነው።

የሌሎችም ሀገራት ምንዛሬ በትላንቱ ቀጥሏል።

ባንኩ ከቅዳሜ አንስቶ ተመሳሳይ የምንዛሬ ተመን እየተጠቀመ ነው።

እስካሁን ድረስ ዕለታዊ ምዛሬያቸውን ይፋ ያደረጉ የግል ባንኮችም ቢሆኑ የአብዛኞቹ ምንዛሬያቸው ከትላንት ብዙ የሚለይ አይደለም።

(የዛሬ ሐምሌ 30/2016 ዓ/ም የባንኮች ዕለታዊ ምንዛሬ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia