TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.5K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#አስቸኳይ

የሳዑዲ አረቢያ የፀጥታ አስከባሪ አካላት በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነና ዜጎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፎ ነበር።

የሳዑዲ ፀጥታ ኃይሎች በሰሩት ኦፕሬሽን ተይዘው በሹሜሲ የማቆያ ጣብያ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የውሃ የምግብ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች እጥረት እንዳጋጠማቸው ተሰምቷል።

በመሆኑም:-

1ኛ. ከ10 ቀን እስከ 3 ዓመት ዕድሜ ላላቸው ህፃናት የሚሆን ወተት

2ኛ. ከ1 ቁጥር እስከ 5 ቁጥር የሆኑ የህፃናት ዳይፐር/ሃፋዛ/

3ኛ. ለታዳጊ ህፃናት እና ለአዋቂዎች የሚሆኑ ደረቅ ምግቦች

4ኛ. ለሴቶች እና ለሕፃናት የሚሆኑ የመፀዳጃ ቁሳቁሶች በተለይ ዋይፕ እና ሞዴስ

5ኛ. የሚጠጣ ውሃ እጥረት ያጋጠመ በመሆኑ ዜጎቻችን ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል።

ዕርዳታ ማድረግ የምትፈልጉ ግለሰቦች/ አደረጃጀቶች በጄዳ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ (ኮሚዩኒቲ) የስራ ኃላፊነቱን ወስዶ እንቅስቃሴ የጀመረ በመሆኑ ዕርዳታችሁን በኮሚኒቲ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 1 ማድረስ እንደሚቻል በጄዳ የሚገኘው ቆንስላ ፅ/ቤት ዛሬ ማምሻውን ገልጿል።

ይህ መልዕክት የደረሳችሁ ጅዳ አካባቢ የምትገኙ የቲክቫህ አባላት በመሉ የምትችሉትን ሁሉ ታደርጉ ዘንድ መልዕክት እናስተላልፋለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ...ጥቃቱ ምግበይ በተባለ ግለሰብ የሚመራ የወንበዴ ኃይል ላይ የተወሰደ እርምጃ ነው ፤ ሰላማዊ ሰው ላይ ጥቃት አልተፈፀምም" - ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ

ከትላንት በስቲያ ከመቐለ በስተ ምዕራብ አቅጣጫ 25 ኪ.ሜ በምትገኝ እንደርታ ወረዳ ደብረናዝሬት ቀበሌ ተቶጋግ እዳጋ ሰሉስ በምትባል መንደር ለገበያ ተሰብስበው የነበሩ ሰዎች በነበሩበት ወቅት ተፈፅሟል የተባለውን የአየር ጥቃት መነጋገሪያነቱ ቀጥሏል።

ቶጎጋ እዳጋ ሰሉስ ላይ ተፈፅሟል በተባለው የአየር ድብደባ እስካሁን ቁጥራቸው ያልታወቀ ዜጎች ህይወት አልፏል፤ በርካቶችም ቁስለኛ ሆነዋል።

የአይን እማኞች ድብደባው ማክሰኞ ከቀኑ ስድስት ሰዓት አካባቢ ለገበያ ተሰብስቦ በነበረ ህዝብ ላይ ነው የተፈፀመው ብለዋል። በድብደባው በሰዎች ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ በእንስሳት ላይ ጉዳት ደርሷል።

የአይን እማኞቹ በቅድሚያ የተመታው ገበያው እንደሆነ በኃላም በቤቶች ላይ እንደነበር አስረድተዋል።

ከቦታው ጉዳት ደርሶባቸው መቐለ አይደር ሆስፒታል የገቡት 5 ሰዎች ሲሆኑ ከእነሱ መካከል አንዷ የ2 ዓመት ከአራት ወር ህፃን ትገኛለች።

ህፃኗ ከፍተኛ የሆኑ ጉዳት የደረሰባት ሲሆን በአሁን ሰዓት መተንፈስ ስለማትችል የመተንፈሻ ቱቦ ተገጥሞላት ይገኛል። በሌላ በኩል የህፃኗ አባት ጉዳት ደርሶበት ወደ ህክምና እንዳይገባ በወታደሮች ተከልክሏል ተብሏል።

አንድ የአይን እማኝ ደግሞ አጠገቡ ሶስት ሰዎች መሞታቸውን ገልጿል። አህዮች ጨምሮ ብዙ እንስሶችም ሞተዋል ብሏል ፤ በአካባቢው ታጣቂዎች እንደነበሩ ተጠይቆ ምንም ታጣቂ አላየሁም ብሏል።

ጉዳት የደረደባቸውን ሰዎች ለማምጣት የአምቡላንስ ሹፌሮች አምስት ጊዜ ተጉዘው አይቻልም ተብለው መመለሳቸውን ገልፀዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/Tgoga-Tigray-06-24

@tikvahethiopia
"..ህዝቡን እያሽበርኩ በዚህ እቀጥላለሁ የሚል ከሆነ ዳግም በተጠናከረ መልኩ የሀይል እርምጃ ይወሰድበታል" - ሀገር መከላከያ ሰራዊት

ከሰሞኑን ትግራይ ክልል የነበረው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ለምርጫው ሰላማዊነት ሲባል ወደሌላ የአገሪቱ አካባቢዎች መንቀሳቀሱን ተከትሎ በሽብርተኝነት የተፈረጀው የህውሓት ሚሊሻዎች ከተደበቁበት በመውጣት ሰላማዊውን የትግራይ ህዝብ ሲያሸብሩ ነበር አለ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ዛሬ በሰጠው መግለጫ።

የሰራዊቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮ/ል ጌትነት አዳነ ፥ ሀገራዊ ምርጫውን ተከትሎ ከውጭም ከውስጥም ስጋት ስለነበር ሰራዊቱ በመንግስት ትዕዛዝ መሰረት ከትግራይ ወደ ማዕከል፣ ምስራቅ፣ ምእራብና የደቡብ የሀገራችን ክፍል እንዲንቀሳቀስ ተደርጎ ነበር ብለዋል።

"ይህን ሁኔታ እንደ መልካም አጋጣሚ በመውሰድ በየጢሻው ተደብቆ የነበረው የህወሓት ሚሊሻ ህዝቡን ሲያስገድድና ሰላማዊ እንቅስቃሴውን ሲያስተጓጉል ነበር" ሲሉ ተናግረዋል።

መከላከያ ሰራዊቱ በወሰደው እርምጃ ህዝብን ወደ ሰላማዊ ኑሮው መመለስ ተችሏል ሲሉም ተደምጠዋል።

ዳይሬክተሩ ፥ በክልሉ የወደሙ መሰረተ ልማቶችን በፍጥነት በመስራት ገበሬው እንዲያርስ፣ ነጋዴው እንዲነግድ፣ ተማሪዎች እንዲማሩ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እንደተሰሩ ገልጸዋል።

ይህ መልሶ የማቋቋም ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እየተደረገ ባለበት ወቅት የህወሓት ሀይል ህዝቡ ተጠቃሚ እንዳይሆን ፋይዳ ቢሲ ትንኮሳዎችን ከተደበቀበት እየወጣ እየተነኮሰ ይገኛል ብለዋል።

በሽብርተኝነት የተፈረጀው ቡድን ህዝቡን እያሽበርኩኝ በዚህ እቀጥላለሁ የሚል ከሆነ ዳግም በተጠናከረ መልኩ የሀይል እርምጃ እንደሚወሰድበት አስጠንቅቀዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/Tigray-06-24

#ኢፕድ
@tikvahethiopia
#Update

በሳውዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን በ2 ሳምንታት ሙሉ በሙሉ ወደ አገራቸው ለማስገባት የሚያስችል ኮሚቴ ተቋቁሞ ስራ መጀመሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሳምንታዊ ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ።

ቃል አቀባዩ ፥ በሳውዲ የሚገኙ ዜጎች ጉዳይ በሁለት ሳምንት ውስጥ ምላሽ ያገኛል ሲሉ ተናግረዋል።

በሳዑዲ የሚገኙ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን እንግልትና ስቃይ ለማስቆም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተካተቱበት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ሥራውን እንደጀመረ ገልፀዋል።

ግብረ ሀይሉ በቀጣይ 2 ሳምንት ውስጥ በ ሳዑዲ የሚገኙ ዜጎችን ወደ አገራቸው ይመልሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።

ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8
@tikvahethiopia
"...በምርጫው ዕለት በአገሪቱ ደም ለማፋሰስ የሚፈልጉ ኃይሎች ነበሩ ነገር ግን ሴራቸው ከሽፏል" - አምባሳደር ዲና ሙፍቲ

የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫውን #በሰላማዊ መንገድ በማከናወን በእለቱ ደም ለማፋሰስ ያቀዱ ኃይሎችን ሴራ አክሽፏል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ።

ቃል አቀባዩ ይህን ያሉት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ነው።

አምሳባሳደሩ በምርጫው ወቅት እና ከምርጫ በኋላ በአገሪቱ ደም እንዲፋሰስ የሚፈልጉ ኃይሎች እንደነበሩ አስታውሰዋል።

በምርጫው እለት የነበረውን ሂደት በርካታ አገር አቀፍ እና አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን በስፋት ሽፋን የሰጡት መሆኑንም ገልጸዋል።

የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫው ታማኝና ሰላማዊ እንደነበር ማረጋገጡንም አክለው መናገራቸውን ኢዜአ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
CANAL+ ለልጆችዎ ካዘጋጃቸው ሁለት የአማረኛ ቻናሎች በተጨማሪ አምስት ከዓለም የተወጣጡ አዝናኝ እና አስተማሪ የልጆች ቻናሎችን ይዞ መምጣቱን ያውቁ ኖሯል?

ስለ ሰባቱ የCANAL+ የልጆች ቻናሎች የበለጠ መረጃ ለማግኘት ሊንኩን በመጫን የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ! https://yangx.top/canalplusbusiness
#PressBriefing

ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እለታዊ የሚዲያ ማብራሪያ ይሰጣል።

ቦርዱ ማብራሪያውን ከቀኑ 10:30 ከስካይላይት ሆቴል ነው የሚሰጠው።

ውድየቲክቫህ አባላት መግለጫውን ሚከታተሉ የቤተሰባችን አባላት በስፍራው ይገኛሉ።

መግለጫውን በቀጥታ በ ቴሌግራም Voice Chat ማዳመጥ እንደምትችሉ ከወዲሁ እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
ያሶን ጨምሮ 5 እስረኞች ከእስር ተፈተዋል።

በእስር ላይ ከነበሩት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (OLF) አመራር እና አባላት መካከል ያሶ ከበበውን ጨምሮ 5 እስረኞች ትላንት ተፈተዋል።

በእነ አቶ ያሶ መዝገብ ስር በተከሰሱት ስድስት ተከሳሾች ላይ የቀረበባቸው ማስረጃ እውነት መሆኑም ማረጋገጥ ባለመቻሉ ፍርድ ቤት ስድስቱም ተከሳሾች በነፃ እንዲሰናበቱ መወሰኑን የተከሳሽ ጠበቆች ለኦ ኤም ኤን ተናግረዋል።

ይህን ተከትሎም በትንትናው ዕለት 6ቱም ተከሳሾች ከእስር ተለቀዋል።

ከመስከረም 2/2011 ዓ/ም ጀምሮ ማስረጃ ሳይቀርብባቸው በእስር ላይ እንደነበሩ ጠበቆቻቸው አስታውሰዋል።

@tikvahethiopia
አቶ ዳገቶ ኩምቤ ከእስር ተፈቱ።

ለ10 ወር ያህል በእሥር የቆዩት የቀድሞ የዎላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ ከእስር መፈታታቸው ተሰምቷል።

ከእሳቸው በተጨማሪም ምክትላቸው የነበሩት አቶ ገበዜ ጎዳና ዛሬ ሰኔ 17 /2013 ዓ.ም ዎላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎታ በነፃ አሰናብቷቸዋል።

የቀድሞው የዎላይታ ዞን አመራሮች የተከሰሱት ስልጣናቸውን አላግባብ የመገልገል ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ነበር።

Video Credit : Woldetsaadiqa

@tikvahethiopia
Live stream started
#LIVE

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ዕለታዊ ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።

ከላይ ባለው የVoice Chat 'Join ' የሚለውን በመጫን በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ።

@tikvahethiopia
#Update

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 በነበረው መግለጫ የነጌሌ ምርጫ ክልል (ጉጂ-ኦሮሚያ) በክልሉ የሚወዳደር የግል ተወዳዳሪ በምርጫ መስጫ ወረቀቱ ላይ ዝርዝሩ ባለመካተቱ ባቀረበው ቅሬታ መሰረት ምርጫውን ወደ ጳጉሜ 1 አዛውሮት እንደነበር ይታወሳል።

ዛሬ መግለጫ እየሰጡ የሚገኙት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርትኳን ሚደቅሳ በምርጫ ክልሉ ከቦርዱ እውቅና ውጪ ከመቶ በላይ በሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫ መደረጉን ገልጸዋል።

ምርጫ ስርዓቱ የህግ ውጤት የሚኖረው እንደማይሆን /ውድቅ መደረጉን አሳውቀዋል።

ወ/ሪት ብርቱካን የምርጫ ቦርድን ውሳኔ ችላ ብለው ድምፅ እንዲሰጥ ያደረጉ አካላት በህግ ይጠየቃሉ ብለዋል፤ ጉዳዩንም ለፌዴራል ፖሊስ አሳውቀናል ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
Live stream finished (54 minutes)
#Update

"በደሴ 10 በሚሆኑ ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ሳጥኖች ተሞልተው ተገኙ" ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ አሳውቀዋል።

በ10ሩ የምርጫ ጣቢያዎች የተፈጠረውን ጉዳይም ዛሬ በነበራቸው መግለጫ አስረድተዋል።

በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የውጤት አገላለፅ እንዲሁም የውጤት አመዘጋገብ በትክክለኛው መንገድ ስለመፈፁ የሚረጋገጥበት የራሱ ደረጃ አለው ይህም በስልጣና ላይ ተሰጥቷል ብለዋል።

ከእንዚህ ደረጃዎች/ሂደቶች መካከል ፦
- የመጀመሪያው በዚያ ጣቢያ ስንት ሰው ነው የሚመዘገበው ?
- በዕለቱ መጥቶ መዝገብ ላይ ፈርሞ ድምፅ የሰጡ ብዛት ስንት ናቸው ? ፊርማቸው ተቆጥሮ መመዝገብ አለበት።
- የመጡት ሰዎች ተመዝግበዋል ከተባሉት ሰዎች ቁጥራቸው መበላለጥ ስለሌለበት ይህም ይረጋገጣል።
- የደረሰው የድምፅ መስጫ ወረቀት ብዛት ስንት ነው ?
- ሳጥን ውስጥ የተገኘው ምን ያህል ነው ?
- የተበላሸ የድምፅ መስጫ ወረቀት ስንት ነው ? የሚሉት ይገኙበታል።

ደሴ የተገኙት 10 ምርጫ ጣቢያዎች ትክክለኛነቱን የሚያረጋግጡ አካሄዶችን ሳይፈፅሙ ፣ ሂሳቡንም በትክክል ሳይሰሩ በመላካቸው በምርጫ ክልል ደረጃ እንደገና መታየት ስላለበት / ድምፅ ቆጠራው መደገም ስላለበት የምርጫ ክልሉ ለጊዜው ኳራንታይን አድርጎ አስቀምጦታል።

ይህ ሁኔታ ነው የማይሆን ትርጉም ተሰጥቶት #ሀሰተኛ_መረጃ እንዲሰራጭ ምክንያት የሆነው ሲሉ ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

የ24 ሰዓት የኮቪድ ሪፖርት :

• የላብራቶሪ ምርመራ - 4,525
• ቫይረሱ የተገኘባቸው - 99
• ህይወታቸው ያለፈ - 4
• ከበሽታው ያገገሙ 642

አጠቃላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 275,601 የደረሱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 4,296 ህይወታቸው ሲያልፍ 257,429 ሰዎች አገግመዋል። ክትባት የተከተቡ ዜጎች 1,987,927 ደርሰዋል።

@tikvahethiopia
Audio
AudioLab
#ምርጫ2013

በምርጫ ወቅት የምንጠቀማቸው ቃላቶች ፦

በአሁን ወቅት በተደጋጋሚ ለሚነሱት የምርጫ ቃላቶች ማብራሪያ እንዲሰጡን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወይዘሪት ሶልያና ሽመልስን ጋብዘናል።

ማብራሪያ የተሰጠባቸው ቃላቶች፦

- ኳራንታይን
- ውጤት ማጣራትና ማረጋገጥ

በተጨማሪም ወ/ሪት ሶልያናን ስለ ቅሬታ አቀራረብ እና ውጤት ስረዛ ጥያቄ አቅርበንላቸዋል።

ወ/ሪት ሶሊያና የሰጡትን ምላሽ ከላይ ከድምጽ ፋይሉ ያድምጡ።

#TikvahFamily #ምርጫ2013

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

ኳራንቲን የተደረጉ /በምርመራ ላይ ያሉ ጣቢያዎች ስንት ናቸው ?

