TIKVAH-ETHIOPIA
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት.pdf
Amnesty International & HRW .pdf
22.5 MB
#ሪፖርት
ከጥቂት ሳምንታት በፊት የትግራይ ኃይሎች በአማራ ክልል ገብተው በቆዩባቸው ወቅት የፈፀሟቸው ከጦር ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ ወንጀሎች ዙሪያ ሰፋ ያለ ሪፖርት ያቀረበው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ አዲስ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከሂውማን ራይትስ ዎች ጋር በመተባበር ላለፉት 15 ወራት የሰራውን ሪፖርት ነው ይፋ ያደረገው።
ዛሬ ይፋ የሆነው ሪፖርት ፥" 'ከዚህ ምድር እናስወግዳችኋለን'፡ በሰብዓዊነት የሚፈጸም ወንጀል እና የዘር ማጽዳት በኢትዮጵያዋ ምዕራብ ትግራይ ዞን" የተሰኘ ነው።
ይህ ሪፖርት በምዕራብ ትግራይ የትግራይ ተወላጆች ላይ ተፈፀሙ የተባሉ በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በስፋት ይዳስሳል።
ከጦርነቱ መቀስቀስ ጀምሮ የአማራ ኃይሎች እና ባለስልጣናት በምዕራብ ትግራይ ባሉ የትግራይ ተወላጆች ላይ ከጦር ወንጀል እና በሰብዓዊነት ላይ ከሚፈጸሙ ወንጀሎች ጋር የሚስተካከሉ መጠነ ሰፊ ወንጀሎች ፈጽመዋል ብሏል ሪፖርቱ።
ሪፖርቱ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳበት ምዕራብ ትግራይ የሚንቀሳቀሱት የአማራ ልዩ ኃይል እንዲሁም ሚሊሻዎች "የዘር ማጽዳት እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን" መፈጸማቸውን ገልጿል።
የዛሬው ሪፖርት በጦርነቱ የመጀመሪያ ጥቂት ወራት ውስጥ የተፈጸሙ ጥፋቶችን ጭምር የዳሰሰ ሲሆን የትግራይ ሚሊሻዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪ ሲቪሎች በ ማይካድራ ከተማ አካባቢው ነዋሪ በሆኑ እና ለቀን ስራ በመጡ የአማራ ተወላጆች ላይ "የጦር ወንጀሎችን" መፈጸማቸውን አስታውሷል።
በሌላ በኩል ሁለቱ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በአካባቢው ያለውን አስከፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ለማስቆም በአፍሪካ ሕብረት የሚመራ ሰላም አስከባሪ ኃይል እንዲሰማራ ጠይቀዋል።
(ሙሉው 240 ገፅ ሪፖርት ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ከጥቂት ሳምንታት በፊት የትግራይ ኃይሎች በአማራ ክልል ገብተው በቆዩባቸው ወቅት የፈፀሟቸው ከጦር ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ ወንጀሎች ዙሪያ ሰፋ ያለ ሪፖርት ያቀረበው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ አዲስ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከሂውማን ራይትስ ዎች ጋር በመተባበር ላለፉት 15 ወራት የሰራውን ሪፖርት ነው ይፋ ያደረገው።
ዛሬ ይፋ የሆነው ሪፖርት ፥" 'ከዚህ ምድር እናስወግዳችኋለን'፡ በሰብዓዊነት የሚፈጸም ወንጀል እና የዘር ማጽዳት በኢትዮጵያዋ ምዕራብ ትግራይ ዞን" የተሰኘ ነው።
ይህ ሪፖርት በምዕራብ ትግራይ የትግራይ ተወላጆች ላይ ተፈፀሙ የተባሉ በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በስፋት ይዳስሳል።
ከጦርነቱ መቀስቀስ ጀምሮ የአማራ ኃይሎች እና ባለስልጣናት በምዕራብ ትግራይ ባሉ የትግራይ ተወላጆች ላይ ከጦር ወንጀል እና በሰብዓዊነት ላይ ከሚፈጸሙ ወንጀሎች ጋር የሚስተካከሉ መጠነ ሰፊ ወንጀሎች ፈጽመዋል ብሏል ሪፖርቱ።
ሪፖርቱ የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳበት ምዕራብ ትግራይ የሚንቀሳቀሱት የአማራ ልዩ ኃይል እንዲሁም ሚሊሻዎች "የዘር ማጽዳት እንዲሁም በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን" መፈጸማቸውን ገልጿል።
የዛሬው ሪፖርት በጦርነቱ የመጀመሪያ ጥቂት ወራት ውስጥ የተፈጸሙ ጥፋቶችን ጭምር የዳሰሰ ሲሆን የትግራይ ሚሊሻዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪ ሲቪሎች በ ማይካድራ ከተማ አካባቢው ነዋሪ በሆኑ እና ለቀን ስራ በመጡ የአማራ ተወላጆች ላይ "የጦር ወንጀሎችን" መፈጸማቸውን አስታውሷል።
በሌላ በኩል ሁለቱ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በአካባቢው ያለውን አስከፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ለማስቆም በአፍሪካ ሕብረት የሚመራ ሰላም አስከባሪ ኃይል እንዲሰማራ ጠይቀዋል።
(ሙሉው 240 ገፅ ሪፖርት ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ICHREE.pdf
233.1 KB
#ሪፖርት
በኢትዮጵያ ጦርነት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እንዲያጣራ በተመድ የተቋቋመው የሰብዓዊ መብቶች የባለሙያዎች ቡድን (ICHREE) 19ኝ ገፆች ያሉት የመጀመሪያ ግኝት ሪፖርት።
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ጦርነት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እንዲያጣራ በተመድ የተቋቋመው የሰብዓዊ መብቶች የባለሙያዎች ቡድን (ICHREE) 19ኝ ገፆች ያሉት የመጀመሪያ ግኝት ሪፖርት።
@tikvahethiopia
FDRE Inter-Ministerial Taskforce .pdf
771.8 KB
#ሪፖርት
የኢፌዴሪ የሚኒስትሮች ግብረ-ኃይል የወንጀል ምርመራ እና ክስ ዝግጅት ኮሚቴ በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረ ግጭት የተፈጸሙ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና ወንጀሎችን በተመለከተ የተከናወኑ የወንጀል ምርመራ ስራዎች የመጀመሪያ ዙር ሪፖርት በትላንትናው ዕለት ይፋ አድርጓል።
@tikvahethiopia
የኢፌዴሪ የሚኒስትሮች ግብረ-ኃይል የወንጀል ምርመራ እና ክስ ዝግጅት ኮሚቴ በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረ ግጭት የተፈጸሙ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና ወንጀሎችን በተመለከተ የተከናወኑ የወንጀል ምርመራ ስራዎች የመጀመሪያ ዙር ሪፖርት በትላንትናው ዕለት ይፋ አድርጓል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጋምቤላ ክልል ፡ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ከሕግ አግባብ ውጭ የተፈጸሙ የኃይል እርምጃዎች ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በጋምቤላ ከተማ፣ ጋምቤላ ክልል ከጠዋት እስከ ምሽት የቀጠለ ግጭት እና የፀጥታ እና የደኅንነት ችግርን ተከትሎ ለአንድ ቀን የከተማዋ የመንግሥት አገልግሎቶች፣ የንግድ እንቅስቃሴዎች እና ሌሎችም አገልግሎቶች ተቋርጠው መዋላቸው ይታወሳል። ጥቃቱ በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (በተለምዶ ኦነግ…
በጋምቤላ_ከተማ_በክልሉ_የጸጥታ_ኃይሎች፣_በኦነግ_ሸኔ_እና_የጋነግ_ታጣቂዎች_የተፈጸሙ_የሰብአዊ_መብቶች.pdf
235.3 KB
#ሪፖርት
ዛሬ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጋምቤላ ክልል፣ ጋምቤላ ከተማ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ኮሚሽኑ ይፋ ያደረገው ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች፣ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሸኔ) በጋምቤላ ነጻነት ግንባር (ጋነግ) መካከል የተደረገው ውጊያን ተከትሎ ከሰኔ 7 እስከ 9 ቀን 2014 ዓ/ም በክልሉ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ታጣቂ ኃይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙ ግድያዎችን፣ የአካል ጉዳቶችን፣ የንብረት ጉዳት እና ዘረፋዎችን በተመለከተ ነው።
ከሰኔ 20 እስከ ነሐሴ 16 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ምርመራ ያደረገው ኢሰመኮ ዛሬ ይፋ ያደረገው ባለ 13 ገጽ ሪፖርት ነው።
(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ዛሬ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጋምቤላ ክልል፣ ጋምቤላ ከተማ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ኮሚሽኑ ይፋ ያደረገው ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም በክልሉ የጸጥታ ኃይሎች፣ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ ኦነግ ሸኔ) በጋምቤላ ነጻነት ግንባር (ጋነግ) መካከል የተደረገው ውጊያን ተከትሎ ከሰኔ 7 እስከ 9 ቀን 2014 ዓ/ም በክልሉ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ታጣቂ ኃይሎች በተወሰዱ እርምጃዎች በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙ ግድያዎችን፣ የአካል ጉዳቶችን፣ የንብረት ጉዳት እና ዘረፋዎችን በተመለከተ ነው።
ከሰኔ 20 እስከ ነሐሴ 16 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ምርመራ ያደረገው ኢሰመኮ ዛሬ ይፋ ያደረገው ባለ 13 ገጽ ሪፖርት ነው።
(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
Report_of_the_Ethiopian_Human_Rights_Commission_EHRC_and_the_Office.PDF
1.6 MB
#EHRC #UN #ሪፖርት
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽህፈት ቤት ከሐምሌ ወር 2014 ዓ/ም - መጋቢት ወር 2015 ዓ/ም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች በሽግግር ፍትሕ ጉዳይ ላይ ከተጎጂዎችና ጉዳት ከደረሰባቸው ማኅበረሰቦች ጋር ባደረጉት ምክክር የተገኙ ግኝቶችን በተመለከተ ይፋ ያደረጉት ባለ 90 ገጽ ሪፖርት ከላይ ባለፈው ፋይል ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ጽህፈት ቤት ከሐምሌ ወር 2014 ዓ/ም - መጋቢት ወር 2015 ዓ/ም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች በሽግግር ፍትሕ ጉዳይ ላይ ከተጎጂዎችና ጉዳት ከደረሰባቸው ማኅበረሰቦች ጋር ባደረጉት ምክክር የተገኙ ግኝቶችን በተመለከተ ይፋ ያደረጉት ባለ 90 ገጽ ሪፖርት ከላይ ባለፈው ፋይል ተያይዟል።
@tikvahethiopia
2023.pdf
3.9 MB
#ሪፖርት
የሀገራትን የረሃብ ደረጃ የሚለካው የረሀብ ኢንዴክስ (GHI) ሪፖርት ይፋ ተደርጓል።
በዚህም #ኢትዮጵያ 26.2 በመቶ በማስመዝገብ ከ125 ሀገራት ከመጨረሻዎቹ 101ኛ ደረጃን ይዛለች።
ኢትዮጵያ በ2022 ለይ ከ121 ሀገራት ውስጥ በ27.6 በመቶ በማስመዝገብ 104ኛ ደረጃም ይዛ ነበር።
በ2023 ሪፖርት የረሃብ ልኬቱ ቀንሶ 26.2 በመቶ ተሰጥቷታል።
ሪፖርቱ በየዓመቱ ይፋ የሚደረግ ነው።
በዚህ ጥናት ላይ የሀገራትን ደረጃ ለመስጠት ከሚዳሰሱ ዋና ዋና መሰረታዊ የሚባሉ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ፤ ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሕፃናት የምግብ እጥረት ፣ ሞትና የምግብ አቅርቦት ዋነኞቹ ናቸው።
@tikvahethiopia
የሀገራትን የረሃብ ደረጃ የሚለካው የረሀብ ኢንዴክስ (GHI) ሪፖርት ይፋ ተደርጓል።
በዚህም #ኢትዮጵያ 26.2 በመቶ በማስመዝገብ ከ125 ሀገራት ከመጨረሻዎቹ 101ኛ ደረጃን ይዛለች።
ኢትዮጵያ በ2022 ለይ ከ121 ሀገራት ውስጥ በ27.6 በመቶ በማስመዝገብ 104ኛ ደረጃም ይዛ ነበር።
