TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.6K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
加入频道
#NobelPeacePrize

ከትናንት በስቲያ በኖርዌይ ኦስሎ በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማታቸውን ለተቀበሉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በአሁኑ ሰዓት በብሔራዊ ቤተመንግስት አቀባበል እና የእራት ግብዣ እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡ በኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ በተዘጋጀው በዚህ አቀባበል እና የእራት ግብዣ ላይ የፌደራል እና የክልል መንግስታት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

(ኢቢሲ)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

100ኛው የዓለም የሰላም ኖቤል ሽልማት አንደኛው ሜዳሊያና ዲፕሎማ በብሔራዊ ሙዚየም እንዲቀመጥ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ወስኗል። ሜዳሊያውና ዲፕሎማው በብሔራዊ ሙዚየም የሚቀመጠው እሁድ ታህሳስ 5 ከቀኑ 8፡30 ነው ተብሏል።

(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#NobelPeacePrize #AbiyAhemed

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ያገኙት የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት አንደኛው ሜዳሊያና ዲፕሎማ በብሔራዊ ሙዚየም የማስቀመጥ ስነ ስርዓት እየተከናወነ ነው።

(📸ኤፍቢሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia