TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ዛሬ ህዳር 3/2016 ዓ.ም በመቐለ የተካሄደው የታክሲ አገልግሎት የማቆም አድማ ከማህበራቱ እውቅና ውጪ የተፈፀመና ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑን ሶስት የታክሲ ማህበራት ባወጡት መግለጫ አሳወቁ። ማህበራቱ ከሰዓት በኃላ ባሰራጩት ይፋዊ መግለጫ ፤ " ለመንግስት ያቀረብነው ጥያቄ በህጋዊ መንገድ እንዲመለስ ጥረት እያካሄድን ባለንበት ጊዜ አገልግሎት ማቋረጥ አግባብ አይደለም " ብለዋል። አድማ…
#Update
" የምንሰጠውን ምክርና ማሳሰብያ ችላ ብሎ በአድማው የሚቀጥል ባለንብረትና አሽከርካሪ ላይ #ጥብቅ_እርምጃ ይወሰዳል " - ወ/ሪት ራሄል ሃይለ
የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ በመቐለ የተደረገው የታክሲ አገልግሎት ማቋረጥና አድማ " ህጋዊ አይደለም " ብሏል።
ቢሮው ከመቐለ የትራንስፓርት ፅህፈት ቤትና ፓሊስ በጋራ ' አካሄድኩት ' ባለው ግምገማ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች ቀድም ሲል አገልግሎት ለማቋረጥና አድማ ለመምታት የሚያበቃ ቅሬታና ጥያቄ አላቀረቡም ሲል ገልጿል።
የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወ/ሪት ራሄል ሃይለ ህዳር 3/2016 ዓ.ም አመሻሽ ለሚድያ በሰጡት መግለጫ ፤ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች አገልግሎት የማቋረጥና አድማ የመምታት ደርጊቱ ችላ ተብሎ የማይታለፍ ህጋዊ እርምጃና ተጠያቂነት የሚያስከትል በመሆኑ በመገንዘብ ስራቸው ይቀጥሉ ዘንድ መክረዋል።
የመንግስት ምክርና ማሳሰብያ ችላ ብሎ በአድማ የሚቀጥል ባለንብረትና አሽከርካሪ ግን ጥብቅ እርምጃ ይወሰድበታል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ለምለም ኪሓ ፣ ህዳሴና ሓወልቲ የተባሉ የመቐለ የታክሲ ማህበራት አመራሮች በማህተም አስደግፈው ህዳር 3/2016 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ለሚድያዎች በላኩት መግለጫ ፤ አግልግሎት ማቋረጡና አድማው ከእውቅናቸው ወጪ የተደረገ ኢ-ህጋዊ ነው ማለታቸው መዘገባችን ይታወሳል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
በመቐለ ከተማ የታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች ባደረጉት አድማ ነዋሪዎች ለእንግልት እና አላግባብ ለሆነ ወጭ ተዳርገዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ ያነጋገራቸው የታክሲ ባለንብረቶች እና አሽከርካሪዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየናረ በመሄድ ላይ የሚገኘው የኑሮ ሁኔታ ፣ የመኪና እቃ መለዋወጫ መወደድ የሹፌርና የረዳት ክፍያ ገበያ ላይ ባለው ታሪፍ መሸፈን እጅግ እንደከበዳቸው ፤ ያለው ታሪፍ እንዲስተካከል ከአንድ ወር በፊት መንግሥትን በማህበራቸው በኩል ቢጠይቁም ምላሽ ስላላገኙ ወደ አድማ እንደገቡ ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
" የምንሰጠውን ምክርና ማሳሰብያ ችላ ብሎ በአድማው የሚቀጥል ባለንብረትና አሽከርካሪ ላይ #ጥብቅ_እርምጃ ይወሰዳል " - ወ/ሪት ራሄል ሃይለ
የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ በመቐለ የተደረገው የታክሲ አገልግሎት ማቋረጥና አድማ " ህጋዊ አይደለም " ብሏል።
ቢሮው ከመቐለ የትራንስፓርት ፅህፈት ቤትና ፓሊስ በጋራ ' አካሄድኩት ' ባለው ግምገማ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች ቀድም ሲል አገልግሎት ለማቋረጥና አድማ ለመምታት የሚያበቃ ቅሬታና ጥያቄ አላቀረቡም ሲል ገልጿል።
የትግራይ የትራንስፓርትና መገናኛ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወ/ሪት ራሄል ሃይለ ህዳር 3/2016 ዓ.ም አመሻሽ ለሚድያ በሰጡት መግለጫ ፤ የታክሲ ባለቤቶችና አሽከርካሪዎች አገልግሎት የማቋረጥና አድማ የመምታት ደርጊቱ ችላ ተብሎ የማይታለፍ ህጋዊ እርምጃና ተጠያቂነት የሚያስከትል በመሆኑ በመገንዘብ ስራቸው ይቀጥሉ ዘንድ መክረዋል።
የመንግስት ምክርና ማሳሰብያ ችላ ብሎ በአድማ የሚቀጥል ባለንብረትና አሽከርካሪ ግን ጥብቅ እርምጃ ይወሰድበታል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ለምለም ኪሓ ፣ ህዳሴና ሓወልቲ የተባሉ የመቐለ የታክሲ ማህበራት አመራሮች በማህተም አስደግፈው ህዳር 3/2016 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ለሚድያዎች በላኩት መግለጫ ፤ አግልግሎት ማቋረጡና አድማው ከእውቅናቸው ወጪ የተደረገ ኢ-ህጋዊ ነው ማለታቸው መዘገባችን ይታወሳል ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
በመቐለ ከተማ የታክሲ አገልግሎት ሰጪዎች ባደረጉት አድማ ነዋሪዎች ለእንግልት እና አላግባብ ለሆነ ወጭ ተዳርገዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ ያነጋገራቸው የታክሲ ባለንብረቶች እና አሽከርካሪዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየናረ በመሄድ ላይ የሚገኘው የኑሮ ሁኔታ ፣ የመኪና እቃ መለዋወጫ መወደድ የሹፌርና የረዳት ክፍያ ገበያ ላይ ባለው ታሪፍ መሸፈን እጅግ እንደከበዳቸው ፤ ያለው ታሪፍ እንዲስተካከል ከአንድ ወር በፊት መንግሥትን በማህበራቸው በኩል ቢጠይቁም ምላሽ ስላላገኙ ወደ አድማ እንደገቡ ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ የዲጂታል ባንክ አግልግሎት ሙሉ በሙሉ መጀመሩን ገለጸ። ባንኩ ፤ በሲስተም ችግር ምክንያት ፦ - በቅርንጫፎች፥ - በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ - በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሞ እንደነበር አስውሷል። በቅርንጫፍ እና በኤቲኤም የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀደም ብለው መጀመራቸውን ገልጾ አሁን ደግሞ በዲጂታል የሚሰጡ የባንክ አገልግሎቶች…
#Update #CBE #NBE
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ትላንት ባጋጠመው ችግር የደንበኞች መጉላላትን ጨምሮ የደረሱ #ጉዳቶች ስለመኖራቸው ተነግሯል።
ጉዳቶቹ ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ለህብረተሰቡ ይገለጻሉ ነው የተባለው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጋቢት 7 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ስርዓት ላይ ያጋጠመውን ችግርና የአገልግሎት መቋረጥ በተመለከተ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።
" ባንኮች በሥርዓቶቻቸዉ ላይ በየጊዜዉ የደህንነት ፍተሻ እንዲሁም የማሻሻያ ሥራዎችን ያከናዉናሉ " ያለው ብሔራዊ ባንክ ፤ " በሥርዓቶቹ ላይ በሚከናወን ለዉጦችና ፍተሻዎች የባንኮች አገልግሎት አልፎ አልፎ ሊቋረጥ ይችላል " ብሏል።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትናንትና ዕለት የተከሰተዉ የአገልግሎት መቋረጥ ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን #አረጋግጫለሁ ሲል ገልጿል።
ችግሩ ከተከሰተበት ሰዓት አንስቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የባንኩን እና የደንበኞቹን ደህንነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ክትትል ሲያደርግ እንደቆየና በተደረገው ርብርብ አገልግሎቶች እንዲመለሱ መደረጉን ጠቁሟል።
ብሔራዊ ባንክ በዚሁ መግለጫ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባጋጠመው ችግር #ጉዳቶች እንደደረሱ ጠቁሟል።
ስለ ጉዳቶቹ በዝርዝር ያለው ነገር ባይኖርም አስፈላጊው ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ለህዝብ ይገለጻል ብሏል።
በተፈጠረው ችግር የደንበኞች መጉላላትም መከሰቱን አመላክቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፋይናንስ ተቋማት ላይ በየጊዜዉ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያደርግ አመልክቶ በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ ያሉ በሁሉም የፋይናንስ ተቋማት የሚገኙ የፋይናንስ ሥርዓቶች ደህንነቸዉ የተጠበቀ ነው ብሏል።
" ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት የፋይናንስ አገልግሎቶችን መጠቀም መቀጠል ይችላል " ሲል አሳውቋል።
የፋይናንስ ተቋማትም የሥርዓቶቻቸዉን ደህንነትና ቀልጣፋነት ይበልጥ ለማሳደግ የቴክኖሎጂ ተለዋዋጭ ባህርይ በማየት በቀጣይነት መሥራት እንደሚኖርባቸዉ #ጥብቅ_ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ትላንት ባጋጠመው ችግር የደንበኞች መጉላላትን ጨምሮ የደረሱ #ጉዳቶች ስለመኖራቸው ተነግሯል።
ጉዳቶቹ ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ለህብረተሰቡ ይገለጻሉ ነው የተባለው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጋቢት 7 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ስርዓት ላይ ያጋጠመውን ችግርና የአገልግሎት መቋረጥ በተመለከተ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።
" ባንኮች በሥርዓቶቻቸዉ ላይ በየጊዜዉ የደህንነት ፍተሻ እንዲሁም የማሻሻያ ሥራዎችን ያከናዉናሉ " ያለው ብሔራዊ ባንክ ፤ " በሥርዓቶቹ ላይ በሚከናወን ለዉጦችና ፍተሻዎች የባንኮች አገልግሎት አልፎ አልፎ ሊቋረጥ ይችላል " ብሏል።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትናንትና ዕለት የተከሰተዉ የአገልግሎት መቋረጥ ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን #አረጋግጫለሁ ሲል ገልጿል።
ችግሩ ከተከሰተበት ሰዓት አንስቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የባንኩን እና የደንበኞቹን ደህንነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ክትትል ሲያደርግ እንደቆየና በተደረገው ርብርብ አገልግሎቶች እንዲመለሱ መደረጉን ጠቁሟል።
ብሔራዊ ባንክ በዚሁ መግለጫ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባጋጠመው ችግር #ጉዳቶች እንደደረሱ ጠቁሟል።
ስለ ጉዳቶቹ በዝርዝር ያለው ነገር ባይኖርም አስፈላጊው ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ለህዝብ ይገለጻል ብሏል።
በተፈጠረው ችግር የደንበኞች መጉላላትም መከሰቱን አመላክቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፋይናንስ ተቋማት ላይ በየጊዜዉ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያደርግ አመልክቶ በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ ያሉ በሁሉም የፋይናንስ ተቋማት የሚገኙ የፋይናንስ ሥርዓቶች ደህንነቸዉ የተጠበቀ ነው ብሏል።
" ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት የፋይናንስ አገልግሎቶችን መጠቀም መቀጠል ይችላል " ሲል አሳውቋል።
የፋይናንስ ተቋማትም የሥርዓቶቻቸዉን ደህንነትና ቀልጣፋነት ይበልጥ ለማሳደግ የቴክኖሎጂ ተለዋዋጭ ባህርይ በማየት በቀጣይነት መሥራት እንደሚኖርባቸዉ #ጥብቅ_ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
@tikvahethiopia