ወደ ኖርዌይ ለልምድ ልውውጥ የሄዱ የሁለት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ወደ ሀገር ሳይመለሱ ቀሩ።
የኢዜማ እና የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት ለልምድ ልውውጥ ከሃገር በወጡበት አለመመለሳቸው ተሰምቷል።
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦሮ) የሴቶች ጉዳይ ሃላፊ ወ/ሮ አበበች ደቻሳ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የሴቶች ጉዳይ ተጠሪ የነበሩት ወ/ሮ ቅድስት ግርማ በመስከረም አጋማሽ ለልምድ ልውውጥ ወደ #ኖርዌይ ባቀኑበት ወቅት አለመመለሳቸው ተነግሯል።
ሁለቱ አባላት ወደ ኖርዌይ ያቀኑትና ያልተመለሱት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የልምምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ በተላኩበት ወቅት መሆኑን የም/ ቤቱ ጸሃፊ አቶ ደስታ ዲንቃ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አባላቱ በጋራ ምክር ቤቱ የሴቶች ክንፍ ሰብሳቢነት እና ስራ አስፈጻሚነት ሲያገለግሉ ነበር።
አቶ ደስታ ፥ " የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማጠናከር በሃገር ደረጃ ከፓርላማ አባላት ጋር እና የሲቪክ ተቋማት ጋር እየተገናኙ ብዙ ስራዎችን ሲሰሩ ነበር " ብለዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የኢዜማ አባል ፤ አባሏ በስራ ገበታቸው ላይ አለመኖራቸው በማስረዳት " ለምን እንዳልተመለሱ የምናውቀው ነገር የለም " ብሏል።
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በበኩሉ ከልጆቿና ከባለቤቷ ጋር በፖለቲካ ምክንያት ለእስር ተዳርገው እንደነበር የገለጸ ሲሆን ለመቅረቷም ምክንያት ይህ ሳይሆን እንዳልቀረ ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢዜማ እና የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት ለልምድ ልውውጥ ከሃገር በወጡበት አለመመለሳቸው ተሰምቷል።
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቦሮ) የሴቶች ጉዳይ ሃላፊ ወ/ሮ አበበች ደቻሳ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የሴቶች ጉዳይ ተጠሪ የነበሩት ወ/ሮ ቅድስት ግርማ በመስከረም አጋማሽ ለልምድ ልውውጥ ወደ #ኖርዌይ ባቀኑበት ወቅት አለመመለሳቸው ተነግሯል።
ሁለቱ አባላት ወደ ኖርዌይ ያቀኑትና ያልተመለሱት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የልምምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ በተላኩበት ወቅት መሆኑን የም/ ቤቱ ጸሃፊ አቶ ደስታ ዲንቃ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አባላቱ በጋራ ምክር ቤቱ የሴቶች ክንፍ ሰብሳቢነት እና ስራ አስፈጻሚነት ሲያገለግሉ ነበር።
አቶ ደስታ ፥ " የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማጠናከር በሃገር ደረጃ ከፓርላማ አባላት ጋር እና የሲቪክ ተቋማት ጋር እየተገናኙ ብዙ ስራዎችን ሲሰሩ ነበር " ብለዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የኢዜማ አባል ፤ አባሏ በስራ ገበታቸው ላይ አለመኖራቸው በማስረዳት " ለምን እንዳልተመለሱ የምናውቀው ነገር የለም " ብሏል።
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በበኩሉ ከልጆቿና ከባለቤቷ ጋር በፖለቲካ ምክንያት ለእስር ተዳርገው እንደነበር የገለጸ ሲሆን ለመቅረቷም ምክንያት ይህ ሳይሆን እንዳልቀረ ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia