የቦሌ ክ/ከተማ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት/...
ዛሬ መጋቢት 09/2011ዓ.ም በክ/ከተማችን ውስጥ ወረዳ 1 ልዩ ስሙ ቦሌ ሚካኤል በሚባለው ሰፈር በቄሮዎች እና በአካባቢው ወጣቶች መካከል ግጭት እንደተፈጠረ ተደርጎ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚንሸራሸረው ዜና ሐሰት እንደሆነ በስፍራው በመገኘት ማረጋገጥ ችለናል፡፡ በርግጥ የግለሰቦች ግጭት ነበር፤ የጠቡ መንስኤ የታክሲ ተራ አስከባሪዎች ከጫት ነጋዴዎች ጋር የፈጠሩት አለመግባባት ሲሆን በግጭቱ በአቅራቢያው የነበረ የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ የሚገኝበት ሕንጻ መስተዋት መጠነኛ የመሰበር አደጋ ከመድረሱ በስተቀር በሰው ላይ የደረሰ ምንም አይነት ጉዳት የለም፡፡በአሁኑ ሰአትም ሰላማዊ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬ መጋቢት 09/2011ዓ.ም በክ/ከተማችን ውስጥ ወረዳ 1 ልዩ ስሙ ቦሌ ሚካኤል በሚባለው ሰፈር በቄሮዎች እና በአካባቢው ወጣቶች መካከል ግጭት እንደተፈጠረ ተደርጎ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚንሸራሸረው ዜና ሐሰት እንደሆነ በስፍራው በመገኘት ማረጋገጥ ችለናል፡፡ በርግጥ የግለሰቦች ግጭት ነበር፤ የጠቡ መንስኤ የታክሲ ተራ አስከባሪዎች ከጫት ነጋዴዎች ጋር የፈጠሩት አለመግባባት ሲሆን በግጭቱ በአቅራቢያው የነበረ የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ የሚገኝበት ሕንጻ መስተዋት መጠነኛ የመሰበር አደጋ ከመድረሱ በስተቀር በሰው ላይ የደረሰ ምንም አይነት ጉዳት የለም፡፡በአሁኑ ሰአትም ሰላማዊ እንቅስቃሴ ነው ያለው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬ በቦሌ ስለተፈጠረው ጉዳይ በቦታው የነበሩ አካላትን ማግኘት ከቻልኩ ምን እንደተፈጠረ ጠይቄ ተጨማሪ መረጃ አደርሳችኃለሁ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሳነ ሊቀጳጳሳት አቡነ ፍራንሲስ በደቡብ ሱዳን ለተደረሰው የሰላም ስምምነት ያላቸውን ድጋፍ ለመግለፅ ያለመ ጉብኝት በሀገሪቱ ሊያደርጉ ነው፡፡ በቫቲካን ከሀገሪቱ ኘሬዝዳንት ሳልቫኪር ጋር የተወያዩት አቡነ ፍራንሲስ ለማድረግ ያለሙት ጉብኝት ለሀገሪቱ ህዝቦች ያላቸውን ቅርበትና የሰላም ሂደቱን ለማበረታታት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሁለቱ መሪዎች ውይይት በሰላም ሒደቱ፣ የተሰደዱ የሀገሪቱ ዜጎች በሚመለሱበትና በቀጣይ የልማት ዙሪያ ያተኮረ እንደነበር ቫቲካን ገልፃለች፡፡ አቡነ ፍራንሲስ ከ2 አመት በፊት ደቡብ ሱዳን ለመጎብኘት የነበራችውን ዕቅድ በሀገሪቱ በነበረው አለመረጋጋት ምክንያት ማዘግየታቸው ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡- አሶሼትድ ኘሬስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፡- አሶሼትድ ኘሬስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰላም ሚኒቴር‼️
በምንጃር ሸንኮራ እና ፈንታሌ ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት በቁጥጥር ስር መዋሉን የሰላም ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ እና በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ መካከል አሞራ ቤት በምትባል ቀበሌ እንስሳትን ውሃ በማጠጣት ሂደት የተፈጠረው ግጭት በዛሬው ዕለት በቁጥጥር መዋሉን በሚኒስቴሩ የግጭት አፈታት ዳይሬክተሩ አቶ ኃይለአብ ጌታቸው ለebc ተናግረዋል፡፡
ዳይሬክተሩ እንዳስታወቁት በአዋሳኝ አካባቢዎቹ መጋቢት 8 ፣2011 የተፈጠረው ግጭት እንሰሳትን ውሃ ለማጠጣት በሚል ምክንያት ተጀምሮ ለሁለት ሰው ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል፡፡
በግጭቱ በሁለቱም ወገን ከሞቱት ሁለት ሰዎች በተጨማሪ በሰባት ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡
የመከላከያ ሠራዊትም ግጭት በተፈጠረበት አካባቢ ገብቶ የማረጋጋት ስራ እየሰራ እንደሆነም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
የሁለቱ ዞን አስተዳዳሪዎች ግጭት በተፈጠረበት አካባቢ ዛሬ በመሄድ ህዝቡን በማወያየት ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረጉ መሆኑንም አቶ ኃይለአብ አመልክተዋል።
በእንሰሳት ግጦሽ እና የመጠጥ ውሃ የተፈጠረው አለመግባባት ከዚህ በፊትም እንደሚከሰትና በሁለቱም ወገን በኩል ያሉ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ እንደከዚህ ቀደም ባሉ ውይይቶች ችግሩን እንደሚፈቱት ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።
Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በምንጃር ሸንኮራ እና ፈንታሌ ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት በቁጥጥር ስር መዋሉን የሰላም ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ እና በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ መካከል አሞራ ቤት በምትባል ቀበሌ እንስሳትን ውሃ በማጠጣት ሂደት የተፈጠረው ግጭት በዛሬው ዕለት በቁጥጥር መዋሉን በሚኒስቴሩ የግጭት አፈታት ዳይሬክተሩ አቶ ኃይለአብ ጌታቸው ለebc ተናግረዋል፡፡
ዳይሬክተሩ እንዳስታወቁት በአዋሳኝ አካባቢዎቹ መጋቢት 8 ፣2011 የተፈጠረው ግጭት እንሰሳትን ውሃ ለማጠጣት በሚል ምክንያት ተጀምሮ ለሁለት ሰው ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል፡፡
በግጭቱ በሁለቱም ወገን ከሞቱት ሁለት ሰዎች በተጨማሪ በሰባት ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡
የመከላከያ ሠራዊትም ግጭት በተፈጠረበት አካባቢ ገብቶ የማረጋጋት ስራ እየሰራ እንደሆነም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡
የሁለቱ ዞን አስተዳዳሪዎች ግጭት በተፈጠረበት አካባቢ ዛሬ በመሄድ ህዝቡን በማወያየት ችግሩን ለመፍታት ጥረት እያደረጉ መሆኑንም አቶ ኃይለአብ አመልክተዋል።
በእንሰሳት ግጦሽ እና የመጠጥ ውሃ የተፈጠረው አለመግባባት ከዚህ በፊትም እንደሚከሰትና በሁለቱም ወገን በኩል ያሉ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ እንደከዚህ ቀደም ባሉ ውይይቶች ችግሩን እንደሚፈቱት ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።
Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአርበኞች ግንቦት ሰባት የውጪ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ነዓምን ዘለቀ ከድርጅቱ ሀላፊነት መልቀቃቸውን አስታወቁ። ኢሳት እንደዘገበው ከኤርትራ የተመለሱ የድርጅቱ ወታደሮች አያያዝ እንቅልፍ ስለነሳኝ ሀላፊነቴን በገዛ ፈቀዴ ለቅቄያለሁ ብለዋል። ከዚህ ቀደምም ከድርጅቱ ለመልቀቅ ሀሳብ እንደነበራቸው ያመለከቱት አቶ ነዓምን ከማናቸውም የድርጅቱ አባላትም ሆነ አመራሮች ጋር የግል ቅራኔ የለኝም ብለዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህዝብና ቤት ቆጠራ ኮሚሽን ትላንት መጋቢት 9 ቀን 2011 ባካሄደው ስብሰባ አራተኛዉን የህዝብና ቤት ቆጠራ ለማካሄድ የተደረገዉን ዝግጅት በመገምገም የዉሳኔ ሃሳቦች ኣሳልፏል::
በዚህም መሠረት:-
• የሕዝብና ቤት ቆጠራው እንዲቀጥል በቴክኒክ ደረጃ በቂ ዝጅግት የተደረገ መሆኑንና ኮሚሽኑና ማእከላዊ እስታትስቲክስ ኤጀንሲ ሰፊ ስራ የሰሩ መሆኑን፤
• የካርታ እና ተያያዥ ስራዎች እየተገባደዱ መሆኑን፤
• ሌሎች ዝግጅቶችም እየተደረጉ መሆኑን ግንዛቤ ወስዶ የቆጠራውን አላማና ግብ በአስተማማኝ ሁኔታ ለማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት የተሟሉ ባለመሆናቸው ማለትም በየአካባቢው ለስራው መሳካት በተገቢው ሁኔታ መጠናቀቅ የሚገባቸው ተግባራት ባለመጠናቀቃቸው እና ተጨማሪ ግዜ የሚያስፈልግ በመሆኑ፤
• ምንም አንኳን ለቆጠራ የቀሩን ቀናት ጥቂት ቢሆንም በተለያዩ ገጭቶች ምክንያት የትፈናቀሉ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ወገኖች ወደነበሩበት ቀዬ የመመለሱ ስራ በበቂ ሁኔታ ባለመሰራቱ አሁንም በርካታ ዜጎች በጊዜያዊ መጠለያ የሚገኙ በመሆኑ እነዚህ ወገኖች ትርጉም ባለው ደረጃ ወደ ነበሩበት ቦታ እስኪመለሱ ድረስ ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ ቆጠራው እንዲራዘም የውሳኔ ሃሳቡን ለተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች እንዲቀርብ በአብላጫ ድምፅ ወስኗል።
#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዚህም መሠረት:-
• የሕዝብና ቤት ቆጠራው እንዲቀጥል በቴክኒክ ደረጃ በቂ ዝጅግት የተደረገ መሆኑንና ኮሚሽኑና ማእከላዊ እስታትስቲክስ ኤጀንሲ ሰፊ ስራ የሰሩ መሆኑን፤
• የካርታ እና ተያያዥ ስራዎች እየተገባደዱ መሆኑን፤
• ሌሎች ዝግጅቶችም እየተደረጉ መሆኑን ግንዛቤ ወስዶ የቆጠራውን አላማና ግብ በአስተማማኝ ሁኔታ ለማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት የተሟሉ ባለመሆናቸው ማለትም በየአካባቢው ለስራው መሳካት በተገቢው ሁኔታ መጠናቀቅ የሚገባቸው ተግባራት ባለመጠናቀቃቸው እና ተጨማሪ ግዜ የሚያስፈልግ በመሆኑ፤
• ምንም አንኳን ለቆጠራ የቀሩን ቀናት ጥቂት ቢሆንም በተለያዩ ገጭቶች ምክንያት የትፈናቀሉ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ወገኖች ወደነበሩበት ቀዬ የመመለሱ ስራ በበቂ ሁኔታ ባለመሰራቱ አሁንም በርካታ ዜጎች በጊዜያዊ መጠለያ የሚገኙ በመሆኑ እነዚህ ወገኖች ትርጉም ባለው ደረጃ ወደ ነበሩበት ቦታ እስኪመለሱ ድረስ ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ ቆጠራው እንዲራዘም የውሳኔ ሃሳቡን ለተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች እንዲቀርብ በአብላጫ ድምፅ ወስኗል።
