TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#ጥንቃቄ

በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ሦስት መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ እናዳይጠቀም ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ጥራታቸው፣ ደህንነታቸውና ፈዋሽነታቸው ያልተረጋገጠ እና በጤና ላይ ከቀላል እስከ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ፦

👉 Titan gel፣
👉 Mara Moja
👉 Relief የተባሉ መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አሳስቧል።

መድኃኒቶቹ በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ያልተመዘገቡና በህጋዊ መንገድም ወደ አገር ዉስጥ ያልገቡ ናቸው።

Titan gel የተባለው መድኃኒት በሐኪም ብቻ በመታዘዝ ጥቅም ላይ መዋል ያለበት ሲሆን ነገር ግን በድብቅና በህገወጥ መንገድ ገበያ ላይ አንደሚገኝ ታውቋቃ።

መድኃኒቶቹን ማንኛውም ግለሰብ ወይም አካል በህጋዊ ተቋማት ሆነ በህገወጥ መንገድ ሲያገኛቸው እንዳይጠቀማቸውና በባለስልጣን መስሪያቤቱ ነጻ የስልክ መስመር 8482 በአቅሪያባቸው ለሚገኙ የክልል ተቆጣጠሪዎች ወይም ለጸጥታ አካላት በመጠቆም አስፈላጊዉን ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል።

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሚያዚያ የቤንዚን እና የናፍጣ ምርቶች ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፥ የሚያዚያ ወር የቤንዚን እና የናፍጣ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በመጋቢት ወር ላይ ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል አስታውቋል። የአውሮፕላን ነዳጅ ፣ የከባድ ጥቁር ናፍጣ እና የቀላል ጥቁር ናፍጣ የመሸጫ ዋጋ በዓለም አቀፍ ዋጋ መሰረት ተሰልቶ የመጣው ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ መወሰኑን ኤፍ ቢ…
#የነዳጅ_ዋጋ_ጭማሪ

ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።

በዚህም ፦

👉 ቤንዚን በሊትር 36 ብር ከ87 ሳንቲም ፣
👉 ነጭ ናፍጣ በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ኬሮሲን በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 52 ብር ከ45 ሳንቲም፣
👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 51 ብር ከ78 ሳንቲም
👉 የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 78 ብር ከ87 ሳንቲም እንዲሆን መወሰኑን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

ዝርዝሩን ያንብቡ : https://telegra.ph/ETHIOPIA-05-07

@tikvahethiopia
ዲቪ (DV) 2023 ይፋ ሆኗል።

የ2023 ዲቪ ሎተሪ ዛሬ ማታ ይፋ የሆነ ሲሆን ሞልታችሁ ስትጠባበቁ የነበራችሁ በሙሉ የዲቪ ውጤታችሁን በዚህ ሊንክ https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል።

@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የነዳጅ ሰልፍ በአዲስ አበባ ከተማ !

ነዳጅ ለማግኘት ረጅም የሆኑ ሰልፎችን መጠበቅ ከተጀመረ ሰነባብቷል። ይህ ችግር በርካታ ጊዜያት ተደጋግሞ ቢነሳም መፍትሄ አልተገኘለትም።

በዚህ ምክንያት ዜጎች ሰዓታቸውን በነዳጅ ሰልፍ ሳይባክን ሰርተው ለመብላት የዕለት ገቢያቸውን ለማግኘት ፈተና እየሆነባቸው ነው።

ተሽከርካሪ ያላቸው ሰራተኞችም ስራቸውን እየተው ለነዳጅ እየተሰለፉ በመሆኑ ስራቸው እየተበደለ ነው።

ነዳጅ ላይ የዋጋ ማስተካከያ ቢደረግም በተባለው ዋጋ ለማግኘት እንኳን ፈተና ሆኗል። የዓለም ነዳጅ ዋጋ ንረት እንደተጠበቀ ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ እውነት በቂ ነዳጅ ስለሌለ/ስለማይገባ ነው ? ወይስ ያለውን በአግባቡ የማስተዳደር ችግር ? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።

በክልል ከተሞች ማደያዎች ነዳጅ የለም ይላሉ ፤ ህገወጥ በሆነ መልኩ በየመንገዱ፣ በየሱቁ ላይ ሲሸጥ ይታያል ፤ ማደያዎች ለሊት ላይ በጄሪካን ለተለያዩ አካላት እንደሚቀዱ ነው የሚነገረው።

ይህን ለማስቆም ሰፊ ጥረት ሲደረግ አይታይም፤ ምክንያቱም ችግሩ ወራትን ስላስቆጠረ በዚህ ህገወጥ ድርጊት የሚሳተፉ እና እጃቸው ያለበት ብዙ አካላት እንዳሉ ግን እሙን ነው።

ይህ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ችግር ልጓም ካልተበጀለት የሚፈጥረው ቀውስ ከፍተኛ ነውና ትኩረትን ይሻል።

@tikvahethiopia
" የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት በሚያዚያ ወር 12.8 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ተደርጓል " - የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ፤ የዓለም ነዳጅ ዋጋ ባሻቀበበት በዚህ ወቅት መንግሥት በሚያዚያ ወር ብቻ የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት ከ12.8 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ ማድረጉ ገልጿል።

ይህን የተገለፀው ከቀናት በፊት የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ስለ አዲሱ የታለመ የነዳጅ ድጎማና ዋጋ ማሻሻያ በተመለከተ ለሚዲያ አካላት በተዘጋጀ መድረክ ላይ ነው።

እስከ ሚያዚያ ወር ማጠናቀቂያ ድረስ በአንድ ወር ብቻ ከ12.8 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ድጎማ መደረጉ ታውቋል።

ከሐምሌ 2014 ዓ.ም. አንስቶ በጠቅላላው ባለፉት አሥር ወራት በመንግሥት የተደረገው የተመዘገበ የድጎማ መጠን ከ73.5 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ሪፖርተር ጋዜጣ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።

https://telegra.ph/Reporter-05-08

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና !

በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ኮሌጅ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል HCP በተባለ ግብረሰናይ ድርጅት እገዛ 500 የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና /CATARACT SURGERY/ ከሰኔ 6 እስከ ሰኔ 12/2014 ዓ.ም ለማድረግ አስቧል፡፡

ይህን ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ በግንቦት ወር ባሉት ቅዳሜና እሁድ ቀናቶች ማለትም (ግንቦት 6፣ 7፣ 13፣ 14፣20፣ 21፣27 ፣28 ) ይካሄዳል።

በኮሌጁ የስልክ አገልግሎት 976 በመደወል ለቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ ቀጠሮ ማስያዝ ይቻላል።

#ማሳሰቢያ ፡- በስልክ ቀጠሮ ያልተሰጠዉ ታካሚ ቅድመ ምርመራም፣ ልየታም ይሁን ምዝገባ ማድረግ አይችልም ተብሏል።

(ውድ ቤተሰቦቻችን መልዕክቱን አጋሩ)

@tikvahethiopia
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ፦

🛢️ከአንድ አመት በፊት 👉 68 የአሜሪካ ዶላር
🛢️አሁን 👉 113 የአሜሪካ ዶላር

ለነዳጅ ዋጋ እንዲህ መናር ሩስያ እና ዩክሬን የገቡበት እና ዛሬም ድረስ መቋጫ ያላገኘው ጦርነት ዋነኛው ሲሆን ጦርነቱ በአጠቃላይ ዓለምን አናግቷል ማለት ይቻላል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሌተናል_ኮሎኔል_ፍሥሐ_ደስታ በድረግ ዘመነ መንግስት ኢትዮጵያን በምክትል ፕሬዝዳንትነት የመሩት ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ደስታ በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የቀድሞው መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃ/ማሪያም ምክትል በመሆን የኢሕዲሪ ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ደስታ፣ ኢሕአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ለ20 ዓመታት ያህል በእስር ቆይተዋል። ቤተሰቦቻቸው ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ፤…
ፎቶ ፦ ዛሬ የቀድሞ የኢትዮጵያ ምክትል ፕሬዜዳንት ሌተናል ኮለኔል ፍስሐ ደስታ የቀብር ሥነ ስርዓት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።

በቀብር ስነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የቀድሞ የስራ ባልደረቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተው ነበር።

ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ በህይወት ሳሉ " አብዮቱ እና ትዝታዬ " በተሰኛው መፃፍ ላይ ከፃፉት ፦

" ቂምን ቋጥሮ ቁርሾን ተሸክሞ ዴሞክራሲና ሀገር ለመገንባት ፣ እድገትን እና ብልፅግና ለማምጣት የማይታሰብ ነው። በመሆኑም በዚያ አስከፊ የርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ያለፍነው ሁሉ የታሪኩ አካልና የትውልዱ አባል በመሆናችን የታመቁ ቅራኔዎችን ከማራገብ ይልቅ ያለፈውን ታሪካችንንና ያለንበትን ሁኔታ በቅንነትና በንፁህ ሕሊና በመገምገም ይቅር ለታሪክና ለትውልድ መባባል አለብን "

▪️ሌተናል ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ ከአባታቸው ብላታ ደስታ ወልደማርያም ከእናታቸው ወ/ሮ ሕርይተሥላሴ ትኩዕ ሚያዚያ 13/1933 ትግራይ ዓድዋ ከተማ ነው የተወለዱት ፤ አርብ ሚያዚያ 28/2014 ዓ. ም. እኩለ ሌሊት በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ ባለትዳርና የ1 ልጅ አባት ነበሩ▪️

@tikvahethiopia