በአዲስ አበባ የመጫረሻ #ኳራንቲን ፣ ምንም የማይደረግበት ወይም ደግሞ ወደውጤት ቋት ውስጥ የማይገባ በሚል የተያዙ ሁለት የምርጫ ጣቢያዎች እንዳሉ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ አሳውቀዋል።

አንደኛው በምርጫ ክልል 24 ያለ ሲሆን ሌላኛው በንፋስ ስልክ ያለ ነው።

ከዛ ውጭ እንደገና በመቁጠር እና ሰነዶችን እንደገና በማየት የሚስተካከሉ ሊኖሩ ይችላሉ።

NB : በምርጫው ሂደት "ኳራንቲን ማድረግ" ማለት ከዋናዎቹ ውጤቶች ጋር ሳይቀላቀል ማግለል ወይም ደግሞ መለየት እና በልዩ ሁኔታ ማጣራት ማለት ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ያሶን ጨምሮ 5 እስረኞች ከእስር ተፈተዋል። በእስር ላይ ከነበሩት የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (OLF) አመራር እና አባላት መካከል ያሶ ከበበውን ጨምሮ 5 እስረኞች ትላንት ተፈተዋል። በእነ አቶ ያሶ መዝገብ ስር በተከሰሱት ስድስት ተከሳሾች ላይ የቀረበባቸው ማስረጃ እውነት መሆኑም ማረጋገጥ ባለመቻሉ ፍርድ ቤት ስድስቱም ተከሳሾች በነፃ እንዲሰናበቱ መወሰኑን የተከሳሽ ጠበቆች ለኦ ኤም ኤን ተናግረዋል። …
"በነፃ አልተለቀቅንም"

ከትላት በስቲያ ከእስር የተፈቱ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር የፖለቲካ መኮንን አቶ ያሶ ከበበው ስለአፈታታቸው እንዲሁም ስለእስራቸው ትላንት ምሽት አየር ላይ በዋለው የቪኦኤ አፋን ኦሮሞ የሬድዮ ስርጭት ላይ አስተያየት ሰጥተዋል።

ከ30 የጊዜ ቀጠሮ በኃላ ፍርድ ቤት የተመላለሱት እነ አቶ ያሶ በነፃ እንዳልተለቀቁ እና ታስረው እንደወጡ ወቀሳ አሰምተዋል።

አቶ ያሶ፥ "ፍ/ቤቱ ከተጠረጠርኩበት ወንጀል ነፃ ነህ አለኝ እንጂ አንተ ነፃ ሰው ነህ አላለኝም።

አንድ ሰው ሁለት አመት ታስሮ ነፃ ነህ ተብሎ ሲፈታ መደሰት ይለበትም፤ ምክንያቱም ሁለት አመት ታስሮ ነው የወጣው መባል አለበት።

ፍርድ ቤት በነፃ ነው ያሰናበትኩት ማለት የለበትም ፤ እኔ ሁለት ዓመት ታስሬ ነው የወጣሁት ነገር ግን ከተጠረጠርኩበት ወንጀል ነፃ ነህ የሚል ሃሳብ ነው ከተከሳሾቼ የተረዳሁት" ብለዋል።

የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ስለእነ አቶ ያሶ ተይዘው ስለቆዩበት ጊዜ በሰጠው አስተያየት በክርክር ሂደት በእስር ቤት ቆይተው ፍርድ ቤት በመመላለስ የባከነ ጊዞ ሳይሆን የፍትህ ማስገኛ ጊዜ ነው ሲል ገልጿል።

አቶ ያሶ መንግስት የህግ የበላይነት አስከብራለሁ እያለ ያለ ሰዎችን ካለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይታሰራሉ ያሉ ሲሆን አጋጥሟቸው የነበረውን ችግር ተናግረዋል፦

"ለምሳሌ አንድ ሰው በፀጥታ ኃይል ቁጥጥር ስር ሲውል በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሆን አለበት። ነገር ግን እኔ ከመንገድ ላይ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ነው የተያዝኩት፤ ይህ ህገወጥ ነው። በተጨማሪ ከታሰርን በኃላ አራዳ ፍርድ ቤት የዋስትና መብት ሰጥቶን የዋስትና ማስከበሪያ ከተከፈለ በኃላ አሁንም ፖሊስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ወደጎን በመተው ለአንድ አመት ከስምንት ወር አሰረን"

ያንብቡ : telegra.ph/YASO-KABABAW-06-25

@tikvahethiopia