TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gambella ንፁሃንን " መረጃ ሰጥታችኋል " በሚል በአቃቂ ሁኔታ #እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ፤ ግድያው ላይም ተሳትፈዋል ከተባሉ ተከሳሾች ውስጥ የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ በተከሰሱበት ክስ #ነጻ መባላቸው ተሰምቷል። ሌሎች የቀድሞ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች እና የልዩ ኃይል አዛዦችን ጨምሮ 12 ተከሳሾች ግን የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል። …
#EHRC #Gambella

“ ቪዲዮው የቆየ ነው ፤ ከሁለት ዓመት በፊት ነው ” - የኢሰመኮ ጋምቤላ ክልል ጽሕፈት ቤት

ባለፉት ሳምንታት ውስጥ አንድ እጅግ በጣም አሰቃቂ ቪድዮ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወር ቆይቷል።

እውነት ለመናገር በቪድዮ ላይ የሚታየው የጭካኔ ተግባር በቃላት የሚገለጽ አይደለም።

ቪድዮው የጋምቤላ ክልል የጸጥታ ልብስ የለበሱ አካላት ሰዎችን እጅግ በአሰቃቂ ሁኔታ በድንጋይ ጭምር ጭንቅላታቸውን እየፈጠፈጡ በጅምላ ሲገድሏቸው የሚያሳይ ለማየት የሚከብድ ዘግናኝ ቪዲዮ ነው።

ይህን ቪዲዮ የተመለከቱ በርካቶች ፣ “ እውነት እኛ ሀገር ነው ? እኛ ሀገር ከሆነስ ለዚህ ተግባር ተጠያቂነት እና ፍትሕ ተረጋግጧል ? ” በማለት በእጅጉ አዝነው ጠይቀዋል።

አብዛኛዎቹ ሰዎችም ቪዲዮው ከሰሞኑን የተፈጸመ ጥቃት አድርገውም የወሰዱ ነበሩ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለጉዳዩ ቅርብ ናቸው ያላቸውን አካላት ስለቪድዮው ጠይቋል።

ይህንን ቪዲዮ ኮሚሽናችሁ ተመልክቶት ነበር ? በማለት የጠየቃቸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋምቤላ ክልል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አቤል አዳነ፣ “ ቪዲዮው የቆየ ቪዲዮ ነው። ከሁለት ዓመታት በፊት የነበረ ቪዲዮ ነው ” ብለዋል።

ሰኔ 7 / 2014 ዓ/ም “ የሸኔና ጋነግ ” ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል ገብተው ጥቃት እንደፈጸሙ አስታውሰዋል።

በኋላ “ የክልሉ ልዩ ኃይሎች ‘ ኦነግ ሸኔ ቀርተዋል ’ ብለው የጠረጠሯቸውን ሰዎች በየቤታቸው እየሄዱ፣ እዛው ፓሊስ ኮሚሽን አካባቢ ወስደው ግድያ ፈጽመውባቸዋል ” ነው ያሉት።

“ ይህንን ቪዲዮ ጨምረን ሌሎችንም ምርመራ አድርገን የምርመራውን ሪፓርት ይፋ አድርገናል በሰዓቱ ” ብለዋል።

የኮሚሽኑ አስተያዬት የተካተተበትን ሪፓርትም ልከዋል። 

ግድያውን የፈጸሙት አካላት በሕግ ፊት ተጠያቂ ተደርገው ይሆን ? በማለት ላቀረብንላቸው ጥያቄ “ በዚህ ጉዳይ ላይ ተጠርጥረው የታሰሩ ሰዎች አሉ ” ብለዋል።

ከፌደራል ፓሊስ ፣ ከፍትህ ሚኒስቴር የተውጣጣ አጣሪ መርማሪ ቡድንም ጋምቤላ መጥቶ ጉዳዩን እንደመረማረና ‘በጉዳዩ ላይ ተጠይቂ ናቸው’ ብሎ የሚያስባቸውን ሁሉ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጎ የፍርድ ሂደታቸው እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል።

ከነዚህም ውስጥ በወቅቱ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር የነበሩትና ምክትላቸውን ጨምሮ ሌሎችም እንዳሉበት አክለዋል።

ትላንትና ከሰኔ 7 ቀን 2014 የጋምቤላ ክስተት ጋር በተያያዘ ንፁሃንን " መረጃ ሰጥታችኋል " በሚል በአቃቂ ሁኔታ #እንዲገደሉ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል ፤ ግድያው ላይም ተሳትፈዋል የተባሉ ፦
➡️ የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ አመራሮች ፣
➡️ የልዩ ኃይል አዛዦች (ዋናውና ምክትሉ)
➡️ የተለያዩ የጸጥታ አባላት
የጥፋተኝነት ፍርድ እንደተላለፈባቸው ፤ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የቀድሞ ዋና ኮሚሽነር አቡላ ኦባንግ ግን በተከሰሱበት ክስ #ነጻ መባላቸው ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
ስቴም ፖወር !

ኢትዮጵያ ለሚገኙ ወጣት ሴቶች ለ3ተኛ ዙር የቀረበ ጥሪ !

ስቴም ፖወር (STEMpower) ከፊንላንድ ኤምባሲ (Embassy of Finland Ethiopia) እና ከአይቢኤም (IBM) ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ከ1,000 በላይ ሥራ አጥ ወጣት ሴቶችን ተግባራዊ የሥራ ክህሎት ለመስጠት ያለመ " ትጋት " የተሰኘ ፕሮግራም አስተዋውቀዋል።

ባለፉት 2 ዙሮች 1700 በላይ ለሚሆኑ ሴቶች በ Project Management, Web Development , Cyber Security, Digital Marketing , Data Analytics , Information Technology , Job Readiness , Work Readiness ስልጠና የሰጠ ከመሆኑ በተጨማሪ የስራ እድል በመፈጠር ተጠቃሚ እንዲሆኑ እድል አመቻችቷል፡፡

#ነጻ በሚሰጠውና ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው ሰርተፊኬት በሚያስገኘው በዚህ ስልጠና እነዚህን ኮርሶች ለመውሰድ ፍላጎት ያላችሁ ሴቶች ምዝገባ የጀመርን መሆኑን እያሳወቅን ምዝገባው የሚቆየው ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 10 , 2017 ዓ/ም ሲሆን ቀድማችሁ በመመዝገብ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እንጋብዛለን፡፡

እነዚህን ኮርሶች ለመውሰድ ፍላጎት ያላችሁ ከስር ባለውን ሊንክ ይመዝገቡ
👉Link: https://forms.office.com/r/bJedLrdqmd