TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#መግለጫ

ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ በሚገኘው የአካል ጉዳተኞች ጠቅላላ የመብቶች ጥሰት በተመለከተ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሞያ አካል ጉዳተኞች ማህበር ጋዜጣዊ መግለጫ አውጥቷል።

ማህበሩ በላከልን መግለጫ ፥ የተደራሽነት መብትን ጨምሮ የትምህርት፣ የጤና፣ የስራ እና የቅጥር መብቶች እና ሌሎች የአካል ጉዳተኞች መብቶች በየግዜው እየተጣሱ እና ለጥሰቶቹ ሀላፊነት የሚወስድ አካል ሳይኖር እንዲሁም ጥፋተኞችም ተጠያቂ ሳይደረጉ የመብት ጥሰቶቹ ተድበስብሰው በመታለፍ ላይ ናቸው ብሏል።

የአካል ጉዳተኞችን የመብት ጥሰቶችን ተከትሎ ተጠያቂነት ባለመኖሩም ጥሰት የሚፈጸምባቸው ሰዎች ሳይካሱ እየቀሩ እና ጥሰት ፈጻሚዎችም ድርጊታቸውን ትክክል አድርገው እንዲወስዱትና የመብት ጥሰቱም ያለከልካይ እንዲቀጥል ምክንያት ሆኗል ብሏል።

አሁን በተግባር እንደሚታየው የአካል ጉዳተኞች የመብት ጉዳዮች በግለሰቦች መዳፍ ላይ የተንጠለጠሉ በመሆናቸው፤ አካል ጉዳተኛው ማህበረሰብ መብቱን እንደምጽዋት እንዲጠይቅና እንዲቀበል ተገዷል ሲልም ገልጿል።

ማህበሩ ፥ በአካልጉዳተኛ ግለሰቦች ላይ ከሚፈጸሙ አይነተብዙ የመብት ጥሰቶች በተጨማሪ ከመንግስት በኩል አካል ጉዳተኞችን በቁልፍ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከአካታችነት መሻት በሚመነጭ ተነሳሽነት የማካተት ስራዎች በበቂ ሁኔታ እየተሰሩ አይደለም ብሏል።

ከሀገሪቱ ህዝብ ቁጥር ከ17.6 በላይ የሚሸፍነው አካል ጉዳተኛው ማህበረሰብ እንደሆነ ያታወቃል ያለው ማህበሩ የተለየ በጀት የማይበጀትለት መሆኑና የመብት ጥያቄ በሚያነሳበት ግዜም ፖለቲካዊ ውክልና የሌለው ማህበረሰብ መሆኑን ተከትሎ ምላሽ ሳይሰጠው በመቅረት ላይ ነው ብሏል።

ማህበሩ እየተባባሰ መጥቷል ላለቸው የመብቶች ጥሰት መፍትሄ ያለውን በዝርዝር አስቀመጧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#መግለጫ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ እንዲሁም ሚኒስትር ዴኤታዎች የፈተናውን አጀማመርና አጠቃላይ ያለውን ሂደት በሚመለከት መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው ምን አሉ ?

- በ130 ማዕከላት ከ560 ሺህ በላይ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና እየወሰዱ ነው።

- በመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ በምስራቅ ጎጃም እናርጅና እናውጋ ወረዳ ተማሪዎች ፈተናው ከመጀመሩ በፊት " #አንፈተንም " በሚል ለቀው ወጥተዋል፤ ምክንያቱን በአግባቡ አጣርተን የሚወሰደው እርምጃ ይገለፃል።

- በሐዋሳ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ የሚገኝ ድልድይ ተደርምሶ በተወሰኑ ተማሪዎች ላይ አደጋ ደርሷል። በአደጋው ጉዳት ያጋጠማቸው ተማሪዎች ህክምና እየተደረገላቸው ነው፤ ተማሪዎቹ ካገገሙ በኋላ ፈተናውን እንዲወስዱ ይደረጋል።

- ከተጠቀሱት (#ሀዋሳ እና #መቅደላ_አምባ) አካባቢዎች #በስተቀር በሌሎች ትምህርት ቤቶች ፈተናው በሰላምና በተረጋጋ መልኩ እየተሰጠ ነው።

#ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መግለጫ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ፤ በተቋሙ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ላይ የተፈጸመውን ህገ-ወጥ እስር አስመልክቶ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

ኢሰመጉ በመግለጫው ፥ መንግስት በአራት የኢሰመጉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ላይ ህገ-ወጥ እስር የፈጸሙ፣ እንዲፈጸም ትዕዛዝ በሰጡ እና በአስቸኳይ ከእስር እንዳይለቀቁ ባደረጉ የፖሊስ አባላት እና አመራሮች ላይ ተገቢውን ምርመራ በማድረግ በህግ ተጠያቂ እንዲያደርግ አሳስቧል።

በተጨማሪ መንግስት ተቀዳሚ ሃላፊነቱ ሰብዓዊ መብቶችን ማክበር፣ ማስከበር እና ማሟላት አንደሆነ በመረዳት በተቃራኒው ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ በሚሰሩ አንደ ኢሰመጉ ባሉ ተቋማት ላይ የሚፈጽማቸውን ጫናዎች፣ ዛቻዎች፤ ማስፈራራቶች፣ ማንገላታቶች፣ ማዋከቦች፣ እስሮችና መሰል ጥሰቶችን መፈጸም እንዲያቆም አስገንዝቧል።

ኢሰመጉ ከባለሙያዎቹ ተወስደው በፖሊስ እጅ የሚገኙ የተለያዩ ሰነዶች መኖራቸውን አመልክቶ ይህ በፖሊስ እጅ ላይ የሚገኙ ሰነዶች ጉዳይ እደሚያሳስበው ገልጿል።

መንግስት ወደፊት መሰል ከህግ አግባብ ውጪ የሆኑ አስሮች እና “ጫናዎችን እንዳይፈጽም ይህንን ድርጊት በሚያደርጉ ስልጣናቸውን አላግባብ በሚጠቀሙ አካላት ላይ ተገቢውን ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድም ኢሰመጉ በመግለጫው አሳስቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ካህኑን ማን ገደላቸው ? " ኃይሌ ጋርመንት " የሁርሲሳ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ቀዳሽ ካህን ቀሲስ ዐባይ መለስ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት በተፈፀመባቸው ጥቃት ተገድለዋል። ካህኑን የሚያውቋቸው አገልጋዮች /ምዕመናን  ስለነበረው ሁኔታ / ስለጥቃቱ ምን አሉ ? (ለማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከተናገሩት የተወሰደ) ቃላቸውን የሰጡ ምዕመን አንድ ፦ " ትላንት/መጋቢት…
#መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶኮስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ፤ መንግስት የቄስ ዓባይ መለሰን ገዳዮች ተከታትሎ ለፍርድ ያቅርብ አለ።

ሀገረ ስብከቱ በሰጠው መግለጫ ፤ " መንግሥት የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ በመሆናቸው ምክንያት በአሰቃቂ ሁኔታ በመንገድ ላይ ተደብድበው ሕይወታቸው እንዲያልፍ የተደረጉት የቄስ ዐባይ መለሰ ገዳዮችን ተከታትሎ ለፍርድ ያቅርብ " ብሏል።

አክሎም ፤ " ችግሩን ከሥር ከመሠረቱ በመፍታት የአገልጋዮችንና የምእመናን መብት እንዲያስከብር " ሲል ጠይቋል።

ከዚህ ባለፈ በሸገር ከተማ አስተዳደር አብያተ ክርስቲያናትን የማፍረስ ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑን በመግለፅ ይህ ድርጊት በአስቸኴይ እንዲቆም እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።

እስካሁን የፈረሱትን አብያተ ክርስቲያናት ቦታ ተመላሽ እንዲያደርግ እና የፈረሰውን ቤተ ክርስቲያንም በራሱ ወጪ እንዲያሠራ እንዲደረግ ሀገረ ስብከቱ ጠይቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መግለጫ : " የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " ሰኞ በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ በተመሳሳይ ሰዓት ይካሄዳል።

ይህንን አስመልክቶ የተሰጠው
መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

የዘንድሮው የእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads በአዲስ አበባ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል (ቦሌ መድኃኔዓለም) ፤ በድሬዳዋ ደግሞ ለገሀር አደባባይ ብቻ ነው የሚካሄደው።

(መግለጫውን ያንብቡ)

@tikvahethiopia