TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.13K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ምርጫ ሁለተኛው ዙር ውጤት ፦ በሁለተኛው ዙር የቀድሞ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ አንደኛ አሁን ሶማሊያን በፕሬዜዳንትነት እየመሩ ያሉት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ሁለተኛ ሆነው አጠናቀዋል። እንዲሁም ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ሶስተኛ ፤ ሀሰን አሊ ኻይሬ አራተኛ ሆነው የ2ኛውን ዙር የምርጫ ፉክክር አጠናቀዋል። የምርጫው ውጤት በቁጥር ፦ 👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 110 👉 ሞሀመድ…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ በሞቃዲሾ ካራን እና አብዲአዚዝ አካባቢዎች በደስታ ተኩስ እሩምታ እየተናጡ ናቸው።

አካባቢዎቹን በተኩስ እሩምታ እየናጡ የሚገኙት በሶማሊያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለ3ኛውና የመጨረሻ ዙር የደረሱት የሀሰን ሼክ ሞሐመድ ደጋፊዎች ናቸው ተብሏል።

በመጨረሻውና ሶስተኛው ዙር የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ከወቅቱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ጋር ይፎካከራሉ።

የመጨረሻው የምርጫ ውጤት በሶማሊያ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ቀንድ በጉጉት እየተጠበቀ ነው።

በሶስተኛው ዙር ከሁለት አንዱ 165 ድምፅ ያገኘው ምርጫውን በድል ያጠናቅቃል፤ ቀጣዩ የሶማሊያ ፕሬዜዳንትነትም ይሆናል።

ፈርማጆ አልያም ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ ማን ቀጣዩ የጎረቤት ሀገር ፕሬዝዳንት ይሆናል ? የሶስተኛው ዙር ምርጫ ምላሽ ይሰጠናል።

Credit : Morad

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቪድዮ ፦ በሞቃዲሾ ካራን እና አብዲአዚዝ አካባቢዎች በደስታ ተኩስ እሩምታ እየተናጡ ናቸው። አካባቢዎቹን በተኩስ እሩምታ እየናጡ የሚገኙት በሶማሊያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለ3ኛውና የመጨረሻ ዙር የደረሱት የሀሰን ሼክ ሞሐመድ ደጋፊዎች ናቸው ተብሏል። በመጨረሻውና ሶስተኛው ዙር የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ከወቅቱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ጋር ይፎካከራሉ። የመጨረሻው የምርጫ…
#Update

በሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ የመጨረሻው ዙር የድምፅ አሰጣጥ ተጠናቋል።

በቀጣይ የድምፅ ቆጠራው ይካሄዳል።

በመጨረሻው ዙር ምርጫ ፈርማጆ አልያም ደግሞ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ፉክክሩን በድል ያጠናቅቃሉ።

ፈርማጆ ካሸነፉ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሆነው ዳግም ይመረጣሉ ፤ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ካሸነፉ ከፈርማጆ በፊት የነበሩበትን የፕሬዜዳንትነት መንበር በመረከብ ሀገራቸውን ዳግም የመምራት እድልን ያገኛሉ።

#ማስታወሻ ፦ የሁለተኛው ዙር ውጤት ፦

👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 110

👉 ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 83

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ የመጨረሻው ዙር የድምፅ አሰጣጥ ተጠናቋል። በቀጣይ የድምፅ ቆጠራው ይካሄዳል። በመጨረሻው ዙር ምርጫ ፈርማጆ አልያም ደግሞ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ፉክክሩን በድል ያጠናቅቃሉ። ፈርማጆ ካሸነፉ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሆነው ዳግም ይመረጣሉ ፤ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ካሸነፉ ከፈርማጆ በፊት የነበሩበትን የፕሬዜዳንትነት መንበር በመረከብ ሀገራቸውን ዳግም የመምራት እድልን ያገኛሉ።…
#ሰበር_ዜና

የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ በድጋሚ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሆነው ተመረጡ።

ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የአሁኑን የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብድላሂ ፈርማጆን እጅግ ፉክክር በተሞላበት ሶስት ዙር የምርጫ ሂደት አሸንፈዋቸዋል።

የመጨረሻ ውጤት ፦

👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 214 ድምፅ
👉 ሞሐመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 110 ድምፅ

3 ድምፅ ዋጋ ቢስ ሆኗል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሰበር_ዜና የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ በድጋሚ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሆነው ተመረጡ። ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የአሁኑን የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብድላሂ ፈርማጆን እጅግ ፉክክር በተሞላበት ሶስት ዙር የምርጫ ሂደት አሸንፈዋቸዋል። የመጨረሻ ውጤት ፦ 👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 214 ድምፅ 👉 ሞሐመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 110 ድምፅ 3 ድምፅ ዋጋ ቢስ ሆኗል። @tikvahethiopia
#BREAKING

የሶማሊያ ፌደራል ፓርላማ ሀሰን ሼክ ሞሀመድን የሀገሪቱ 10ኛ ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።

አዲሱ ፕሬዜዳንት እ.ኤ.አ. ከመስከረም 2012 እስከ የካቲት 16 / 2017 ድረስ በፕሬዝዳንትነት አገልግለዋል።

ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ተሰናባቹን ፕሬዝዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆን በማሸነፍ በሶማሊያ ታሪክ ለሁለት ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡ የመጀመሪያው ሰው መሆን ችለዋል።

ምንጭ፦ የሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የሶማሊያ ፌደራል ፓርላማ ሀሰን ሼክ ሞሀመድን የሀገሪቱ 10ኛ ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል። አዲሱ ፕሬዜዳንት እ.ኤ.አ. ከመስከረም 2012 እስከ የካቲት 16 / 2017 ድረስ በፕሬዝዳንትነት አገልግለዋል። ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ተሰናባቹን ፕሬዝዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆን በማሸነፍ በሶማሊያ ታሪክ ለሁለት ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡ የመጀመሪያው ሰው መሆን ችለዋል። ምንጭ፦ የሶማሊያ…
#SOOMAALIYA 🇸🇴

አጫጭር ጉዳዮች ፦

➡️ አዲሱ ሶማሊያ ፕዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ዳግም ፈርማጆን አሸንፈው ፕሬዜዳንት ሆነው ከተመረጡ በኃላ ሀገራቸው ሰላም የሰፈነባትና ከዓለም ጋር ሰላም ያላት ሀገር አደርጋታለሁ ሲሉ ቃል ገብተዋል።

➡️ የቀድሞ ፕሬዜዳንት መሃመድ አብድላሂ ፈርማጆ ለአዲሱ ፕሬዜዳንት እንኳን ደስ ያልዎት መልዕክት አስተላልፈዋል። ፈርማጆ " ወንድሜ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ 10ኛው የሀገራችን ፕሬዜዳንት ሆነው በመመረጦ እንኳን ደስ ያልዎት " ያሉ ሲሆን መላው ሶማሊያውያን ለአዲሱ ፕሬዜዳንት ድጋፋቸውን እንዲሰጡና ለስኬታቸው እንዲፀልዩ ጥሪ አቅርበዋል። ምርጫው በሰላም እንዲጠነቀቅ ላደረጉ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል።

➡️ ለአዲሱ ፕሬዜዳንት የተለያዩ ሀገራት መሪዎች የእንኳን ደስ ያልዎት መልዕክት እያስተላለፉ ይገኛል። መልዕክታቸው ካስተላለፉት አንዱ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ዐቢይ አህመድ ሲሆኑ " ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ በድጋሚ የሶማሊያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሆነው በመመረጥዎ እንኳን ደስ ያለዎት ለማለት እወዳለሁ " ብለዋል። አክለውም " የጋራ በሆኑ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን እንደምንሠራ እምነቴ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

➡️ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለአዲሱ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት የእንኳን ደስ ያልዎት መልዕክት አስተላልፏል።

➡️ በኢትዮጵያ የሶማሌ ክልላዊ መንግስት ፕሬዜዳንት አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ለአዲሱ ፕሬዝዳንት እንኳን ደስ ያልዎት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በስልጣን ዘመናቸው ስኬትን ተመኝተዋል። በሌላ በኩል የቀድሞው ፕሬዜዳንት በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል ያለውን የወንድማማችነት ግንኙነት እንዲጠናከር ላደረጉት አስተዋፆ አመስግነዋቸዋል።

@tikvahethiopia
#Amhara #BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እና በአማራ ክልል ወረዳዎች እንደቀድሞው ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲኖር መግባባት ላይ መደረሱ ተገለፀ።

አራት ዓመታትን ያስቆጠረው የመተከል ዞን የሰላም መደፍረስ ወደ ፍፁም ሰላም እንዲመለስ በመተከል እና በአማራ ክልል አጎራባች ወረዳዎች በትናንትናው ዕለት የምክክር መድረክ ተካሂዷል ።

የጓንጓ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ መኮንን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ በሰጡት ቃል የትላንቱን የምክክር መድረክ " ከሁሉም የመተከል ዞን ወረዳዎች እና የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ወረዳዎች የተውጣጡ የእምነት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የፖለቲካ አመራሮች እና በአጠቃላይ ከ500 በላይ እንግዶች ተሳትፈውበታል " ብለዋል።

ኃላፊው ፥ ወረዳዎቹ ከዚህ በፊት ብዙ ተፈናቃዮችን ያስተናግዱ እንደነበር እና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የችግሩ ገፈጥ ቀማሽ እንደነበሩ ገልፀው ፤ አሁን ላይ የነበረውን ግጭት ወደ ጎን ትተው #ለእርቅ መስማማታቸውን ገልፀዋል።

