ኮማንድ ፖስት!
በጌዴኦ ዞን #ሰላምና #መረጋጋትን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን በዞኑ የተቋቋመው ንዑስ ኮማንድ ፖስት ገለጸ፡፡ ንዑስ ኮማንድ ፖስቱ በዞኑ ነባራዊ ሁኔታ ላይ ከባለ ድርሻዎች ጋር ትናንት በዲላ ውይይት አካሂዷል። የንዑስ ኮማንድ ፖስቱ ሰብሳቢ ኮሎኔል መስፍን በየነ የዞኑን ሰላም ወደ ቀደመው ደረጃ ለመመለስ በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በጌዴኦ ዞን #ሰላምና #መረጋጋትን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን በዞኑ የተቋቋመው ንዑስ ኮማንድ ፖስት ገለጸ፡፡ ንዑስ ኮማንድ ፖስቱ በዞኑ ነባራዊ ሁኔታ ላይ ከባለ ድርሻዎች ጋር ትናንት በዲላ ውይይት አካሂዷል። የንዑስ ኮማንድ ፖስቱ ሰብሳቢ ኮሎኔል መስፍን በየነ የዞኑን ሰላም ወደ ቀደመው ደረጃ ለመመለስ በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ምስራቅ_ዕዝ
የህብረተሰቡን #ሰላምና #ደህንነት የማስጠበቅ ስራን እንደሚያጠናክር የምስራቅ ዕዝ አስታወቀ። የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ስራን በተጠናከረ መልኩ እንደሚያስቀጥል በሀገር መከላከያ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ዘውዱ በላይ አስታወቁ።
ዋና አዛዡ ዛሬ በጅግጅጋ ገርባሳ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋም የመካከለኛ አመራሮች ስልጠና በተጀመረበት ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት የህብረተሰቡን ሰላም የሚያውኩ አካላትን በመከላከሉ ረገድ ሰራዊቱ ከነዋሪው ጋር በመሆን የሚጠበቅበትን ግዳጅ ተወጥቷል።
“በአሁኑ ወቅትም በቀጠናው የተለያዩ የጸብ አጫሪነትና የጸረ ሰላም ተግባር ሲፈጠሩ ሰራዊቱ ከክልል የጸጥታ አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሰላምን የማስከበር ስራ እያከናወነ ይገኛል” ብለዋል። በዚህም የቀጠናው የሰላም ሁኔታ ከዓመት ዓመት መሻሻል እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
በቅርቡ በቀጠናው አንዳንድ ከተሞች በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ለማሰማት ዜጎች ወደ አደባባይ የወጡበትን አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን አጀንዳ ለማራመድ የሞከሩ ጥቂት ግለሰቦች እንደነበሩ አስታውሰዋል። ይህም ህብረተሰቡ በብሔርና በሃይማኖት ግጭት ውስጥ እንዲገባ ለማድረግ እንደነበረ ጠቅሰዋል።
ምንጭ፡- ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህብረተሰቡን #ሰላምና #ደህንነት የማስጠበቅ ስራን እንደሚያጠናክር የምስራቅ ዕዝ አስታወቀ። የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ስራን በተጠናከረ መልኩ እንደሚያስቀጥል በሀገር መከላከያ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ዘውዱ በላይ አስታወቁ።
ዋና አዛዡ ዛሬ በጅግጅጋ ገርባሳ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋም የመካከለኛ አመራሮች ስልጠና በተጀመረበት ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት የህብረተሰቡን ሰላም የሚያውኩ አካላትን በመከላከሉ ረገድ ሰራዊቱ ከነዋሪው ጋር በመሆን የሚጠበቅበትን ግዳጅ ተወጥቷል።
“በአሁኑ ወቅትም በቀጠናው የተለያዩ የጸብ አጫሪነትና የጸረ ሰላም ተግባር ሲፈጠሩ ሰራዊቱ ከክልል የጸጥታ አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሰላምን የማስከበር ስራ እያከናወነ ይገኛል” ብለዋል። በዚህም የቀጠናው የሰላም ሁኔታ ከዓመት ዓመት መሻሻል እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
በቅርቡ በቀጠናው አንዳንድ ከተሞች በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ለማሰማት ዜጎች ወደ አደባባይ የወጡበትን አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን አጀንዳ ለማራመድ የሞከሩ ጥቂት ግለሰቦች እንደነበሩ አስታውሰዋል። ይህም ህብረተሰቡ በብሔርና በሃይማኖት ግጭት ውስጥ እንዲገባ ለማድረግ እንደነበረ ጠቅሰዋል።
ምንጭ፡- ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia