ከግንቦት 28/2005 ዓ/ም ጀምሮ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት ከነገ መስከረም 5/2013 ዓ/ም ጀምሮ ኃላፊነቱ እንደተነሳላቸው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ አስታውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አዲሱ የብር ኖት 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ታትሟል!
አዲሱ የብር ኖት 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ታትሞ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ለስርጭት ዘግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ አዲሱን የብር ኖት በማስመልከት ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም አሁን ላይ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ታትሞ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች የብር ኖት ቅያሬውን ለማከናወን ዝግጅቱ መጠናቀቁን ገልጸዋል።
አዲሱን የብር ኖት ለማሳተም 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ውጭ መደረጉንም ገልጸው፤ በሁሉም ክልሎች በበቂ ሁኔታ ለማድረስ ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።
የብር ቅያሬው በውክልና የማይከናወን በመሆኑ መታወቂያ በመያዝ ባለቤቱ ብቻ ማከናወን ይኖርበታል ብለዋል።
ከአጎራባች አገራት የሚገባን ህገ ወጥ የሆነ ገንዘብ ለመቆጣጠር በድንበር አካባቢ ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግ መሆኑን ዶክተር ይናገር መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አዲሱ የብር ኖት 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ታትሞ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ለስርጭት ዘግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ አዲሱን የብር ኖት በማስመልከት ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም አሁን ላይ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ታትሞ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች የብር ኖት ቅያሬውን ለማከናወን ዝግጅቱ መጠናቀቁን ገልጸዋል።
አዲሱን የብር ኖት ለማሳተም 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ውጭ መደረጉንም ገልጸው፤ በሁሉም ክልሎች በበቂ ሁኔታ ለማድረስ ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።
የብር ቅያሬው በውክልና የማይከናወን በመሆኑ መታወቂያ በመያዝ ባለቤቱ ብቻ ማከናወን ይኖርበታል ብለዋል።
ከአጎራባች አገራት የሚገባን ህገ ወጥ የሆነ ገንዘብ ለመቆጣጠር በድንበር አካባቢ ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግ መሆኑን ዶክተር ይናገር መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የትግራይ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ ሆነ!
ዛሬ የትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽን ጳጉሜ 4/2012 ዓ/ም የተደረገውን 6ኛው ክልላዊ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ አድርጓል።
ከአጠቃላዩ 190 የክልሉ ምክር ቤት ወንበሮች 189ኙ በህወሓት የተያዙ ሲሆን በታሪክ ለመጀመሪያ ግዜ አንድ ተቃዋሚ ፓርቲ በምክር ቤቱ አንድ (1) ወንበር አግኝቷል፡፡
ባይቶና በአንድ ወንበር ምክር ቤት የገባ ፓርቲ ሆኗል፡፡
ምንጭ፦ ሚሊዮን ኃይለስላሴ (DW)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዛሬ የትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽን ጳጉሜ 4/2012 ዓ/ም የተደረገውን 6ኛው ክልላዊ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ይፋ አድርጓል።
ከአጠቃላዩ 190 የክልሉ ምክር ቤት ወንበሮች 189ኙ በህወሓት የተያዙ ሲሆን በታሪክ ለመጀመሪያ ግዜ አንድ ተቃዋሚ ፓርቲ በምክር ቤቱ አንድ (1) ወንበር አግኝቷል፡፡
ባይቶና በአንድ ወንበር ምክር ቤት የገባ ፓርቲ ሆኗል፡፡
ምንጭ፦ ሚሊዮን ኃይለስላሴ (DW)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19Ethiopia
መስከረም 4/2013 ዓ/ም
የተደረገ ላብራቶሪ ምርመራ - 9,256
በቫይረሱ የተያዙ - 485
ህይወታቸው ያለፈ - 9
ያገገሙ - 350
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
መስከረም 4/2013 ዓ/ም
የተደረገ ላብራቶሪ ምርመራ - 9,256
በቫይረሱ የተያዙ - 485
ህይወታቸው ያለፈ - 9
ያገገሙ - 350
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrAbiyAhmed
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በነገው ዕለት ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጋር እንደሚወያዩ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር በደረ ገፁ አስነብቧል።
ነገ ረፋዱን ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ለዚሁ ስብሰባ ፤ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በዛሬው ዕለት ጥሪ ተደርጎላቸዋል።
የነገው ውይይት ባለፈው ሐምሌ ወር ከተደረገው ተመሳሳይ ስብሰባ ወዲህ የነበሩ ሂደቶች የሚገመገሙበት እንደሆነ ተገልጿል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በነገው ዕለት ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጋር እንደሚወያዩ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር በደረ ገፁ አስነብቧል።
ነገ ረፋዱን ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ለዚሁ ስብሰባ ፤ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በዛሬው ዕለት ጥሪ ተደርጎላቸዋል።
የነገው ውይይት ባለፈው ሐምሌ ወር ከተደረገው ተመሳሳይ ስብሰባ ወዲህ የነበሩ ሂደቶች የሚገመገሙበት እንደሆነ ተገልጿል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲሱ የብር ኖት 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ታትሟል! አዲሱ የብር ኖት 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ታትሞ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ለስርጭት ዘግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ አዲሱን የብር ኖት በማስመልከት ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም አሁን ላይ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ታትሞ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች የብር ኖት ቅያሬውን ለማከናወን…
ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ከሰጡት መግለጫ የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች ፦
- የብር ለውጡን ተከትሎ ህገ ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር ዝግጅት ተደርጓል።
- በተለያዩ ጎረቤት አገራት የኢትዮጵያ የብር ኖቶች ክምችት አለ ፤ ለብር ለውጡ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ቁጥጥር ይደረጋል። ለዚህም ከጸጥታና የደህንነት አካላት ጋር በመነጋገር የመቆጣጠርና የማምከን ተግባራት ይከናወናል።
- በድንበር አካባቢ የሚገኙ ባንኮች በብር ለውጡ ለህገ ወጥ ድርጊቶች እንዳይጋለጡ ጥብቅ ክትትል ይደረጋል።
- የብር ቅያሬውን ለማከናወን ማንኛውም ግለሰብ የብር ኖቶቹን ራሱ በባንክ መቀየር ሲገባው በሌላ ግለሰብ በውክልና መቀየር አይችልም።
- በ3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጪ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን የብር ኖት ታትሟል፤ የመጠባበቂያ ክምችት እንዲኖር ተጨማሪ የብር ኖቶች እየታተሙ ነው።
- ባለፉት ጥቂት ወራት አዳዲሶቹን የብር ኖቶች ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የማጓጓዝ ስራ ተሰርቷል። አሮጌውን ገንዘብ መቀየር የሚያስችል በቂ ክምችት አለ።
- አዳዲሶቹ የብር ኖቶች እንዳይበላሹ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል፤ ይሄም ኢትዮጵያ የተበላሸ ገንዘብ ለመተካት የምታወጣውን ብዙ ወጪ ያስቀራል።
- ህገ ወጥ ተግባራት የሚፈጽሙ ባንኮች እንደ ጥፋታቸው መጠን እና ልክ ቅጣት ይጣልባቸዋል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
- የብር ለውጡን ተከትሎ ህገ ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር ዝግጅት ተደርጓል።
- በተለያዩ ጎረቤት አገራት የኢትዮጵያ የብር ኖቶች ክምችት አለ ፤ ለብር ለውጡ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ቁጥጥር ይደረጋል። ለዚህም ከጸጥታና የደህንነት አካላት ጋር በመነጋገር የመቆጣጠርና የማምከን ተግባራት ይከናወናል።
- በድንበር አካባቢ የሚገኙ ባንኮች በብር ለውጡ ለህገ ወጥ ድርጊቶች እንዳይጋለጡ ጥብቅ ክትትል ይደረጋል።
- የብር ቅያሬውን ለማከናወን ማንኛውም ግለሰብ የብር ኖቶቹን ራሱ በባንክ መቀየር ሲገባው በሌላ ግለሰብ በውክልና መቀየር አይችልም።
- በ3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጪ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን የብር ኖት ታትሟል፤ የመጠባበቂያ ክምችት እንዲኖር ተጨማሪ የብር ኖቶች እየታተሙ ነው።
- ባለፉት ጥቂት ወራት አዳዲሶቹን የብር ኖቶች ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የማጓጓዝ ስራ ተሰርቷል። አሮጌውን ገንዘብ መቀየር የሚያስችል በቂ ክምችት አለ።
- አዳዲሶቹ የብር ኖቶች እንዳይበላሹ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል፤ ይሄም ኢትዮጵያ የተበላሸ ገንዘብ ለመተካት የምታወጣውን ብዙ ወጪ ያስቀራል።
- ህገ ወጥ ተግባራት የሚፈጽሙ ባንኮች እንደ ጥፋታቸው መጠን እና ልክ ቅጣት ይጣልባቸዋል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ATTENTION
በኢትዮጵያ እና በሌሎች የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ሀገራት ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ሊጥል እንደሚችል የምስራቅ አፍሪካ የአየር ንብረት የልህቀት ማዕከል አስጠነቀቀ፡፡
ማዕከሉ በተለይም በመካከለኛው እና ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በሰሜን ምስራቅ ሶማሊያ አካባቢዎች ከባድ ዝናብ ሊጥል ይችላል ብሏል።
በእነዚህ ሀገራት የሚጠበቀው ከባድ ዝናብ ሊያደርስ የሚችለውን አደጋዎችን ለመከላከል ባለድርሻ አካላት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ የልህቀት ማዕከሉ አስጠንቅቋል፡፡
የዝናብ ትንበያው ከዛሬ ጀምሮ በሚቀጠሉት ሰባት ቀናት ውስጥ የሚጠበቅ ሲሆን በምዕራብ እና መካከለኛው ኢትዮጵያ ጥቂት ቦታዎች ከ 200 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ ዝናብ ይጠበቃል ነው የተባለው፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እንዲሁም በጎረቤት ሀገራት ደቡብ-ምዕራብ ሱዳን ፣ ከሰሜን-ምዕራብ እስከ ደቡብ-ምዕራብ ደቡብ ሱዳን፣ በምዕራብ እና፣ ሰሜን-ምስራቅ ሶማሊያ እንዲሁም በሰሜን-ምዕራብ ዩጋንዳ እና ምዕራብ ኬንያ ከ 50 እስከ 200 ሚሊ ሜትር የሆነ መካከለኛ ዝናብ ይኖራል፡፡
በሰሜን ፣ ምስራቅ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ፣ በማዕከላዊ ሱዳን ፣ በሰሜን ምዕራብ ኤርትራ ፣ በምዕራብ እና ማዕከላዊ ደቡብ ሱዳን፣ በሰሜን እና በደቡብ ሶማሊያ ፣ በጅቡቲ የባህር ዳርቻዎች ፣ በማዕከላዊ እና በምስራቅ ዩጋንዳ አንዳንድ አካባቢዎች ከ50 ሚሊ ሜትር በታች የሆነ ቀላል ዝናብ ይኖራል ተብሏል፡፡
(ኢዜአ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ እና በሌሎች የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት ሀገራት ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ሊጥል እንደሚችል የምስራቅ አፍሪካ የአየር ንብረት የልህቀት ማዕከል አስጠነቀቀ፡፡
ማዕከሉ በተለይም በመካከለኛው እና ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በሰሜን ምስራቅ ሶማሊያ አካባቢዎች ከባድ ዝናብ ሊጥል ይችላል ብሏል።
በእነዚህ ሀገራት የሚጠበቀው ከባድ ዝናብ ሊያደርስ የሚችለውን አደጋዎችን ለመከላከል ባለድርሻ አካላት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ የልህቀት ማዕከሉ አስጠንቅቋል፡፡
የዝናብ ትንበያው ከዛሬ ጀምሮ በሚቀጠሉት ሰባት ቀናት ውስጥ የሚጠበቅ ሲሆን በምዕራብ እና መካከለኛው ኢትዮጵያ ጥቂት ቦታዎች ከ 200 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ ዝናብ ይጠበቃል ነው የተባለው፡፡
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እንዲሁም በጎረቤት ሀገራት ደቡብ-ምዕራብ ሱዳን ፣ ከሰሜን-ምዕራብ እስከ ደቡብ-ምዕራብ ደቡብ ሱዳን፣ በምዕራብ እና፣ ሰሜን-ምስራቅ ሶማሊያ እንዲሁም በሰሜን-ምዕራብ ዩጋንዳ እና ምዕራብ ኬንያ ከ 50 እስከ 200 ሚሊ ሜትር የሆነ መካከለኛ ዝናብ ይኖራል፡፡
በሰሜን ፣ ምስራቅ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ፣ በማዕከላዊ ሱዳን ፣ በሰሜን ምዕራብ ኤርትራ ፣ በምዕራብ እና ማዕከላዊ ደቡብ ሱዳን፣ በሰሜን እና በደቡብ ሶማሊያ ፣ በጅቡቲ የባህር ዳርቻዎች ፣ በማዕከላዊ እና በምስራቅ ዩጋንዳ አንዳንድ አካባቢዎች ከ50 ሚሊ ሜትር በታች የሆነ ቀላል ዝናብ ይኖራል ተብሏል፡፡
(ኢዜአ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጥቅምት እና ህዳር ውስጥ ብዙ ሰው በኮቪድ-19 ይሞታል ተብሎ ተሰግቷል!
በመጪዎቹ ጥቅምት እና ህዳር ወራት በኮቪድ-19 ሳቢያ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ይጨምራል ብለው እንደሚገምቱ የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) የአውሮፓ ቅርንጫፍ ኃላፊ መናገራቸውን ቪኦኤ ዘገበ።
ሃንስ ክሉገ ለአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ በሰጡት ቃል "እየከፋ ነው የሚሄደው፣ ጥቅምት እና ኅዳር ውስጥ ብዙ ሰው ይሞታል ብለን እንሰጋለን” ብለዋል።
የኮቪድ-19 ክትባት ቢገኝ እንኳን ዓለምቀፉ ወረርሽኝ አበቃ ማለት እንደማይሆንም አሳስበዋል።
"የሚገኘው ክትባት ለሁሉም ህዝብ የሚሆን ወይም ሁሉንም የሚረዳ እንደሚሆን አናውቅም። የተወሰነ የህዝብ ክፍል ቫይረሱን እንዲከላከል እንደሚረዳ ለሌላው ደግሞ ምንም ላይጠቅም እንደሚችል ከወዲሁ ፍንጮች እያገኘን ነው ፤ ያ ከሆነ ደግሞ የተለያዩ የክትባት ዓይነቶችን ማዘዝ ሊኖርብን ነው፤ እንደዚያ ሲሆን የሚኖረውን የማጓጓዣ እና የማከፋፈል መከራ ማየት ነው" ብለዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በመጪዎቹ ጥቅምት እና ህዳር ወራት በኮቪድ-19 ሳቢያ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ይጨምራል ብለው እንደሚገምቱ የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) የአውሮፓ ቅርንጫፍ ኃላፊ መናገራቸውን ቪኦኤ ዘገበ።
ሃንስ ክሉገ ለአዣንስ ፍራንስ ፕሬስ በሰጡት ቃል "እየከፋ ነው የሚሄደው፣ ጥቅምት እና ኅዳር ውስጥ ብዙ ሰው ይሞታል ብለን እንሰጋለን” ብለዋል።
የኮቪድ-19 ክትባት ቢገኝ እንኳን ዓለምቀፉ ወረርሽኝ አበቃ ማለት እንደማይሆንም አሳስበዋል።
"የሚገኘው ክትባት ለሁሉም ህዝብ የሚሆን ወይም ሁሉንም የሚረዳ እንደሚሆን አናውቅም። የተወሰነ የህዝብ ክፍል ቫይረሱን እንዲከላከል እንደሚረዳ ለሌላው ደግሞ ምንም ላይጠቅም እንደሚችል ከወዲሁ ፍንጮች እያገኘን ነው ፤ ያ ከሆነ ደግሞ የተለያዩ የክትባት ዓይነቶችን ማዘዝ ሊኖርብን ነው፤ እንደዚያ ሲሆን የሚኖረውን የማጓጓዣ እና የማከፋፈል መከራ ማየት ነው" ብለዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ህፃናትን አስገድደው ደፍረዋል የተባሉ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ!
በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጃዊ ወረዳና ደብረ ማርቆስ ከተማ ህፃናትን አስገድደው ደፍረዋል ተብለው የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች እስከ 25 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጡ።
መረጃ #1 ፦
ይሉሃል እንዳለው የተባለ ግለሰብ በጃዊ ወረዳ የ11 ዓመት እድሜ ያላትን ታዳጊ ህጻን ግንቦት 17/2012 ዓ.ም አስገድዶ ደፍሯል።
የ40 ዓመት እድሜ ያለው ይሄው ግለሰብ ከደፈራት ታዳጊ ህጻን እናት ጋር በአንድ ተቋም የሚሰሩና በጉርብትናም የሚቀራረቡ ናቸው።
ይህንን አጋጣሚ ተጠቅሞ ከህጻኗ ጋር በመቀራረብ ደፍሯታል ድርጊቱን ከፈጸመ በኋላ ለእናቷ ብትናገር እንደሚገላት ማስፈራራቱን በማስረጃ ተረጋግጧል።
ግለሰቡ በዚህ ሳያበቃ እንደገና ግንቦት 19/2012 ዓ.ም በድጋሜ አስገድዶ ሲደፍራት ወላጅ እናቷ ደርሳ ለፖሊስ አመልክታች።
ፈጽሞታል የተባለው የወንጀሉ ድርጊት በፖሊስ ከተጣራ በኋላ አቃቤ ህግ የመሰረተውን ክስ የተመለከተው የጃዊ ወረዳ ፍርድ ቤት በሰውና ሰነድ ማስረጃ አመሳክሮ ግለሰቡ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ጳጉሜን 4/2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል።
መረጃ #2 ፦
በደብረ ማርቆስ ከተማ ህጻን አስገድዶ የመድፈር ሙከራ ባደረገ ግለሰብ ላይ በ12 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል።
የከተማ ነዋሪ የሆነው ግለሰብ ህጻኗን ብር ልስጥሽ በማለት ከቤት አታሎ በመውሰድ ሐምሌ 7/2012 ዓ/ም የመድፈር ሙከራ ማድረጉን በሰውና ሰነድ ማስረጃ ተረጋግጧል።
ድርጊቱን ፈጽሟል የተባለው የሃያ ሰባት (27) ዓመት እድሜ ያለው ጳውሎስ ምህረቴ ጥፈተኛነቱ ተረጋግጦበት የከተማው ፍርድ ቤት ጳጉሜን 5/2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት የቅጣት ውሳኔው ተላልፎበታል። (ኢዜአ)
@tikvahethiopiaBOT
በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጃዊ ወረዳና ደብረ ማርቆስ ከተማ ህፃናትን አስገድደው ደፍረዋል ተብለው የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች እስከ 25 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጡ።
መረጃ #1 ፦
ይሉሃል እንዳለው የተባለ ግለሰብ በጃዊ ወረዳ የ11 ዓመት እድሜ ያላትን ታዳጊ ህጻን ግንቦት 17/2012 ዓ.ም አስገድዶ ደፍሯል።
የ40 ዓመት እድሜ ያለው ይሄው ግለሰብ ከደፈራት ታዳጊ ህጻን እናት ጋር በአንድ ተቋም የሚሰሩና በጉርብትናም የሚቀራረቡ ናቸው።
ይህንን አጋጣሚ ተጠቅሞ ከህጻኗ ጋር በመቀራረብ ደፍሯታል ድርጊቱን ከፈጸመ በኋላ ለእናቷ ብትናገር እንደሚገላት ማስፈራራቱን በማስረጃ ተረጋግጧል።
ግለሰቡ በዚህ ሳያበቃ እንደገና ግንቦት 19/2012 ዓ.ም በድጋሜ አስገድዶ ሲደፍራት ወላጅ እናቷ ደርሳ ለፖሊስ አመልክታች።
ፈጽሞታል የተባለው የወንጀሉ ድርጊት በፖሊስ ከተጣራ በኋላ አቃቤ ህግ የመሰረተውን ክስ የተመለከተው የጃዊ ወረዳ ፍርድ ቤት በሰውና ሰነድ ማስረጃ አመሳክሮ ግለሰቡ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ ጳጉሜን 4/2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል።
መረጃ #2 ፦
በደብረ ማርቆስ ከተማ ህጻን አስገድዶ የመድፈር ሙከራ ባደረገ ግለሰብ ላይ በ12 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል።
የከተማ ነዋሪ የሆነው ግለሰብ ህጻኗን ብር ልስጥሽ በማለት ከቤት አታሎ በመውሰድ ሐምሌ 7/2012 ዓ/ም የመድፈር ሙከራ ማድረጉን በሰውና ሰነድ ማስረጃ ተረጋግጧል።
ድርጊቱን ፈጽሟል የተባለው የሃያ ሰባት (27) ዓመት እድሜ ያለው ጳውሎስ ምህረቴ ጥፈተኛነቱ ተረጋግጦበት የከተማው ፍርድ ቤት ጳጉሜን 5/2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት የቅጣት ውሳኔው ተላልፎበታል። (ኢዜአ)
@tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
ከግንቦት 28/2005 ዓ/ም ጀምሮ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት ከነገ መስከረም 5/2013 ዓ/ም ጀምሮ ኃላፊነቱ እንደተነሳላቸው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ አስታውቋል። @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በተለመደው የዪኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራር ምልመላ እና ስምሪት መመሪያ መሠረት የሥራ ጊዜያቸውን አጠናቀው በክብር መሰናበታቸውን ገልጿል።
ሚኒስቴሩ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በተሰጣቸው የኃላፊነት ጊዜ ላበረከቱት የላቀ አስተዋፆ ምስጋና አቅርቦላቸዋል።
በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት ከሃላፊነታቸው ተነሱ እየተባለ የሚሰራጨውና የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ሚኒስቴሩ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት በተሰጣቸው የኃላፊነት ጊዜ ላበረከቱት የላቀ አስተዋፆ ምስጋና አቅርቦላቸዋል።
በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት ከሃላፊነታቸው ተነሱ እየተባለ የሚሰራጨውና የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#SPHMMC
የቅዱስ ዻውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ (SPHMMC) ለ3 ወር ያህል አቋርጦት የነበረውን ህክምና መስጠት እንደጀመረ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
ሆስፒታሉ የኮሮና ወረርሽኝን በመከላከል ረገድ ምርመራዎች ማካሄድና ታካሚዎችን ከመንከባከብ ጋር ተያይዞ ወደ 25 ሺህ የሚጠጉ ምርመራዎችን እንዳከናወነ ነው የገለፀው።
270 አልጋዎችንም በማዘጋጀት ከኮሮና በሽታ ጋር ተያይዞ የተለየ ህክምና የሚያስፈልጋቸውን ታካሚዎች በመቀበል አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር ተጠቅሷል።
ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ እስከ 900 ሰዎችን በመቀበል 640 ድነው መውጣታቸውና አሁን ላይ ደግሞ 150 ሰዎች በህክምና ላይ የሚገኙ እንደሆኑ ተጠቁሟል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የቅዱስ ዻውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ (SPHMMC) ለ3 ወር ያህል አቋርጦት የነበረውን ህክምና መስጠት እንደጀመረ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
ሆስፒታሉ የኮሮና ወረርሽኝን በመከላከል ረገድ ምርመራዎች ማካሄድና ታካሚዎችን ከመንከባከብ ጋር ተያይዞ ወደ 25 ሺህ የሚጠጉ ምርመራዎችን እንዳከናወነ ነው የገለፀው።
270 አልጋዎችንም በማዘጋጀት ከኮሮና በሽታ ጋር ተያይዞ የተለየ ህክምና የሚያስፈልጋቸውን ታካሚዎች በመቀበል አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበር ተጠቅሷል።
ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ እስከ 900 ሰዎችን በመቀበል 640 ድነው መውጣታቸውና አሁን ላይ ደግሞ 150 ሰዎች በህክምና ላይ የሚገኙ እንደሆኑ ተጠቁሟል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አፋር ገዋኔ ወረዳ ገለዔ ለዶራ እና ገበያ ቦራ ቀበሌዎች ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቻችን በጎርፍ አደጋ ተፈናቅለዋል።
ዜጎቻችን በጎርፍ ቤታቸው ውድሞባቸዋል ፣ ለፀሐይ ተጋልጠዋል እስከሁን የተደረገላቸው ምንም ዓይነት እርዳታ የለም።
በአደጋው ምክንያት ለረሀብ እና ለውሃ ጥም የተጋለጡ ለነዚህ ምስኪን ወገኖቻችን በፍጥነት እረዳታ መደረግ ይኖርበታል (Hassen Koke)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዜጎቻችን በጎርፍ ቤታቸው ውድሞባቸዋል ፣ ለፀሐይ ተጋልጠዋል እስከሁን የተደረገላቸው ምንም ዓይነት እርዳታ የለም።
በአደጋው ምክንያት ለረሀብ እና ለውሃ ጥም የተጋለጡ ለነዚህ ምስኪን ወገኖቻችን በፍጥነት እረዳታ መደረግ ይኖርበታል (Hassen Koke)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia