TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.7K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#UN

እ.ኤ.አ. ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ በኢትዮጵያ መንግስት እና በሰብአዊ ድጋፍ አጋሮች አማካኝነት ከ17,000 ሜትሪክ ቶን በላይ የእርዳታ እህል ትግራይ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዛሬ አሳውቋል።

ድርጅቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ተጨማሪ በግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለመድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እስራኤል ኔታኒያሁ አፍሪካዊያን ስደተኞችን ከእስራኤል ለማስወጣት ለሚያዝ እቅድ ፍቃድ መስጠታቸው ተነገረ። በትላንትናው ዕለት በቴል አቪቭ ጎዳናዎች ላይ በኤርትራዊያን ስደተኞች መካከል የተፈጠረውን አስከፊ ግጭት ተፈጥሮ ነበር። ይህን ተከትሎ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ ደም በተቃባው ግጭት ላይ የተሳተፉት ስደተኞች በሙሉ በአስቸኳይ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እንደሚፈልጉ አስታውቀዋል።…
#Update #UN

እስራኤል ኤርትራውያንን በጅምላ ከማባረር እንድትቆጠብ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠይቋል።

የእስራኤል ባለሥልጣናት በዛቱት መሠረት ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎችን ከሀገሪቱ የሚያስወጡ ከሆነ፣ “ዓለም አቀፍ ሕግን እንደሚተላለፉ” እና ከፍተኛ ሰብዓዊ ችግር እንደሚያስከትልም ድርጅቱ አስታውቋል።

በኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች እና በተቃዋሚዎች መካከል፣ ባለፈው ቅዳሜ በቴል አቪቭ - እስራኤል በተፈጠረ ግጭት፣ በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውንና ንብረት መውደሙን ተከትሎ፣ የአገሪቱ ባለሥልጣናት፣ በግጭቱ የተሳተፉ ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎችን ከሀገር እንደሚያስወጧቸው ዝተው ነበር፡፡

የኤርትራን 30ኛ ዓመት የነፃነት ቀን አስመልክቶ፣ በቴል አቪቭ ተዘጋጅቶ በነበረ ክብረ በዓል ላይ፣ የኤርትራ መንግሥት ደጋፊዎች በአንድ ወገንና ተቃዋሚዎች በሌላ ወገን ተሰልፈው በተፈጠረ ኀይል የተቀላቀለበት ግጭት ዐያሌዎች ተጎድተዋል።

የፖሊስ አባላትም ጉዳት እንደደረሰባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

የተፈጠረው ግጭት እጅግ እንዳሳሰበው የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ገልጾ፣ መረጋጋት እንዲኖር እና ሁለቱም ወገኖች ሁኔታውን ከማባባስ እንዲቆጠቡ ጠይቋል።

ባለፈው ሰኔ በወጣ መረጃ፣ 17 ሺሕ 850 ኤርትራውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች በእስራኤል እንደሚገኙ ታውቋል።

በግጭቱ 170 ጥገኝነት ጠያቂዎች እና በደርዘን የሚቆጠሩ የእስራኤል ፖሊስ አባላት እንደተጎዱ የስደተኞች ኮሚሽኑ ገልጿል።

(ቪኦኤ)
ቪድዮ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
A_HRC_54_55_AdvanceUneditedVersion.docx
79.2 KB
#ETHIOPIA #UN

ኢትዮጵያ ውስጥ ጦርነት እንዲቆም ስምምነት ከተፈረመ አንድ አመት ሊሞላው ቢቃረብም አሁንም ግፍ፣ የጦር ወንጀሎች እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች እየተፈፀሙ ነው ሲል በተመድ ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ኤክስፐርቶች ኮሚሽን ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አሳወቀ።

ኮሚሽኑ የሰላሙ ሁኔታ አሁንም ያልተረጋገጠ መሆኑን ጠቁሟል።

ኮሚሽኑ ባወጣው ባለ 21 ገጽ ሪፖርቱ ከህዳር 3 ቀን 2020 ጀምሮ በግጭቱ ውስጥ በተሳተፉ #ሁሉም_አካላት የተፈፀሙ መጠነ ሰፊ አሰቃቂ ድርጊቶችን አስፍሯል።

ከእነዚህም ውስጥ ፦
- የጅምላ ግድያ፣
- አስገድዶ መድፈር፣
- ረሃብ፣
- የትምህርት ቤቶች እና የህክምና ተቋማት ውድመት፣
- የግዳጅ / በኃይል ማፈናቀል እና የዘፈቀደ እስራት ይገኙበታል።

የኮሚሽኑ ሊቀመንበር መሀመድ ቻንዴ ኦትማን ፤ " የሰላም ስምምነቱ መፈረሙ በአብዛኛው የመሳሪያ ድምፅ ጸጥ ያሰኘው ቢሆንም ፤ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በተለይም በትግራይ ያለውን ግጭት አልፈታም ወይም ምንም አይነት አጠቃላይ የተሟላ ሰላም አላመጣም " ብለዋል።

" በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በአማራ ክልል በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርስ የመብት ጥሰት እና በትግራይ እየተፈጸመ ያለ ግፍን የሚገልጹ ሪፖርቶች እንዳሉት ኮሚሽኑ አሳውቋል።