#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኦሮሚያ ክልል ም/ፕሬዝዳንት ወ/ሮ #ጠይባ_ሀሰን በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ ሕገ ወጥ ግንባታዎች ከፈረሱባቸው የማህበረሰቡ አካላት ጋር በትላንትናው ዕለት ውይይት አድርገዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዲላ ዩኒቨርሲቲ🔝
#የዲላ_ዩኒቨርሲቲ በጎ አድራጎት ክበብ በጌዴኦ ዞን ለሚገኙ የተፈናቀሉት ወገኖች ገቢ ማሰባሰቢያ የሶስት ቀን ዜር ፎር (የስጋ አቅርቦት) ለማስቀረት ዛሬ የፒቲሽን ማሰባሰብ ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ የተቋሙ ተማሪዎችም ትብብር እድታደርጉላቸው ጠይቀዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የዲላ_ዩኒቨርሲቲ በጎ አድራጎት ክበብ በጌዴኦ ዞን ለሚገኙ የተፈናቀሉት ወገኖች ገቢ ማሰባሰቢያ የሶስት ቀን ዜር ፎር (የስጋ አቅርቦት) ለማስቀረት ዛሬ የፒቲሽን ማሰባሰብ ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ የተቋሙ ተማሪዎችም ትብብር እድታደርጉላቸው ጠይቀዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በኮንግ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በተከሰተ የባቡር #መገልበጥ አደጋ በትንሹ 24 ሰዎች #መሞታቸው ተሰምቷል። ከሟቾች መካከል አብዛኛዎቸ ህጻናት ናቸው ተብሏል። በካሳይ ገዛት በደረሰው አደጋ ከ30 በላይ ሰዎችም አካላዊ ጉዳት እንደደረሰባቸው ነው የተጠቆመው። የእቃ ማጓጓዣ ባቡሩ ሰዎችንም አሳፍሮ ሲጓዝ አደጋው የደረሰ ሲሆን በርካታ ተሳቢዎቹ ወደ ወንዝ መግባታቸውን ፖሊስ ገልጿል።
Via ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-MAGAZINE
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"ያለንበትን ዘመን በቅጡ መረዳት ያስፈልጋል ብየ አምናለሁ"- ጸሀፊና ፖለቲከኛ አንዱአለም አራጌ
.
.
- ያለንበት ዘመን በዘመናት መካከል ያለ ብልጭታ ነው፡፡
- ዘረኝነት ወደ ጥፋት የሚወስደን ትልቅ አዘቅት ነው፡፡
- ወደ ተስፋ ሙላት ልንሸጋገር ጫፍ ላይ እንገኛለን፡፡
- ከጨለማ ብርሀን፣ ከጥላቻ ፍቅርን፣ ከመገዳደል መከባበርና መዋደድን መምረጥ አለብን፡፡
- ህልማችንና ራዕያችን ሩቅ የተሰቀለ ዳቦ አይደለም፡፡
- ዲሞክራሲ የመወለድ ምጥ ላይ ነው፤ ሁላችንም ልናዋልደው ይገባል፡፡
ጸሀፊና ፖለቲከኛ አንዱአለም አራጌ ከጠ/ሚር ፅ/ቤት “ኢትዮጵያ የእኔም ናት” ጋር ካደረገው ንግግር የተወሰደ!
Via EPA
@tsegabwolde1
.
.
- ያለንበት ዘመን በዘመናት መካከል ያለ ብልጭታ ነው፡፡
- ዘረኝነት ወደ ጥፋት የሚወስደን ትልቅ አዘቅት ነው፡፡
- ወደ ተስፋ ሙላት ልንሸጋገር ጫፍ ላይ እንገኛለን፡፡
- ከጨለማ ብርሀን፣ ከጥላቻ ፍቅርን፣ ከመገዳደል መከባበርና መዋደድን መምረጥ አለብን፡፡
- ህልማችንና ራዕያችን ሩቅ የተሰቀለ ዳቦ አይደለም፡፡
- ዲሞክራሲ የመወለድ ምጥ ላይ ነው፤ ሁላችንም ልናዋልደው ይገባል፡፡
ጸሀፊና ፖለቲከኛ አንዱአለም አራጌ ከጠ/ሚር ፅ/ቤት “ኢትዮጵያ የእኔም ናት” ጋር ካደረገው ንግግር የተወሰደ!
Via EPA
@tsegabwolde1