TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#Gondar

ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ አዲስ ከንቲባ ተሾመላት።

አቶ ባዩህ አቡሃይ በዛሬው ዕለት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል።

የጎንደር ከተማ ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ በሚገኘው 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ነው አቶ ባዩህ አቡሃይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አድርጎ የሾመው።

ምንጭ፦ የጎንደር ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia
Audio
#Gondar

የጎንደር ግጭት ከተማዋን አስከፊ ሁኔታ ላይ እንደጣላት አንድ በጎንደር ሆስፒታል የሚሰራ የቲክቫህ የቤተሰብ አባል የሆነ የሕክምና ዶክተር አሳውቆናል።

የጎንደር ሁኔታ #እጅግ_አስከፊ እንደነበር የገለፀልን የህክምና ዶክተሩ " በግጭቱ ምክንያት የመጨረሻ ኢሰብአዊ ድርጊት ተፈጽሟል ፤ ሰላማዊ ዜጎች እዚህም እዚያም ተገድለዋል " ሲል አስረድቷል።

በሆስፒታሉ ውሃ ፣ ኦክስጂን ፣ እንዲሁም ደግሞ መድሃኒት ቤት ከመድሃኒት ውጭ እየሆኑ መሆኑን ገልጿል።

" የከባባድ መሳሪያ ድምጾች ከሆስፒታሉ ውስጥ ሆነን ይሰማን ነበር " ያለው ዶክተሩ ላለፉት ቀናት ከተማዋ በተኩስ ስትናጥ መቆየቷን አመልክቷል።

እስከ ትላንት ሰኞ ከሰዓት ድረስ በግጭቱ ምክንያት የተጎዱ ሰዎችን ወደ ሆስፒታል የሚያመላልስ እና አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ አንድ አምቡላንስ ብቻ እንደነበር እሱም በሚያስዝን ሁኔታ ዒላማ መደረጉን የጎንደር ሆስፒታል ዶ/ር የሆነው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል አሳውቆናል።

የንፁሃን ነዋሪዎች ጉዳይ ትኩረት የሚሻው መሆኑን አስገንዝቧል።

(ድምፅ ዛሬ ጥዋት ላይ የተቀዳ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gondar የጎንደር ግጭት ከተማዋን አስከፊ ሁኔታ ላይ እንደጣላት አንድ በጎንደር ሆስፒታል የሚሰራ የቲክቫህ የቤተሰብ አባል የሆነ የሕክምና ዶክተር አሳውቆናል። የጎንደር ሁኔታ #እጅግ_አስከፊ እንደነበር የገለፀልን የህክምና ዶክተሩ " በግጭቱ ምክንያት የመጨረሻ ኢሰብአዊ ድርጊት ተፈጽሟል ፤ ሰላማዊ ዜጎች እዚህም እዚያም ተገድለዋል " ሲል አስረድቷል። በሆስፒታሉ ውሃ ፣ ኦክስጂን ፣ እንዲሁም ደግሞ…
#GONDAR

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የህክምና ዶክተር የሆነው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በከተማው ስላለው ሁኔታ መረጃዎችን አጋርቶናል።

- ታማሚዎች በኦክስጂን እና ደም እጥረት እየሞቱ መሆኑን ገልጿል።

- ለአምቡላንስ ጨምር ምንምአይነት የትራንስፖርት አማራጭ እንደሌለ ፤ ታማሚዎች በሰው ኃይል በሸክም ወደ ሆስፒታሉ እየመጡ መሆኑን አስረድቷል።

- ወደ 20 (ሰላማዊ ሰዎች) ወደ ሆስፒታሉ ከደረሱ በኃላ እንደሞቱ እንዲሁም ከ200 በላይ ሰዎች ተጎድተው ሆስፒታል እንደሚጡ ከነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ ሰላማዊ ሰዎች መሆናቸውን ገልጿል።

- በርከታ ሰዎች በቤታቸው ሞተው፣ ቀብራቸውም በአካባቢያቸው በተለይም በቀበሌ 4 ፣ 12 ፣ 11 እና 18 መፈፀሙን አመልክቷል።

- ባለፈው ሰኞ በነበረ ግጭት ከሆስፒታሉ የተወሰኑ ህፃዎች በመሳሪያ ቢመቱትም የተጎዳ ሰው ግን እንዳልነበር ገልጿል።

- ሆስፒታሉ ምግብ እንዲሁም መድሃኒት እያለቀበት መሆኑን አመልክቷል።

ዛሬ ጎንደር እንዴት ናት ?

አሁን ላይ በጎንደር ከተማ ከየትኛውም አቅጣጫ የተኩስ ድምፅ እየተሰማ አይደለም። ጥዋት ላይ ለጥቂት ሰከንድ ፒያሳ እና ቀበሌ 18 አካባቢ ተኩስ ተሰምቶ ነበር።

ከትላንት ማታ አንስቶ ዛሬም ጥዋት በከተማው አብዛኛው ክፍል ላይ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለ ሲሆን ሰራዊቱ በሆስፒታሉ አካባቢም መኖሩን ይኸው ዶክተር ገልጿል።

የህክምና ዶክተሩ ከምንም በላይ በሆስፒታል ያለው የኦክስጅን ፣ የደም እጥረት እንዲሁም የአምቡላንስ ትራንስፖርት ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በመግለፅ መፍትሄ እንዲፈለግ ጥሪ አቅርቧል።

ጥንታዊቷ እና ታሪካዊቷ #ጎንደር ባለፉት ቀናት ከፍተኛ የሆነ ግጭት ካስተናገዱ የአማራ ክልል ከተሞች መካከል አንዷ ናት።

@tikvahethiopia