በ2023 ሪፖርት የረሃብ ልኬቱ ቀንሶ 26.2 በመቶ ተሰጥቷታል።
ሪፖርቱ በየዓመቱ ይፋ የሚደረግ ነው።
በዚህ ጥናት ላይ የሀገራትን ደረጃ ለመስጠት ከሚዳሰሱ ዋና ዋና መሰረታዊ የሚባሉ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ፤ ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሕፃናት የምግብ እጥረት ፣ ሞትና የምግብ አቅርቦት ዋነኞቹ ናቸው።
@tikvahethiopia
#ሪፖርት
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ዐውድ ውስጥና ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢነትና ሥጋቶችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሪፖርት አውጥቷል።
በሪፖርቱ ፦
- ከሕግ ውጭ ግድያ (በድሮን ጨምሮ) ፣ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ፤
- የዘፈቀደ፣ ሕገወጥ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፤
- እገታ
- አስገድዶ መሰወር እና ያሉበት ቦታ ሳይታወቅ አስሮ ማቆየት
- የሀገር ውስጥ መፈናቀል ... ተዳሰዋል።
° በጸጥታ መደፍረስ፣
° ከመንግሥት አካላት ተገቢውን ምላሽና ትብብር በወቅቱ ባለማግኘት
° በሌሎች ምክንያቶች ምርመራቸውና ክትትላቸው የዘገዩና የተጓተቱ በርካታ ጉዳዮችን መኖራቸው ተገልጿል።
እነዚህን ጉዳዮች በመርመርና ክትትል በማድረግ በተገቢው ጊዜ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከኮሚሽኑ የተላከለትን ዝርዝር ሪፖርት ከላይ አያይዟል፤ በጥሞና ያንብቡት።
ኢሰመኮ በግጭት ዐውድ ውስጥ እና ከዐውድ ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችንና ሥጋቶችን በአስቸኳይ ማቆም ይገባል ብሏል።
የአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎችን ጨምሮ ሁሉንም የትጥቅ ግጭቶች በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምና የሰብአዊ መብቶች መከበርን ማረጋገጥ እንደሚገባም አስገንዝቧል።
#EHRC
#Ethiopia #TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ዐውድ ውስጥና ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢነትና ሥጋቶችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሪፖርት አውጥቷል።
በሪፖርቱ ፦
- ከሕግ ውጭ ግድያ (በድሮን ጨምሮ) ፣ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ፤
- የዘፈቀደ፣ ሕገወጥ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፤
- እገታ
- አስገድዶ መሰወር እና ያሉበት ቦታ ሳይታወቅ አስሮ ማቆየት
- የሀገር ውስጥ መፈናቀል ... ተዳሰዋል።
° በጸጥታ መደፍረስ፣
° ከመንግሥት አካላት ተገቢውን ምላሽና ትብብር በወቅቱ ባለማግኘት
° በሌሎች ምክንያቶች ምርመራቸውና ክትትላቸው የዘገዩና የተጓተቱ በርካታ ጉዳዮችን መኖራቸው ተገልጿል።
እነዚህን ጉዳዮች በመርመርና ክትትል በማድረግ በተገቢው ጊዜ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከኮሚሽኑ የተላከለትን ዝርዝር ሪፖርት ከላይ አያይዟል፤ በጥሞና ያንብቡት።
ኢሰመኮ በግጭት ዐውድ ውስጥ እና ከዐውድ ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችንና ሥጋቶችን በአስቸኳይ ማቆም ይገባል ብሏል።
የአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎችን ጨምሮ ሁሉንም የትጥቅ ግጭቶች በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምና የሰብአዊ መብቶች መከበርን ማረጋገጥ እንደሚገባም አስገንዝቧል።
#EHRC
#Ethiopia #TikvahEthiopia
@tikvahethiopia