TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርድር መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አዛዥ መሮ ዲሪባ ፥ የታጠቂ ቡድኑን ከፌደራል መንግሥቱ ጋር የሚያደራድር ሦስተኛ አካል መኖሩን ለቢቢሲ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል። ጃል መሮ አደራዳሪዎቹ እነማን እንደሆኑ በስም ከጥቀስ ተቆጥበዋል። መሮ ዲሪባ ታጣቂ ቡድኑን ወክለው ከመንግሥት ጋር የሚደራደሩ የልዑክ ቡድን አባላት ወደ #ታንዛኒያ ጉዞ እያደረጉ ስለመሆኑ አሳውቀዋል።…
#Update
" ወደ ፖለቲካዊ ስምምነት እንደሚያመራ ተስፋ እናደርጋለን " - ኑር ሙሀሙድ
የኢትዮጵያ መንግስት እና በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰው የታጣቂ ቡድን መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት በታንዛኒያ ከፊል ራስ ገዝ በሆነችው #ዛንዚባር ንግግር መጀመራቸውን ኢጋድ አሳውቋል።
የኢጋድ ቃል አቀባይ ኑር ሙሀሙድ ሼይኽ በታንዛኒያ ንግግር መጀመሩን ገልጸው ፤ " ወደ ፖለቲካዊ ስምምነት እንደሚያመራ ተስፋ እናደርጋለን " ብለዋል።
ሁለቱም ተደራዳሪ አካላት ንግግር ስለመጀመሩ ማረጋገጫ ቢሰጡም ዝርዝር መረጃ ይፋ አላደረጉም ፤ የታንዛኒያ ባለስልጣናትም ስለድርድሩ የተለየ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ሮይተርስ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነገር ግን ስለ ድርድሩ በቅርበት የሚየውቁ ሁለት ሰዎችን ዋቢ በማድረግ ባሰራጨው ዘገባ የኢትዮጵያ መንግሥት ተደራዳሪ ልዑክ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የሚመራ ሲሆን በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ቡድን በማን እንደሚመራ ዘገባው ያለው ነገር የለም።
#ሮይተርስ
@tikvahethiopia
" ወደ ፖለቲካዊ ስምምነት እንደሚያመራ ተስፋ እናደርጋለን " - ኑር ሙሀሙድ
የኢትዮጵያ መንግስት እና በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰው የታጣቂ ቡድን መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት በታንዛኒያ ከፊል ራስ ገዝ በሆነችው #ዛንዚባር ንግግር መጀመራቸውን ኢጋድ አሳውቋል።
የኢጋድ ቃል አቀባይ ኑር ሙሀሙድ ሼይኽ በታንዛኒያ ንግግር መጀመሩን ገልጸው ፤ " ወደ ፖለቲካዊ ስምምነት እንደሚያመራ ተስፋ እናደርጋለን " ብለዋል።
ሁለቱም ተደራዳሪ አካላት ንግግር ስለመጀመሩ ማረጋገጫ ቢሰጡም ዝርዝር መረጃ ይፋ አላደረጉም ፤ የታንዛኒያ ባለስልጣናትም ስለድርድሩ የተለየ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ሮይተርስ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነገር ግን ስለ ድርድሩ በቅርበት የሚየውቁ ሁለት ሰዎችን ዋቢ በማድረግ ባሰራጨው ዘገባ የኢትዮጵያ መንግሥት ተደራዳሪ ልዑክ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የሚመራ ሲሆን በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ቡድን በማን እንደሚመራ ዘገባው ያለው ነገር የለም።
#ሮይተርስ
@tikvahethiopia