TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አቶ አብዱ ሁሴን የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር ሆነው ተሹመዋል። ዶክተር አህመዲን መሐመድ  ደግሞ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ እና የከተማ እና መሰረተ ልማት ቢሮ ኅላፊ  ሆነው መሾማቸው ተን ከዚህ በተጨማሪ የባህር ዳር ከንቲባው ዶክተር ድረስ ሳህሉ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ሆነው…
" ኃላፊነቱን ከመቀበል ውጭ አማራጭ ባለመኖሩ ተቀብያለሁ " - አቶ አረጋ ከበደ

አዲሱ አማራ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ አረጋ ከበደ ፤ ከሹመቱ በኃላ ባሰሙት ንግግር ወደ ኃላፊነት የመጡበት ወቅት ፈታኝ እና የጋራ ትብብርን የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል።

" ክልሉ አሁን ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ ለሁሉም ግልጽ ነው " ያሉት አቶ አረጋ " ኃላፊነቱን ከመቀበል ውጭ አማራጭ ባለመኖሩ ተቀብያለሁ " ብለዋል።

በኃላፊነት ዘመናቸው ክልሉ አሁን ካለበት ዘርፈ ብዙ ችግሮች አውጥቶ የተሻለ እና የተረጋጋ ክልል ለማድረግ የሚችሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

አቶ አረጋ ከበደ በንግግራቸው የህዝቡ የዘመናት ጥያቄና ጥቅም ላይ ያልተገባ ንግግር የሚያደርጉ ቡድኖች ድርጊታቸው ከትንኮሳ አይለይም ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ አረጋ ፤ " በክልሉ የተፈጠረውን ወቅታዊ ችግር እንደአጋጣሚ በመውሰድ በክልሉ ሕዝብ የዘመናት ጥያቄ እና ጥቅም ላይ ተገቢ ያልሆነ ንግግር የሚሰነዝሩ ቡድኖች ድርጊታቸው ከትንኮሳ የማይለይ መሆኑን ማወቅ ይገባቸዋል " ብለዋል።

የክልሉ መንግሥት ሕጋዊ የፌዴራል መንግሥት ውሳኔ የሚጠብቅ እንጂ ሕዝብ የጠየቀውን ጥያቄ የሚዘነጋ እንዳልሆነ ሊገነዘቡ ይገባል ብለዋል።

የክልሉ ፕሬዜዳንት በንግግራቸው " የሚያደርጉትን ያልተገባ ንግግር ከትንኮሳ ለይተን አናያውም " ያሏቸው የትኞቹን ቡድኖች እንደሆነ #በግልፅ ስም ጠርተው አልተናግሩም።

@tikvahethiopia