ከሁለቱም ወገን እንደቀድሞው ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲኖር መግባባት ላይ መደረሱ የተነገረ ሲሆን በቦታው ያሉ ልዩ ሀይሎች፣ መከላከያን ጨምሮ እንዲሁም ጥምር የፌዴራል ፖሊስ ሃይል ሀላፊነት እንዳለባቸው ተነስቷል።

ከዚህ በፊት ሸፍተው በጫካ የነበሩ የጉሙዝ ብሔረሰብ ተወላጆች እጃቸውን በመስጠት ትጥቅ ፈትተው፤ በባህላቸው መሠረት ዕርቅ ፈፅመው ከማህበረሰቡ ጋር መቀላቀላቸውን የጓንጓ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ መኮንን ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።

Credit : Ethio FM 107.8

@tikvahethiopia
#አብን #አቶ_ክርስቲያን_ታደለ

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) አመራሩና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ፤ የአብን ጉዳይ ያገባናል የሚሉ አመራሮች ፣ አባላት፣ ደጋፊዎች ማዋከብ እና አፈና እየደረሰባቸው መሆኑን በመግለፅ ይህ ድርጊት በአስቸኳይ መቆም ይኖርበታል አሉ።

ደርሷል ስላሉት ማዋከብ እና አፈና ፣ መቼ ? የት ? እንዴት ? እነማንን ? ስለሚሉ ዝርዝር ጉዳዮችን በግልፅ የሰጡት ማብራሪያ የለም።

አቶ ክርስቲያን በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፥ " አብን ዝቅ ሲል የአባላቱና ደጋፊዎች፥ ከፍ ሲልም የንቅናቄውን ዓላማ የሚጋሩ ኢትዮጵያውያን ንብረት መሆኑን ገዥው የብልጽግና ፓርቲና ያዋቀረው መንግስት በውል ሊያውቁት ይገባል " ብለዋል።

አክለውም " የተፎካካሪ ፓርቲ የውስጥ ጉዳይ የፓርቲው አባላትና በየደረጃው ያለው ሕጋዊ መዋቅር ጉዳይ ነው። የአብን ጉዳይ ያገባናል የሚሉ አመራሮችን፣ አባላትንና ደጋፊዎችን ማዋከቡ በአስቸኳይ መቆም ይኖርበታል " ሲሉ ገልፀዋል።

" እየተደረገ ያለው አፈናና ውርክቢያ ማንንም አይጠቅምም፤ በተለይ ደግሞ ገዥውን ፓርቲ አይጠቅምም " ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

አቶ ክርስቲያን ፤ " አብን በሕዝብ ምርጫ በራሱ መንግስት ለመሆን የሚታገል ፓርቲ እንጂ የገዥው ፓርቲ ሁሉንም የመጠቅለል ስካር መደገፊያ ምርኩዝ አይደለም " ሲሉ ፅፈዋል።

አቶ ክርስቲያን ታደለ ከጥቂት ቀናት በፊት የፓርቲያቸው ስራ አስፈፃሚ ከህገደንብ እና አሰራር ውጭ በመሆን አፍራሽ ድርጊቶችን እና የዲሲፕሊን ጥሰቶችን ፈፅመዋል በሚል የመጨረሻ ያለውን ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸው እንደነበር ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ አቶ ክርስቲያን ፤ መሰል ውሳኔዎችን ለመወሰን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሥልጣን የሌለው መሆኑን መግለፃቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
#Oromia #ICRC

በግጭት ምክንያት ተፈናቅለው የነበሩ እና በቅርቡ በምስራቅ ወለጋ፣ ጉቶ ጊዳ ወረዳ፣ አለልቱ ቀበሌ ወደሚገኘው መኖሪያ ስፍራቸው ለተመለሱ 800 ግለሰቦች መሰረታዊ የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉን የዓለም ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) አስታውቋል።

ድጋፍ ከተደረጉት ቁሳቁሶች መካከል ሶላር የእጅ ባትሪዎች ፣ ጀሪካኖች ፣ የማዕድ ቤት እቃዎች ፣ ምንጣፎች ፣ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች እና መጠለያ እንደሚገኙበት ከድርጅቱ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#EOTC

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜያት ከሚካሄዱት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያት አንዱ የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የፊታችን ረቡዕ ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ/ም ከጧቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል።

ይህ ጉባኤ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ርእሰ መንበርነት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት ካሉ አህጉረ ስብከት በሚመጡ ብፁዓን አበው ሊቀነ ጳጳሳት ተሰብሳቢነት የሚከናወን እንደሆነ ተገልጿል።

@tikvahethiopia