ኮሚሽኑ ያፋ ባደረገው ሪፖርት፤ የኤርትራ ወታደሮች እና የአማራ ሚሊሻ አባላት ትግራይ ውስጥ ከፍተኛ ጥሰቶችን መፈፀም መቀጠላቸውን አመልክቷል። ይህም ስልታዊ የሆኑ አስገድዶ መድፈር፣ በሴቶች እና ልጃገረዶች ላይ የሚፈፀም ፆታዊ ጥቃቶችን እንደሚያካትት አመልክቷል።

ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ በመንግስት ሃይሎች ይፈፀማል ስላለው የሰላማዊ ዜጎች እስራት እና የማሰቃየት ድርጊትን በተመለከተ በሪፖርቱ ላይ አስፍሯል።

በተጨማሪም ፤ በቅርቡ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ በአማራ ተወላጅ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን የሚያሳዩ በርካታ ሪፖርቶችን እንዳገኘ አሳውቋል።

ኮሚሽኑ ፤ የአማራ ክልል የጸጥታ ሁኔታ እያሽቆለቆለ መምጣቱ እና ለጭካኔ ወንጀሎች የሚያጋልጡ ሁኔታዎች መኖራቸው በእጅጉ እንደሚያሳስበው አመልክቷል።

ይህ ሁኔት በኢትዮጵያ እንዲሁም በሰፊው ቀጣና መረጋጋት ላይ እንዲሁም በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሴቶች፣ ወንዶች፣ ህፃናት ላይ እንድምታ እንዳለው ገልጿል።

https://www.ohchr.org/en/press-releases/2023/09/ethiopia-nearly-one-year-after-ceasefire-un-experts-warn-ongoing-atrocities

(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
Report_of_the_Ethiopian_Human_Rights_Commission_EHRC_and_the_Office.PDF
1.6 MB
#EHRC #UN #ሪፖርት

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽህፈት ቤት ከሐምሌ ወር 2014 ዓ/ም - መጋቢት ወር 2015 ዓ/ም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች በሽግግር ፍትሕ ጉዳይ ላይ ከተጎጂዎችና ጉዳት ከደረሰባቸው ማኅበረሰቦች ጋር ባደረጉት ምክክር የተገኙ ግኝቶችን በተመለከተ ይፋ ያደረጉት ባለ 90 ገጽ ሪፖርት ከላይ ባለፈው ፋይል ተያይዟል።

@tikvahethiopia
#FoodandAgricultureOrganization #UN

የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ  የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያ ተሸለሙ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ ሽልማት የተሰጣቸው ዛሬ በጣልያን፤ ሮም ከተማ ነው።

በተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት (FAO) ፤ ሮም ውስጥ ባሰናዳው ዝግጅት ዶ/ር ዐቢይ ፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እያደረጉ ላለው ጥረት የከበረውን አግሪኮላ ሜዳልያ እንዳበረከተላቸው ተነግሯል።

የፋኦ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ኩ ዶግዩ ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፋኦ ከፍተኛ ሽልማት ለሆነው አግሪኮላ ሜዳልያ ሽልማት በመብቃታቸውን " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።

ይህ ሽልማት መሪዎች እና ሌሎችም የዓለማችን እውቅ ሰዎች የምግብ ዋስትናናን ደህንነትን ለማረጋገጥ እና ድህነትን ለመቀነስ ለሚያደርጉት የተሳካ ጥረት የሚሰጥ እንደሆነ ጠቁመዋል።

በዚህም የአግሪኮላ ሜዳሊያ ለጠ/ ሚኒስትሩ እየተበረከተው ፦
* በኢትዮጵያ ገጠርና ኢኮኖሚ ልማት ላይ ላበረከቱት አስተዋፅኦ
* በተለይም " በስንዴ፤ ምግብ እራስን መቻል ፕሮግራም " ባደረጉት የግል ድጋፍ
* በኢትዮጵያ አረንጓዴ ሌጋሲ (Green Legacy) ስራ መሆኑን አስረድተዋል።

ከዚህ ባለፈ ዋና ዳይሬክተሩ " ባለፉት 5 አመታት ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለችውን አስደናቂ እድገት ተመልክቻለሁ " ማለታቸው ተነግሯል።

ይህ ሊሆን የቻለው " በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጡ ውጤታማ፣ ተጠያቂነት ያለውና የተረጋጋ አመራር ነው " ያሉት የፋኦ ዋና ዳይሬክተር ፤ ተመልክቼዋለሁ ያሉት እድገት የተመዘገበው " ባለፉት ዓመታት በነበሩ አስቸጋሪ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ውስጥ ነው ፤... ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን እንደ አህጉር ለአፍሪካም ይልቅ መልዕክት ነው " ማለታቸው ተሰምቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በበኩላቸው የተሰጣቸውን ሽልማትና እና እውቅናን ተከትሎ ባሰራጩት መልዕክት ምስጋና አቅርበው ፤ " ከፍ ያለ ጠቀሜታ ባላቸውና የኢንደስትሪ ግብዓት በሆኑ የግብርና ምርቶች ላይ ማተኮራችን ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እያስገኘልን ይገኛል። የምግብ ሉዓላዊነት ጉዟችንን በፅናት እናስቀጥላለን " ብለዋል።

የፋኦ አግሪኮላ ሜዳልያን በተሸለሙበት ወቅት የፋኦ አመራሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ እና የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተው ነበር ተብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከፋኦ ድረገፅ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia